Übersetzung der Bedeutungen von dem heiligen Quran - الترجمة الأمهرية - زين * - Übersetzungen


Übersetzung der Bedeutungen Surah / Kapitel: Al-Furqân   Vers:

ሱረቱ አል ፉርቃን

تَبَارَكَ ٱلَّذِي نَزَّلَ ٱلۡفُرۡقَانَ عَلَىٰ عَبۡدِهِۦ لِيَكُونَ لِلۡعَٰلَمِينَ نَذِيرًا
1. ያ ፉርቃንን (እውነትን ከውሸት የሚለየውን) ቁርኣን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስፈራሪ ይሆን ዘንድ ያወረደው (አምላክ) ክብሩ ላቀ (ጥራት ተገባው)።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ٱلَّذِي لَهُۥ مُلۡكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَلَمۡ يَتَّخِذۡ وَلَدٗا وَلَمۡ يَكُن لَّهُۥ شَرِيكٞ فِي ٱلۡمُلۡكِ وَخَلَقَ كُلَّ شَيۡءٖ فَقَدَّرَهُۥ تَقۡدِيرٗا
2. አላህ ያ የሰማያትና የምድር ንግስና የእርሱ ብቻ የሆነ፤ ልጅንም ያልያዘ (ልጅም የሌለው)፤ በንግስናዉም ተጋሪ የሌለው፤ ሁሉንም ነገር የፈጠረና በትክክልም (በስርአት) የመጠነው አምላክ ነው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ ءَالِهَةٗ لَّا يَخۡلُقُونَ شَيۡـٔٗا وَهُمۡ يُخۡلَقُونَ وَلَا يَمۡلِكُونَ لِأَنفُسِهِمۡ ضَرّٗا وَلَا نَفۡعٗا وَلَا يَمۡلِكُونَ مَوۡتٗا وَلَا حَيَوٰةٗ وَلَا نُشُورٗا
3. ከሓዲያን ከእርሱ ከአላህ ሌላ ምንንም የማይፈጥሩንና እነርሱ ራሳቸው የሚፈጠሩ፤ ለነፍሶቻቸዉም (ከራሳቸው ላይ) ጉዳትን መከላከልም ሆነ ለራሳቸው ጥቅምን ማምጣት (ማስከበር) የማይችሉ፤ ለሞት ማብቃትም ሆነ ህይወትን መለገስና ከሞት መቀስቀስንም የማይችሉን አማልክትን አምላክ አድርገው ያዙ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّآ إِفۡكٌ ٱفۡتَرَىٰهُ وَأَعَانَهُۥ عَلَيۡهِ قَوۡمٌ ءَاخَرُونَۖ فَقَدۡ جَآءُو ظُلۡمٗا وَزُورٗا
4. እነዚያ በአላህ የካዱ ሰዎች «ይህ ቁርኣን እርሱ (ሙሐመድ) በራሱ የቀጠፈውና በእርሱም ላይ ሌሎች ህዝቦች ያገዙት ውሸት እንጂ ሌላ አይደለም።» አሉ። በእርግጥም በደልንና እብለትን ፈጸሙ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالُوٓاْ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ ٱكۡتَتَبَهَا فَهِيَ تُمۡلَىٰ عَلَيۡهِ بُكۡرَةٗ وَأَصِيلٗا
5. «እነዚህ የመጀመሪያ ሰዎች ተረቶች (አፈታሪክ) ናቸው። አስጽፎታል፤ እናም በእርሱ ላይ ጧትና ማታ ትነበብለታለች።» አሉ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قُلۡ أَنزَلَهُ ٱلَّذِي يَعۡلَمُ ٱلسِّرَّ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ إِنَّهُۥ كَانَ غَفُورٗا رَّحِيمٗا
6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው:: እርሱ መሓሪና አዛኝ ነውና።» በላቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالُواْ مَالِ هَٰذَا ٱلرَّسُولِ يَأۡكُلُ ٱلطَّعَامَ وَيَمۡشِي فِي ٱلۡأَسۡوَاقِ لَوۡلَآ أُنزِلَ إِلَيۡهِ مَلَكٞ فَيَكُونَ مَعَهُۥ نَذِيرًا
7. አሉም: «ይህ መልዕክተኛ ምን አይነት መልዕክተኛ ነው? ምግብ የሚመገብ ወደ ገበያ የሚመላለስ፤ ከእርሱ ጋር አስፈራሪ ይሆን ዘንድ ወደ እርሱ መልአክ (በገሃድ) አይወረድም ኖሯልን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَوۡ يُلۡقَىٰٓ إِلَيۡهِ كَنزٌ أَوۡ تَكُونُ لَهُۥ جَنَّةٞ يَأۡكُلُ مِنۡهَاۚ وَقَالَ ٱلظَّٰلِمُونَ إِن تَتَّبِعُونَ إِلَّا رَجُلٗا مَّسۡحُورًا
