قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہری ترجمہ * - ترجمے کی لسٹ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ نبأ   آیت:

ሱረቱ አን ነበእ

عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
عربی تفاسیر:
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ
ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡
عربی تفاسیر:
ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ
ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡
عربی تفاسیر:
كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
عربی تفاسیر:
ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡
عربی تفاسیر:
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا
ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን?
عربی تفاسیر:
وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا
ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን?
عربی تفاسیر:
وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا
ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡
عربی تفاسیر:
وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا
እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡
عربی تفاسیر:
وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا
ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡
عربی تفاسیر:
وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا
ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡
عربی تفاسیر:
وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا
ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡
عربی تفاسیر:
وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا
አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡
عربی تفاسیر:
وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا
ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡
عربی تفاسیر:
لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا
በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡
عربی تفاسیر:
وَجَنَّٰتٍ أَلۡفَافًا
የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا
የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡
عربی تفاسیر:
يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا
በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡
عربی تفاسیر:
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا
ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡
عربی تفاسیر:
وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا
ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا
ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡
عربی تفاسیر:
لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابٗا
ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡
عربی تفاسیر:
لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا
በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤
عربی تفاسیر:
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرۡدٗا وَلَا شَرَابًا
በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡
عربی تفاسیر:
إِلَّا حَمِيمٗا وَغَسَّاقٗا
ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡
عربی تفاسیر:
جَزَآءٗ وِفَاقًا
ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ حِسَابٗا
እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡
عربی تفاسیر:
وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابٗا
በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡
عربی تفاسیر:
وَكُلَّ شَيۡءٍ أَحۡصَيۡنَٰهُ كِتَٰبٗا
ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡
عربی تفاسیر:
فَذُوقُواْ فَلَن نَّزِيدَكُمۡ إِلَّا عَذَابًا
ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ مَفَازًا
ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡
عربی تفاسیر:
حَدَآئِقَ وَأَعۡنَٰبٗا
አትክልቶችና ወይኖችም፡፡
عربی تفاسیر:
وَكَوَاعِبَ أَتۡرَابٗا
እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡
عربی تفاسیر:
وَكَأۡسٗا دِهَاقٗا
የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡
عربی تفاسیر:
لَّا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا كِذَّٰبٗا
በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡
عربی تفاسیر:
جَزَآءٗ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابٗا
ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡
عربی تفاسیر:
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا ٱلرَّحۡمَٰنِۖ لَا يَمۡلِكُونَ مِنۡهُ خِطَابٗا
የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡
عربی تفاسیر:
يَوۡمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ صَفّٗاۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَقَالَ صَوَابٗا
መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡
عربی تفاسیر:
ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلۡحَقُّۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡
عربی تفاسیر:
إِنَّآ أَنذَرۡنَٰكُمۡ عَذَابٗا قَرِيبٗا يَوۡمَ يَنظُرُ ٱلۡمَرۡءُ مَا قَدَّمَتۡ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلۡكَافِرُ يَٰلَيۡتَنِي كُنتُ تُرَٰبَۢا
እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡
عربی تفاسیر:
 
معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ نبأ
سورتوں کی لسٹ صفحہ نمبر
 
قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - امہری ترجمہ - ترجمے کی لسٹ

قرآن کریم کے معانی کا امہری زبان میں ترجمہ: شیخ محمد صادق اور محمد الثانی حبیب نے کیا ہے۔ ترجمہ کی تصحیح مرکز رُواد الترجمہ کی جانب سے کی گئی ہے، ساتھ ہی اظہارِ رائے، تقییم اور مسلسل بہتری کے لیے اصل ترجمہ بھی باقی رکھا گیا ہے ۔

بند کریں