কুরআনুল কারীমের অর্থসমূহের অনুবাদ - আমহারীয় ভাষায় অনুবাদ * - অনুবাদসমূহের সূচী

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

অর্থসমূহের অনুবাদ সূরা: সূরা আন-নাযেআত   আয়াত:

ሱረቱ አን ናዚዓት

وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
আরবি তাফসীরসমূহ:
تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»
আরবি তাফসীরসমূহ:
قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
የሙሳ ወሬ መጣልህን?
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤
আরবি তাফসীরসমূহ:
ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣
আরবি তাফসীরসমূহ:
يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
የካደ ሰውማ፣
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ
আরবি তাফসীরসমূহ:
فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡
আরবি তাফসীরসমূহ:
 
অর্থসমূহের অনুবাদ সূরা: সূরা আন-নাযেআত
সূরাসমূহের সূচী পৃষ্ঠার নাম্বার
 
কুরআনুল কারীমের অর্থসমূহের অনুবাদ - আমহারীয় ভাষায় অনুবাদ - অনুবাদসমূহের সূচী

আমহারিক ভাষায় আল-কুরআনুল কারীমের অর্থসমূহের অনুবাদ। শায়েখ মুহাম্মদ সাদিক এবং মুহাম্মদ ছানী হাবীব অনূদিত। অতপর মারকাযু রুওয়াদুদ তরজমার তত্ত্বাবধানে সংশোধন করা হয়েছে। পরামর্শ, মূল্যায়ন ও উত্তরোত্তর উন্নতির স্বার্থে মূল অনুবাদ দেখারও সুযোগ রয়েছে।

বন্ধ