8. «ወይም ወደ እርሱ ድልብ አይሰጠዉምን? ወይም ከእርሷ የሚበላባት አትክልት ለእርሱ አትኖረዉምን?» አሉ። «በዳዮችም ላመኑት የተደገመበትን ሰው እንጂ ሌላን አትከተሉም።» አሉ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ٱنظُرۡ كَيۡفَ ضَرَبُواْ لَكَ ٱلۡأَمۡثَٰلَ فَضَلُّواْ فَلَا يَسۡتَطِيعُونَ سَبِيلٗا
9.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ላንተ ምሳሌዎችን እንዴት እንዳደረጉልህና ከዚያም እንዴት እንደ ተሳሳቱ ተመልከት:: ወደ እውነት ለመድረስ መንገድንም አይችሉም::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
تَبَارَكَ ٱلَّذِيٓ إِن شَآءَ جَعَلَ لَكَ خَيۡرٗا مِّن ذَٰلِكَ جَنَّٰتٖ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ وَيَجۡعَل لَّكَ قُصُورَۢا
10. ያ ቢሻ ከዚህ ካሉት የተሻለን ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው አትክልት ስፍራዎችን ላንተ የሚያደርግልህ ህንጻ ቤቶችንም የሚያደርግልህ የሆነው ጌታ ችሮታው በዛ:: (ክብሩ ላቀ)
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
بَلۡ كَذَّبُواْ بِٱلسَّاعَةِۖ وَأَعۡتَدۡنَا لِمَن كَذَّبَ بِٱلسَّاعَةِ سَعِيرًا
11. ይልቁንም እነርሱ በትንሳኤ አስተባበሉ:: በትንሳኤ ላስተባበለም ሁሉ አቃጣይ እሳት አዘጋጅተናል::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِذَا رَأَتۡهُم مِّن مَّكَانِۭ بَعِيدٖ سَمِعُواْ لَهَا تَغَيُّظٗا وَزَفِيرٗا
12. ከሩቅ ስፍራ ባየቻቸው ጊዜ የእርሷን የቁጭት መገንፈልንና ማናፋትን ይሰማሉ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِذَآ أُلۡقُواْ مِنۡهَا مَكَانٗا ضَيِّقٗا مُّقَرَّنِينَ دَعَوۡاْ هُنَالِكَ ثُبُورٗا
13. ከጓደኞቻቸው ጋር (ከሰይጣኖቻቸው ጋር) በአንድ የታሰሩ ሆነዉም ከእርሷ በጠባብ ስፍራ በተጣሉ ጊዜ በዚያ ስፍራ ጥፋትን ይጠራሉ:: (ዋ ጥፋታችን! ይላሉ)።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَّا تَدۡعُواْ ٱلۡيَوۡمَ ثُبُورٗا وَٰحِدٗا وَٱدۡعُواْ ثُبُورٗا كَثِيرٗا
14. ዛሬማ አንድን ጥፋት ብቻ አትጥሩ:: ይልቁንም ብዙን ጥፋት ጥሩ ይባላሉ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قُلۡ أَذَٰلِكَ خَيۡرٌ أَمۡ جَنَّةُ ٱلۡخُلۡدِ ٱلَّتِي وُعِدَ ٱلۡمُتَّقُونَۚ كَانَتۡ لَهُمۡ جَزَآءٗ وَمَصِيرٗا
15. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) (እንዲህ) በላቸው: «ይህ የተሻለ ነውን? ወይስ ጥንቁቆቹ ተስፋ የተሰጡት የዘልዓለሟ ገነት?» ገነት ለእነርሱ ምንዳና መመለሻ ሆነች።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَّهُمۡ فِيهَا مَا يَشَآءُونَ خَٰلِدِينَۚ كَانَ عَلَىٰ رَبِّكَ وَعۡدٗا مَّسۡـُٔولٗا
16. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ለእነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ሆነው የሚፈልጉት ሁሉ አለላቸው:: ይህ ተስፋ ከጌታህ ሊለመን የሚገባው ተስፋ ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَيَوۡمَ يَحۡشُرُهُمۡ وَمَا يَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ فَيَقُولُ ءَأَنتُمۡ أَضۡلَلۡتُمۡ عِبَادِي هَٰٓؤُلَآءِ أَمۡ هُمۡ ضَلُّواْ ٱلسَّبِيلَ
