Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation * - Translations’ Index

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Translation of the meanings Surah: Al-Burūj   Ayah:

ሱረቱ አል ቡሩጅ

وَٱلسَّمَآءِ ذَاتِ ٱلۡبُرُوجِ
የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَٱلۡيَوۡمِ ٱلۡمَوۡعُودِ
በተቀጠረው ቀንም፤
Arabic explanations of the Qur’an:
وَشَاهِدٖ وَمَشۡهُودٖ
በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
قُتِلَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡأُخۡدُودِ
የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ٱلنَّارِ ذَاتِ ٱلۡوَقُودِ
የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِذۡ هُمۡ عَلَيۡهَا قُعُودٞ
እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَهُمۡ عَلَىٰ مَا يَفۡعَلُونَ بِٱلۡمُؤۡمِنِينَ شُهُودٞ
እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَا نَقَمُواْ مِنۡهُمۡ إِلَّآ أَن يُؤۡمِنُواْ بِٱللَّهِ ٱلۡعَزِيزِ ٱلۡحَمِيدِ
ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ٱلَّذِي لَهُۥ مُلۡكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ وَٱللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيۡءٖ شَهِيدٌ
በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ ٱلَّذِينَ فَتَنُواْ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ وَٱلۡمُؤۡمِنَٰتِ ثُمَّ لَمۡ يَتُوبُواْ فَلَهُمۡ عَذَابُ جَهَنَّمَ وَلَهُمۡ عَذَابُ ٱلۡحَرِيقِ
እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ جَنَّٰتٞ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُۚ ذَٰلِكَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡكَبِيرُ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ بَطۡشَ رَبِّكَ لَشَدِيدٌ
የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّهُۥ هُوَ يُبۡدِئُ وَيُعِيدُ
እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَهُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلۡوَدُودُ
እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ذُو ٱلۡعَرۡشِ ٱلۡمَجِيدُ
የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
فَعَّالٞ لِّمَا يُرِيدُ
የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ ٱلۡجُنُودِ
የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?
Arabic explanations of the Qur’an:
فِرۡعَوۡنَ وَثَمُودَ
የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ فِي تَكۡذِيبٖ
በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
وَٱللَّهُ مِن وَرَآئِهِم مُّحِيطُۢ
አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
بَلۡ هُوَ قُرۡءَانٞ مَّجِيدٞ
ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
فِي لَوۡحٖ مَّحۡفُوظِۭ
የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
 
Translation of the meanings Surah: Al-Burūj
Surahs’ Index Page Number
 
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Translations’ Index

Translation of the Quran meanings into Amharic by Muhammad Sadeq and Muhammad Ath-Thany Habib. Corrected by supervision of Rowwad Translation Center. The original translation is available for suggestions, continuous evaluation and development.

close