ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية * - فهرس التراجم

XML CSV Excel API
تنزيل الملفات يتضمن الموافقة على هذه الشروط والسياسات

ترجمة معاني سورة: الحاقة   آية:

سورة الحاقة - ሱረቱ አል ሓቃህ

ٱلۡحَآقَّةُ
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
التفاسير العربية:
مَا ٱلۡحَآقَّةُ
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
التفاسير العربية:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحَآقَّةُ
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
التفاسير العربية:
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ وَعَادُۢ بِٱلۡقَارِعَةِ
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
التفاسير العربية:
فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهۡلِكُواْ بِٱلطَّاغِيَةِ
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
التفاسير العربية:
وَأَمَّا عَادٞ فَأُهۡلِكُواْ بِرِيحٖ صَرۡصَرٍ عَاتِيَةٖ
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
التفاسير العربية:
سَخَّرَهَا عَلَيۡهِمۡ سَبۡعَ لَيَالٖ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومٗاۖ فَتَرَى ٱلۡقَوۡمَ فِيهَا صَرۡعَىٰ كَأَنَّهُمۡ أَعۡجَازُ نَخۡلٍ خَاوِيَةٖ
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
التفاسير العربية:
فَهَلۡ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٖ
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
التفاسير العربية:
وَجَآءَ فِرۡعَوۡنُ وَمَن قَبۡلَهُۥ وَٱلۡمُؤۡتَفِكَٰتُ بِٱلۡخَاطِئَةِ
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
التفاسير العربية:
فَعَصَوۡاْ رَسُولَ رَبِّهِمۡ فَأَخَذَهُمۡ أَخۡذَةٗ رَّابِيَةً
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّا لَمَّا طَغَا ٱلۡمَآءُ حَمَلۡنَٰكُمۡ فِي ٱلۡجَارِيَةِ
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
التفاسير العربية:
لِنَجۡعَلَهَا لَكُمۡ تَذۡكِرَةٗ وَتَعِيَهَآ أُذُنٞ وَٰعِيَةٞ
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
التفاسير العربية:
فَإِذَا نُفِخَ فِي ٱلصُّورِ نَفۡخَةٞ وَٰحِدَةٞ
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
التفاسير العربية:
وَحُمِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ وَٱلۡجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةٗ وَٰحِدَةٗ
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
التفاسير العربية:
فَيَوۡمَئِذٖ وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
التفاسير العربية:
وَٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَهِيَ يَوۡمَئِذٖ وَاهِيَةٞ
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
التفاسير العربية:
وَٱلۡمَلَكُ عَلَىٰٓ أَرۡجَآئِهَاۚ وَيَحۡمِلُ عَرۡشَ رَبِّكَ فَوۡقَهُمۡ يَوۡمَئِذٖ ثَمَٰنِيَةٞ
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
التفاسير العربية:
يَوۡمَئِذٖ تُعۡرَضُونَ لَا تَخۡفَىٰ مِنكُمۡ خَافِيَةٞ
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
التفاسير العربية:
فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
التفاسير العربية:
إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
التفاسير العربية:
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
التفاسير العربية:
فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
التفاسير العربية:
قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
التفاسير العربية:
كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
التفاسير العربية:
وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
التفاسير العربية:
وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
التفاسير العربية:
يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
التفاسير العربية:
مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
التفاسير العربية:
هَلَكَ عَنِّي سُلۡطَٰنِيَهۡ
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
التفاسير العربية:
خُذُوهُ فَغُلُّوهُ
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
التفاسير العربية:
ثُمَّ ٱلۡجَحِيمَ صَلُّوهُ
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
التفاسير العربية:
ثُمَّ فِي سِلۡسِلَةٖ ذَرۡعُهَا سَبۡعُونَ ذِرَاعٗا فَٱسۡلُكُوهُ
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
التفاسير العربية:
إِنَّهُۥ كَانَ لَا يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
التفاسير العربية:
وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
التفاسير العربية:
فَلَيۡسَ لَهُ ٱلۡيَوۡمَ هَٰهُنَا حَمِيمٞ
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
التفاسير العربية:
وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنۡ غِسۡلِينٖ
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
التفاسير العربية:
لَّا يَأۡكُلُهُۥٓ إِلَّا ٱلۡخَٰطِـُٔونَ
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
التفاسير العربية:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَا تُبۡصِرُونَ
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
التفاسير العربية:
وَمَا لَا تُبۡصِرُونَ
በማታዩትም ነገር፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
التفاسير العربية:
وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
التفاسير العربية:
وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
التفاسير العربية:
تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
التفاسير العربية:
وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
التفاسير العربية:
لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ
በቀኝ በያዝነው ነበር፡፡
التفاسير العربية:
ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
التفاسير العربية:
فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
التفاسير العربية:
وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
التفاسير العربية:
وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
التفاسير العربية:
وَإِنَّهُۥ لَحَسۡرَةٌ عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
التفاسير العربية:
وَإِنَّهُۥ لَحَقُّ ٱلۡيَقِينِ
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
التفاسير العربية:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
التفاسير العربية:
 
ترجمة معاني سورة: الحاقة
فهرس السور رقم الصفحة
 
ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - فهرس التراجم

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

إغلاق