17. እነርሱንና ከአላህ ሌላ የሚገዟቸውን የሚሰበስብበትንና «እናንተ እነዚህን ባሮቼን አሳሳታችሁን? ወይስ እነርሱው እራሳቸው መንገድን ሳቱ?» የሚልበትን ቀን አስታውስ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالُواْ سُبۡحَٰنَكَ مَا كَانَ يَنۢبَغِي لَنَآ أَن نَّتَّخِذَ مِن دُونِكَ مِنۡ أَوۡلِيَآءَ وَلَٰكِن مَّتَّعۡتَهُمۡ وَءَابَآءَهُمۡ حَتَّىٰ نَسُواْ ٱلذِّكۡرَ وَكَانُواْ قَوۡمَۢا بُورٗا
18. (ተመላኪዎቹም): «አላህ ሆይ! ጥራት ይገባህ:: ከአንተ ሌላ ረዳቶችን ልንይዝ አይገባንም:: ግን እነርሱንም ሆነ አባቶቻቸውን መገንዘብን እስከ ተውና ጠፊ ህዝቦችም እስከሚሆኑ ድረስ አጣቀምካቸው።» ይላሉ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَقَدۡ كَذَّبُوكُم بِمَا تَقُولُونَ فَمَا تَسۡتَطِيعُونَ صَرۡفٗا وَلَا نَصۡرٗاۚ وَمَن يَظۡلِم مِّنكُمۡ نُذِقۡهُ عَذَابٗا كَبِيرٗا
19. በምትሉትም አማልክቶቻችሁ አስዋሹዋችሁ:: ቅጣቴን መገፍተርንም ሆነ እራሳችሁን መርዳት አትችሉም:: ከናንተም የሚበድልን ሰው ታላቅን ቅጣት እናቀምሰዋለን:: (ይባላሉ።)
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَمَآ أَرۡسَلۡنَا قَبۡلَكَ مِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ إِلَّآ إِنَّهُمۡ لَيَأۡكُلُونَ ٱلطَّعَامَ وَيَمۡشُونَ فِي ٱلۡأَسۡوَاقِۗ وَجَعَلۡنَا بَعۡضَكُمۡ لِبَعۡضٖ فِتۡنَةً أَتَصۡبِرُونَۗ وَكَانَ رَبُّكَ بَصِيرٗا
20. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ካንተ በፊትም ከመልዕክተኞች እነርሱ በእርግጥ ምግብን የሚበሉ በገበያዎችም የሚሄዱ ሆነው እንጂ አላክንም:: ከፊላችሁንም ለከፊሉ ፈተና አድርገናል:: ትታገሳላችሁን? ጌታህም ተመልካች ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
۞ وَقَالَ ٱلَّذِينَ لَا يَرۡجُونَ لِقَآءَنَا لَوۡلَآ أُنزِلَ عَلَيۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ أَوۡ نَرَىٰ رَبَّنَاۗ لَقَدِ ٱسۡتَكۡبَرُواْ فِيٓ أَنفُسِهِمۡ وَعَتَوۡ عُتُوّٗا كَبِيرٗا
21. እነዚያ መገናኘታችንን የማይጠብቁ ሰዎች «በእኛ ላይ ለምን መላእክት አልወረደም ወይም ጌታችንን ለምን አናይም?» አሉ። በነፍሶቻቸው ውስጥ በእርግጥ ኮሩ። ታላቅንም አመጽ አመጹ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
يَوۡمَ يَرَوۡنَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ لَا بُشۡرَىٰ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُجۡرِمِينَ وَيَقُولُونَ حِجۡرٗا مَّحۡجُورٗا
22. መላዕክትን በሚያዩበት ቀን በዚያ ጊዜ ለአመጸኞች የምስራች የላቸዉም። (መላዕክቱም) «የተከለከለ ክልክል» ይላሉ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَدِمۡنَآ إِلَىٰ مَا عَمِلُواْ مِنۡ عَمَلٖ فَجَعَلۡنَٰهُ هَبَآءٗ مَّنثُورًا
23. ወደ ሰሩት ስራም እናስባለን:: ከዚያም እንደ ተበተነ ትቢያ እናደርገዋለን::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَصۡحَٰبُ ٱلۡجَنَّةِ يَوۡمَئِذٍ خَيۡرٞ مُّسۡتَقَرّٗا وَأَحۡسَنُ مَقِيلٗا
