কুরআনুল কারীমের অর্থসমূহের অনুবাদ - আমহারীয় ভাষায় অনুবাদ * - অনুবাদসমূহের সূচী

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

অর্থসমূহের অনুবাদ সূরা: সূরা আল-মাআরিজ   আয়াত:

ሱረቱ አል መዓሪጅ

سَأَلَ سَآئِلُۢ بِعَذَابٖ وَاقِعٖ
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
لِّلۡكَٰفِرِينَ لَيۡسَ لَهُۥ دَافِعٞ
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
مِّنَ ٱللَّهِ ذِي ٱلۡمَعَارِجِ
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
تَعۡرُجُ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ وَٱلرُّوحُ إِلَيۡهِ فِي يَوۡمٖ كَانَ مِقۡدَارُهُۥ خَمۡسِينَ أَلۡفَ سَنَةٖ
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَٱصۡبِرۡ صَبۡرٗا جَمِيلًا
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِنَّهُمۡ يَرَوۡنَهُۥ بَعِيدٗا
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَنَرَىٰهُ قَرِيبٗا
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
يَوۡمَ تَكُونُ ٱلسَّمَآءُ كَٱلۡمُهۡلِ
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَتَكُونُ ٱلۡجِبَالُ كَٱلۡعِهۡنِ
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَلَا يَسۡـَٔلُ حَمِيمٌ حَمِيمٗا
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
يُبَصَّرُونَهُمۡۚ يَوَدُّ ٱلۡمُجۡرِمُ لَوۡ يَفۡتَدِي مِنۡ عَذَابِ يَوۡمِئِذِۭ بِبَنِيهِ
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَأَخِيهِ
በሚስቱም በወንድሙም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَفَصِيلَتِهِ ٱلَّتِي تُـٔۡوِيهِ
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَمَن فِي ٱلۡأَرۡضِ جَمِيعٗا ثُمَّ يُنجِيهِ
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
كَلَّآۖ إِنَّهَا لَظَىٰ
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
نَزَّاعَةٗ لِّلشَّوَىٰ
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
تَدۡعُواْ مَنۡ أَدۡبَرَ وَتَوَلَّىٰ
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَجَمَعَ فَأَوۡعَىٰٓ
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
۞ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ خُلِقَ هَلُوعًا
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِذَا مَسَّهُ ٱلشَّرُّ جَزُوعٗا
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَإِذَا مَسَّهُ ٱلۡخَيۡرُ مَنُوعًا
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِلَّا ٱلۡمُصَلِّينَ
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
ٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ دَآئِمُونَ
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ فِيٓ أَمۡوَٰلِهِمۡ حَقّٞ مَّعۡلُومٞ
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
لِّلسَّآئِلِ وَٱلۡمَحۡرُومِ
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ هُم مِّنۡ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشۡفِقُونَ
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمۡ غَيۡرُ مَأۡمُونٖ
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِفُرُوجِهِمۡ حَٰفِظُونَ
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِلَّا عَلَىٰٓ أَزۡوَٰجِهِمۡ أَوۡ مَا مَلَكَتۡ أَيۡمَٰنُهُمۡ فَإِنَّهُمۡ غَيۡرُ مَلُومِينَ
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَمَنِ ٱبۡتَغَىٰ وَرَآءَ ذَٰلِكَ فَأُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡعَادُونَ
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ هُمۡ لِأَمَٰنَٰتِهِمۡ وَعَهۡدِهِمۡ رَٰعُونَ
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ هُم بِشَهَٰدَٰتِهِمۡ قَآئِمُونَ
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلَّذِينَ هُمۡ عَلَىٰ صَلَاتِهِمۡ يُحَافِظُونَ
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
أُوْلَٰٓئِكَ فِي جَنَّٰتٖ مُّكۡرَمُونَ
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَمَالِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ قِبَلَكَ مُهۡطِعِينَ
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው?
আরবি তাফসীরসমূহ:
عَنِ ٱلۡيَمِينِ وَعَنِ ٱلشِّمَالِ عِزِينَ
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
أَيَطۡمَعُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُدۡخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٖ
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን?
আরবি তাফসীরসমূহ:
كَلَّآۖ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّمَّا يَعۡلَمُونَ
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِرَبِّ ٱلۡمَشَٰرِقِ وَٱلۡمَغَٰرِبِ إِنَّا لَقَٰدِرُونَ
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ خَيۡرٗا مِّنۡهُمۡ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَذَرۡهُمۡ يَخُوضُواْ وَيَلۡعَبُواْ حَتَّىٰ يُلَٰقُواْ يَوۡمَهُمُ ٱلَّذِي يُوعَدُونَ
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
يَوۡمَ يَخۡرُجُونَ مِنَ ٱلۡأَجۡدَاثِ سِرَاعٗا كَأَنَّهُمۡ إِلَىٰ نُصُبٖ يُوفِضُونَ
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
خَٰشِعَةً أَبۡصَٰرُهُمۡ تَرۡهَقُهُمۡ ذِلَّةٞۚ ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلَّذِي كَانُواْ يُوعَدُونَ
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
 
অর্থসমূহের অনুবাদ সূরা: সূরা আল-মাআরিজ
সূরাসমূহের সূচী পৃষ্ঠার নাম্বার
 
কুরআনুল কারীমের অর্থসমূহের অনুবাদ - আমহারীয় ভাষায় অনুবাদ - অনুবাদসমূহের সূচী

আমহারিক ভাষায় আল-কুরআনুল কারীমের অর্থসমূহের অনুবাদ। শায়েখ মুহাম্মদ সাদিক এবং মুহাম্মদ ছানী হাবীব অনূদিত। অতপর মারকাযু রুওয়াদুদ তরজমার তত্ত্বাবধানে সংশোধন করা হয়েছে। পরামর্শ, মূল্যায়ন ও উত্তরোত্তর উন্নতির স্বার্থে মূল অনুবাদ দেখারও সুযোগ রয়েছে।

বন্ধ