قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہری ترجمہ * - ترجمے کی لسٹ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ حاقہ   آیت:

ሱረቱ አል ሓቃህ

ٱلۡحَآقَّةُ
እውነትን አረጋጋጪቱ (ትንሣኤ)፡፡
عربی تفاسیر:
مَا ٱلۡحَآقَّةُ
አረጋጋጪቱም (እርሷ) ምንድን ናት!
عربی تفاسیر:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا ٱلۡحَآقَّةُ
አረጋጋጪቱም ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
عربی تفاسیر:
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ وَعَادُۢ بِٱلۡقَارِعَةِ
ሰሙድና ዓድ በቆርቋሪይቱ (ትንሣኤ) አስተባበሉ፡፡
عربی تفاسیر:
فَأَمَّا ثَمُودُ فَأُهۡلِكُواْ بِٱلطَّاغِيَةِ
ሠሙድማ ወሰን በሌላት ጩኸት ተጠፋ፤ (ተወደሙ)፡፡
عربی تفاسیر:
وَأَمَّا عَادٞ فَأُهۡلِكُواْ بِرِيحٖ صَرۡصَرٍ عَاتِيَةٖ
ዓድማ በኀይል በምትንሻሻ ብርቱ ነፋስ ተጠፉ፡፡
عربی تفاسیر:
سَخَّرَهَا عَلَيۡهِمۡ سَبۡعَ لَيَالٖ وَثَمَٰنِيَةَ أَيَّامٍ حُسُومٗاۖ فَتَرَى ٱلۡقَوۡمَ فِيهَا صَرۡعَىٰ كَأَنَّهُمۡ أَعۡجَازُ نَخۡلٍ خَاوِيَةٖ
ተከታታይ በኾኑ ሰባት ሌሊቶችና ስምንት መዓልቶች ውስጥ በእነርሱ ላይ ለቀቃት፡፡ ሕዝቦቹንም፤ በውስጧ የተጣሉ ኾነው ልክ ክፍት የኾኑ የዘንባባ ግንዶች መስለው ታያቸዋለህ፡፡
عربی تفاسیر:
فَهَلۡ تَرَىٰ لَهُم مِّنۢ بَاقِيَةٖ
ለእነርሱም ቀሪን ታያለህን?
عربی تفاسیر:
وَجَآءَ فِرۡعَوۡنُ وَمَن قَبۡلَهُۥ وَٱلۡمُؤۡتَفِكَٰتُ بِٱلۡخَاطِئَةِ
ፈርዖን ከበፊቱ የነበሩትም ሰዎች ተገልባጮቹም (ከተሞች) በኀጢአት (ሥራዎች) መጡ፡፡
عربی تفاسیر:
فَعَصَوۡاْ رَسُولَ رَبِّهِمۡ فَأَخَذَهُمۡ أَخۡذَةٗ رَّابِيَةً
የጌታቸውንም መልእክተኛ ትዕዛዝ ጣሱ፡፡ የበረታችንም አያያዝ ያዛቸው፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّا لَمَّا طَغَا ٱلۡمَآءُ حَمَلۡنَٰكُمۡ فِي ٱلۡجَارِيَةِ
እኛ ውሃው ባየለ ጊዜ በተንሻላይቱ ታንኳ ውስጥ ጫንናችሁ፡፡
عربی تفاسیر:
لِنَجۡعَلَهَا لَكُمۡ تَذۡكِرَةٗ وَتَعِيَهَآ أُذُنٞ وَٰعِيَةٞ
ለእናንተ መገሰጫ ልናደርጋት አጥኒ የኾነችም ጆሮ ታጠናት ዘንድ፡፡
عربی تفاسیر:
فَإِذَا نُفِخَ فِي ٱلصُّورِ نَفۡخَةٞ وَٰحِدَةٞ
በቀንዱም አንዲት መንነፋት በተነፋች ጊዜ፡፡
عربی تفاسیر:
وَحُمِلَتِ ٱلۡأَرۡضُ وَٱلۡجِبَالُ فَدُكَّتَا دَكَّةٗ وَٰحِدَةٗ
ምድርና ጋራዎችም (ከስፍራቸው) በተነሱና አንዲትን መሰባበር በተሰባበሩ ጊዜ፡፡
عربی تفاسیر:
فَيَوۡمَئِذٖ وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ
በዚያ ቀን ኋኝቱ (ትንሣኤ) ትኾናለች፡፡
عربی تفاسیر:
وَٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَهِيَ يَوۡمَئِذٖ وَاهِيَةٞ
ሰማይም ትቀደዳለች፡፡ ስለዚህ እርሷ በዚያ ቀን ደካማ ናት፡፡
عربی تفاسیر:
وَٱلۡمَلَكُ عَلَىٰٓ أَرۡجَآئِهَاۚ وَيَحۡمِلُ عَرۡشَ رَبِّكَ فَوۡقَهُمۡ يَوۡمَئِذٖ ثَمَٰنِيَةٞ
መላእክትም በየጫፎችዋ ላይ ይኾናሉ፡፡ የጌታህንም ዐርሽ በዚያ ቀን ስምንት መላእክት ከበላያቸው ይሸከማሉ፡፡
عربی تفاسیر:
يَوۡمَئِذٖ تُعۡرَضُونَ لَا تَخۡفَىٰ مِنكُمۡ خَافِيَةٞ
በዚያ ቀን ከእናንተ ተደባቂ (ነገሮች) የማይደበቁ ሲኾኑ ትቅቀረባላችሁ፡፡
عربی تفاسیر:
فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ فَيَقُولُ هَآؤُمُ ٱقۡرَءُواْ كِتَٰبِيَهۡ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ (ለጓደኞቹ) «እንኩ፤ መጽሐፌን አንብቡ» ይላል፡፡
عربی تفاسیر:
إِنِّي ظَنَنتُ أَنِّي مُلَٰقٍ حِسَابِيَهۡ
«እኔ ምርመራየን የምገናኝ መኾኔን አረጋገጥኩ፤» (ተዘጋጀሁም ይላል)፡፡
عربی تفاسیر:
فَهُوَ فِي عِيشَةٖ رَّاضِيَةٖ
እርሱም በተወደደች ኑሮ ውሰጥ ይኾናል፡፡
عربی تفاسیر:
فِي جَنَّةٍ عَالِيَةٖ
በከፍተኛይቱ ገነት ውስጥ፡፡
عربی تفاسیر:
قُطُوفُهَا دَانِيَةٞ
ፍሬዎችዋ ቅርቦች የኾኑ፡፡
عربی تفاسیر:
كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَآ أَسۡلَفۡتُمۡ فِي ٱلۡأَيَّامِ ٱلۡخَالِيَةِ
በአለፉት ቀናት ውስጥ (በምድረ ዓለም) ባስቀደማችሁት ምክንያት ብሉ፤ ጠጡም፤ (ይባላሉ)፡፡
عربی تفاسیر:
وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِشِمَالِهِۦ فَيَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي لَمۡ أُوتَ كِتَٰبِيَهۡ
መጽሐፉንም በግራው የተሰጠማ «ዋ ጥፋቴ! ምነው መጽሐፌን ባልተሰጠሁ» ይላል፡፡
عربی تفاسیر:
وَلَمۡ أَدۡرِ مَا حِسَابِيَهۡ
«ምርመራየንም ምን እንደኾነ ባላወቅኩ፡፡
عربی تفاسیر:
يَٰلَيۡتَهَا كَانَتِ ٱلۡقَاضِيَةَ
«እርሷ (ሞት ሕይወቴን) ምነው ፈጻሚ በኾነች፡፡
عربی تفاسیر:
مَآ أَغۡنَىٰ عَنِّي مَالِيَهۡۜ
«ገንዘቤ ከእኔ ምንንም አላብቃቃኝ፤ (አልጠቀመኝም)፡፡
عربی تفاسیر:
هَلَكَ عَنِّي سُلۡطَٰنِيَهۡ
«ኀይሌ ከእኔ ላይ ጠፋ» (ይላል)፡፡
عربی تفاسیر:
خُذُوهُ فَغُلُّوهُ
«ያዙት፤ እሰሩትም፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ ٱلۡجَحِيمَ صَلُّوهُ
«ከዚያም በእሳት ውሰጥ አግቡት፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ فِي سِلۡسِلَةٖ ذَرۡعُهَا سَبۡعُونَ ذِرَاعٗا فَٱسۡلُكُوهُ
«ከዚያም ርዝመቷ ሰባ ክንድ በኾነች ሰንሰለት ውስጥ አግቡት፡፡»
عربی تفاسیر:
إِنَّهُۥ كَانَ لَا يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱ ታላቅ በኾነው አላህ አያምንም ነበርና፡፡
عربی تفاسیر:
وَلَا يَحُضُّ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኾችንም በማብላት ላይ አያግባባም ነበርና፡፡
عربی تفاسیر:
فَلَيۡسَ لَهُ ٱلۡيَوۡمَ هَٰهُنَا حَمِيمٞ
ለእርሱም ዛሬ እዚህ ዘመድ የለውም፡፡
عربی تفاسیر:
وَلَا طَعَامٌ إِلَّا مِنۡ غِسۡلِينٖ
ምግብም ከእሳት ሰዎች ቁስል እጣቢ (እዥ) በስተቀር የለውም፡፡
عربی تفاسیر:
لَّا يَأۡكُلُهُۥٓ إِلَّا ٱلۡخَٰطِـُٔونَ
ኀጢኣተኞች እንጅ ሌላ አይበላውም፤ (ይባላል)፡፡
عربی تفاسیر:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَا تُبۡصِرُونَ
በምታዩትም ነገር እምላለሁ፡፡
عربی تفاسیر:
وَمَا لَا تُبۡصِرُونَ
በማታዩትም ነገር፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ
እርሱ (ቁርኣን) የተከበረ መልክተኛ ቃል ነው፡፡
عربی تفاسیر:
وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَاعِرٖۚ قَلِيلٗا مَّا تُؤۡمِنُونَ
እርሱም የባለቅኔ ቃል (ግጥም) አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታምናላችሁ፡፡
عربی تفاسیر:
وَلَا بِقَوۡلِ كَاهِنٖۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ
የጠንቋይም ቃል አይደለም፡፡ ጥቂትን ብቻ ታስታውሳላችሁ፡፡
عربی تفاسیر:
تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
عربی تفاسیر:
وَلَوۡ تَقَوَّلَ عَلَيۡنَا بَعۡضَ ٱلۡأَقَاوِيلِ
በእኛ ላይም ከፊልን ቃላት (ያላልነውን) በቀጠፈ ኖሮ፤
عربی تفاسیر:
لَأَخَذۡنَا مِنۡهُ بِٱلۡيَمِينِ
በቀኝ በያዝነው ነበር፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ لَقَطَعۡنَا مِنۡهُ ٱلۡوَتِينَ
ከዚያም ከእርሱ የልቡን ሥር (የተንጠለጠለበትን ጅማት) በቆረጥን ነበር፡፡
عربی تفاسیر:
فَمَا مِنكُم مِّنۡ أَحَدٍ عَنۡهُ حَٰجِزِينَ
ከእናንተም ውስጥ ከእርሱ ላይ ከልካዮች ምንም አይኖሩም፡፡
عربی تفاسیر:
وَإِنَّهُۥ لَتَذۡكِرَةٞ لِّلۡمُتَّقِينَ
እርሱም (ቁርኣን) ለጥንቁቆቹ መገሠጫ ነው፡፡
عربی تفاسیر:
وَإِنَّا لَنَعۡلَمُ أَنَّ مِنكُم مُّكَذِّبِينَ
እኛም ከእናንተ ውስጥ አስተባባዮች መኖራቸውን በእርግጥ እናውቃለን፡፡
عربی تفاسیر:
وَإِنَّهُۥ لَحَسۡرَةٌ عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በከሓዲዎቹ ላይ ጸጸት ነው፡፡
عربی تفاسیر:
وَإِنَّهُۥ لَحَقُّ ٱلۡيَقِينِ
እርሱም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡
عربی تفاسیر:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
عربی تفاسیر:
 
معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ حاقہ
سورتوں کی لسٹ صفحہ نمبر
 
قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہری ترجمہ - ترجمے کی لسٹ

قرآن کریم کے معانی کا امہری زبان میں ترجمہ: شیخ محمد صادق اور محمد الثانی حبیب نے کیا ہے۔ ترجمہ کی تصحیح مرکز رُواد الترجمہ کی جانب سے کی گئی ہے، ساتھ ہی اظہارِ رائے، تقییم اور مسلسل بہتری کے لیے اصل ترجمہ بھی باقی رکھا گیا ہے ۔

بند کریں