24. የገነት ሰዎች በዚያ ቀን በመርጊያ የተሻሉ በማረፊያም በጣም ያማሩ ናቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَيَوۡمَ تَشَقَّقُ ٱلسَّمَآءُ بِٱلۡغَمَٰمِ وَنُزِّلَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ تَنزِيلًا
25. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰማይ በደመና የምትቀደድበትንና መላእክትም መውረድን የሚወርዱበትን ቀን አስታውስ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ٱلۡمُلۡكُ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡحَقُّ لِلرَّحۡمَٰنِۚ وَكَانَ يَوۡمًا عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ عَسِيرٗا
26. እውነተኛው ንግስና በዚያ ቀን ለአር-ረህማን ብቻ ነው:: በከሓዲያን ላይ አስቸጋሪ ቀን ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَيَوۡمَ يَعَضُّ ٱلظَّالِمُ عَلَىٰ يَدَيۡهِ يَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي ٱتَّخَذۡتُ مَعَ ٱلرَّسُولِ سَبِيلٗا
27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በዳይም «ዋ ምኞቴ! ከመልዕክተኛው ጋር ቀጥተኛን መንገድ ምነው ይዤ በሆነ፤ እያለ (በጸጸት) ሁለት እጆችን የሚነክስበትን ቀን (አስታውስ)::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
يَٰوَيۡلَتَىٰ لَيۡتَنِي لَمۡ أَتَّخِذۡ فُلَانًا خَلِيلٗا
28. «ዋ ጥፋቴ! እገሌን በወዳጅነት ባልያዝኩ ኖሮ እመኛለሁ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَّقَدۡ أَضَلَّنِي عَنِ ٱلذِّكۡرِ بَعۡدَ إِذۡ جَآءَنِيۗ وَكَانَ ٱلشَّيۡطَٰنُ لِلۡإِنسَٰنِ خَذُولٗا
29. (የእምነት ቃል የሆነው) «ቁርኣን ከመጣልኝ በኋላ ከማስታወስ በእርግጥ አሳሳተኝ።» ይላል:: ሰይጣንም ለሰው አጋላጭ ነውና።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالَ ٱلرَّسُولُ يَٰرَبِّ إِنَّ قَوۡمِي ٱتَّخَذُواْ هَٰذَا ٱلۡقُرۡءَانَ مَهۡجُورٗا
30. መልዕክተኛዉም (ሙሐመድ) «ጌታዬ ሆይ! ህዝቦቼ ይህንን ቁርኣን የተተወ ነገር አደረጉት።» አለ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَكَذَٰلِكَ جَعَلۡنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوّٗا مِّنَ ٱلۡمُجۡرِمِينَۗ وَكَفَىٰ بِرَبِّكَ هَادِيٗا وَنَصِيرٗا
31. ልክ እንደዚሁም ለነብያቱ ሁሉ ከአመጸኞች የሆነ ጠላትን አድርገናል:: መሪነትና ረዳትነት በጌታህ በቃ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لَوۡلَا نُزِّلَ عَلَيۡهِ ٱلۡقُرۡءَانُ جُمۡلَةٗ وَٰحِدَةٗۚ كَذَٰلِكَ لِنُثَبِّتَ بِهِۦ فُؤَادَكَۖ وَرَتَّلۡنَٰهُ تَرۡتِيلٗا
32. እነዚያ በአላህ የካዱ ሰዎችም «ቁርኣንን በእርሱ ላይ ለምን በጠቅላላ በአንድ ጊዜ አልተወረደለትም።» አሉ። ልክ እንደዚሁ በእርሱ ልብህን ልናረጋ (ከፋፍለን በተለያየ አወረድነው):: ቀስ በቀስ መለያየትንም ለየነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَا يَأۡتُونَكَ بِمَثَلٍ إِلَّا جِئۡنَٰكَ بِٱلۡحَقِّ وَأَحۡسَنَ تَفۡسِيرًا
33. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በየትኛዉም ጥያቄ አይመጡብህም እውነተኛውን መልስና መልካም ፍቹንም የምናመጣልህ ብንሆን እንጅ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ٱلَّذِينَ يُحۡشَرُونَ عَلَىٰ وُجُوهِهِمۡ إِلَىٰ جَهَنَّمَ أُوْلَٰٓئِكَ شَرّٞ مَّكَانٗا وَأَضَلُّ سَبِيلٗا
34. እነዚያ በፊቶቻቻው ላይ እየተጎተቱ ወደ ገሀነም የሚሰበሰቡት እነዚያ ስፍራቸው የከፋ መንገዳቸዉም የጠመመ ናቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ ءَاتَيۡنَا مُوسَى ٱلۡكِتَٰبَ وَجَعَلۡنَا مَعَهُۥٓ أَخَاهُ هَٰرُونَ وَزِيرٗا
35. በእርግጥም ለሙሳ መጽሐፍን ሰጠነው:: ከእርሱም ጋር ወንድሙን ሃሩንን ረዳት አደረግንለት::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَقُلۡنَا ٱذۡهَبَآ إِلَى ٱلۡقَوۡمِ ٱلَّذِينَ كَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا فَدَمَّرۡنَٰهُمۡ تَدۡمِيرٗا
36. «ወደ እነዚያም በተዓምራታችን ወደ አስተባበሉት ህዝቦች ሂዱ።» አልናቸው። (አስዋሿቸዉም) ማጥፋትንም አጠፋናቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَوۡمَ نُوحٖ لَّمَّا كَذَّبُواْ ٱلرُّسُلَ أَغۡرَقۡنَٰهُمۡ وَجَعَلۡنَٰهُمۡ لِلنَّاسِ ءَايَةٗۖ وَأَعۡتَدۡنَا لِلظَّٰلِمِينَ عَذَابًا أَلِيمٗا
37. የኑህን ሰዎችም መልዕክተኞችን ባስተባበሉ ጊዜ አሰመጥናቸው:: ለሰዎችም መገሰጫ አደረግናቸው፤ ለበደለኞችም አሳማሚን ቅጣት አዘጋጅተናል::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَعَادٗا وَثَمُودَاْ وَأَصۡحَٰبَ ٱلرَّسِّ وَقُرُونَۢا بَيۡنَ ذَٰلِكَ كَثِيرٗا
38. ዓድንም፤ሰሙድንም፤ የረስ ሰዎችንና በዚህ መካከል የነበሩትንም ብዙ የክፍለ ዘመናት ህዝቦችንም አጠፋን።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَكُلّٗا ضَرَبۡنَا لَهُ ٱلۡأَمۡثَٰلَۖ وَكُلّٗا تَبَّرۡنَا تَتۡبِيرٗا
39. ሁሉንም (ገሠጽን):: ለእነርሱ ምሳሌዎችን ገለጽን:: ሁሉንም ማጥፋትን አጠፋናቸዉም::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ أَتَوۡاْ عَلَى ٱلۡقَرۡيَةِ ٱلَّتِيٓ أُمۡطِرَتۡ مَطَرَ ٱلسَّوۡءِۚ أَفَلَمۡ يَكُونُواْ يَرَوۡنَهَاۚ بَلۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ نُشُورٗا
40. በዚያችም ክፉ ዝናብን በተዘነበችው ከተማ ላይ (የመካ ከሓዲያን) በእርግጥ መጥተዋል:: የሚያዩዋት አልነበሩምን? በእውነቱ መቀስቀስን የማይፈሩ ነበሩ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِذَا رَأَوۡكَ إِن يَتَّخِذُونَكَ إِلَّا هُزُوًا أَهَٰذَا ٱلَّذِي بَعَثَ ٱللَّهُ رَسُولًا
41. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ባዩህም ጊዜ (እንዲህ) እያሉ መሳለቂያ እንጅ ሌላ አያደርጉህም: «ያ አላህ መልዕክተኛ እድርጎ የላከው ይህ ነውን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِن كَادَ لَيُضِلُّنَا عَنۡ ءَالِهَتِنَا لَوۡلَآ أَن صَبَرۡنَا عَلَيۡهَاۚ وَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ حِينَ يَرَوۡنَ ٱلۡعَذَابَ مَنۡ أَضَلُّ سَبِيلًا
42. «እነሆ በእርሷ ላይ መታገሳችን (ጽናታችን) ባልነበረ ኖሮ ከአማልክቶቻችን ሊያሳስተን ቀርቦ ነበር።» ሲሉም ይሳለቃሉ:: ወደ ፊትም ቅጣትን በሚያዩ ጊዜ መንገድን በጣም የተሳሳተው ማን እንደ ሆነ በእርግጥ ያኔ ያውቃሉ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَرَءَيۡتَ مَنِ ٱتَّخَذَ إِلَٰهَهُۥ هَوَىٰهُ أَفَأَنتَ تَكُونُ عَلَيۡهِ وَكِيلًا
43. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ፍላጎቱን አምላኩ አድርጎ የያዘን ሰው አየህን? አንተም በእርሱ ላይ ጠባቂ ትሆናለህን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَمۡ تَحۡسَبُ أَنَّ أَكۡثَرَهُمۡ يَسۡمَعُونَ أَوۡ يَعۡقِلُونَۚ إِنۡ هُمۡ إِلَّا كَٱلۡأَنۡعَٰمِ بَلۡ هُمۡ أَضَلُّ سَبِيلًا
44. ይልቁንም አብዛኛዎቻቸው የሚሰሙ ወይም የሚያውቁ መሆናቸውን ታስባለህን? እነርሱ እንደ እንስሳዎች እንጂ ሌላ አይደሉም:: ከቶውንም እነርሱ ከእንስሳዎች በባሰ መንገድን የተሳሳቱ ናቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَلَمۡ تَرَ إِلَىٰ رَبِّكَ كَيۡفَ مَدَّ ٱلظِّلَّ وَلَوۡ شَآءَ لَجَعَلَهُۥ سَاكِنٗا ثُمَّ جَعَلۡنَا ٱلشَّمۡسَ عَلَيۡهِ دَلِيلٗا
45. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጌታህ ጥላን እንዴት እንደ ዘረጋ አላየህምን? በሻም ኖሮ የረጋ ባደረገው ነበር:: ከዚያ ጸሐይን በእርሱ ላይ ምልክት አደረግን።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ثُمَّ قَبَضۡنَٰهُ إِلَيۡنَا قَبۡضٗا يَسِيرٗا
46. ከዚያም ቀስ በቀስ ወደ እኛ ሰበሰብነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَهُوَ ٱلَّذِي جَعَلَ لَكُمُ ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا وَٱلنَّوۡمَ سُبَاتٗا وَجَعَلَ ٱلنَّهَارَ نُشُورٗا
47. እርሱም ያ ለእናንተ ሌሊትን ልብስ እንቅልፍንም ማረፊያ ያደረገ:: ቀንንም መተኛ ያደረገላችሁ አምላክ ነው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَهُوَ ٱلَّذِيٓ أَرۡسَلَ ٱلرِّيَٰحَ بُشۡرَۢا بَيۡنَ يَدَيۡ رَحۡمَتِهِۦۚ وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلسَّمَآءِ مَآءٗ طَهُورٗا
48. እርሱ (አላህ) ያ ንፋሶችን አብሳሪዎች ሲሆኑ ከዝናቡ በስተፊት የላከ ነው:: ከሰማይም አጥሪ ውሃን አወረድን::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لِّنُحۡـِۧيَ بِهِۦ بَلۡدَةٗ مَّيۡتٗا وَنُسۡقِيَهُۥ مِمَّا خَلَقۡنَآ أَنۡعَٰمٗا وَأَنَاسِيَّ كَثِيرٗا
49. በእርሱ የሞተችን ሀገር ህያው ልናደርግበት፤ ከፈጠርነዉም ፍጡር እንስሳዎችንና ብዙ ሰዎችንም ልናጠጣበት አወረድነው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ صَرَّفۡنَٰهُ بَيۡنَهُمۡ لِيَذَّكَّرُواْ فَأَبَىٰٓ أَكۡثَرُ ٱلنَّاسِ إِلَّا كُفُورٗا
50. ጸጋችንን ይገነዘቡም ዘንድ በመካከላቸው ከፋፈልነው አበላለጥነዉም:: ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች ክህደትን እንጂ እንቢ አሉ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَوۡ شِئۡنَا لَبَعَثۡنَا فِي كُلِّ قَرۡيَةٖ نَّذِيرٗا
51. በሻንም ኖሮ በየከተማይቱ አስፈራሪን በላክን ነበር::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَلَا تُطِعِ ٱلۡكَٰفِرِينَ وَجَٰهِدۡهُم بِهِۦ جِهَادٗا كَبِيرٗا
52. ከሓዲያንን አትታዘዛቸው:: በእርሱም (በቁርኣን) ታላቅን ትግል ታገላቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
۞ وَهُوَ ٱلَّذِي مَرَجَ ٱلۡبَحۡرَيۡنِ هَٰذَا عَذۡبٞ فُرَاتٞ وَهَٰذَا مِلۡحٌ أُجَاجٞ وَجَعَلَ بَيۡنَهُمَا بَرۡزَخٗا وَحِجۡرٗا مَّحۡجُورٗا
53. እርሱ ያ ሁለትን ባህሮች አጎራብቶ የለቀቀ ነው:: አንዱ ጥም የሚቆርጥና ጣፋጭ ነው:: ሌላኛው ደግሞ የሚመረግግ ጨው ነው:: በመካከላቸዉም ከመቀላቀል መለያንና የተከለለን ክልል ያደረገ ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَهُوَ ٱلَّذِي خَلَقَ مِنَ ٱلۡمَآءِ بَشَرٗا فَجَعَلَهُۥ نَسَبٗا وَصِهۡرٗاۗ وَكَانَ رَبُّكَ قَدِيرٗا
54. እርሱም ያ ከውሃ ሰውን የፈጠረ የዝምድናና የአማችም ባለቤት ያደረገው ነው:: ጌታህም ሁሉን ነገር ቻይ ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَيَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَنفَعُهُمۡ وَلَا يَضُرُّهُمۡۗ وَكَانَ ٱلۡكَافِرُ عَلَىٰ رَبِّهِۦ ظَهِيرٗا
55. ከአላህ ሌላ የማይጠቅማቸውንና የማይጎዳቸውን አካል ይገዛሉ:: ከሓዲ በጌታው ላይ (በማመጽ ለሰይጣን) ረዳት ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَمَآ أَرۡسَلۡنَٰكَ إِلَّا مُبَشِّرٗا وَنَذِيرٗا
56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አብሳሪና አስፈራሪ አድርገን እንጂ አላክንህም::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قُلۡ مَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍ إِلَّا مَن شَآءَ أَن يَتَّخِذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ سَبِيلٗا
57. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «በእርሱ ላይ ዋጋን በፍጹም አልጠይቃችሁም። ወደ ጌታው መልካም መንገድን ለመያዝ የሻ ሰው ይስራ።» በላቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱلۡحَيِّ ٱلَّذِي لَا يَمُوتُ وَسَبِّحۡ بِحَمۡدِهِۦۚ وَكَفَىٰ بِهِۦ بِذُنُوبِ عِبَادِهِۦ خَبِيرًا
58. በዚያም በማይሞተው ህያው አምላክ ላይ ተመካ፤ ከማመስገንም ጋር አጥራው:: የባሮቹን ኃጢአቶች ውስጥ በማወቅ በእርሱ በቃ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ٱلَّذِي خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَمَا بَيۡنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٖ ثُمَّ ٱسۡتَوَىٰ عَلَى ٱلۡعَرۡشِۖ ٱلرَّحۡمَٰنُ فَسۡـَٔلۡ بِهِۦ خَبِيرٗا
59. ያ ሰማያትንና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ ብቻ የፈጠረ ነው። ከዚያም በዐርሹ ላይ ከፍ አለ:: አር-ረህማን ነው:: ከእርሱም አዋቂን ጠይቅ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱسۡجُدُواْۤ لِلرَّحۡمَٰنِ قَالُواْ وَمَا ٱلرَّحۡمَٰنُ أَنَسۡجُدُ لِمَا تَأۡمُرُنَا وَزَادَهُمۡ نُفُورٗا۩
60. ለእነርሱም «ለአር-ረህማን ስገዱ።» በተባሉ ጊዜ «አር-ረህማን ማን ነው? ለምታዘንና ለማናውቀው እንሰግዳለን እንዴ?» ይላሉ። ይህም መራቅን ጨመራቸው። {1}
{1} እዚህ የንባብ ሱጁድ (ሱጁዱ ትላወህ) ይደረጋል።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
تَبَارَكَ ٱلَّذِي جَعَلَ فِي ٱلسَّمَآءِ بُرُوجٗا وَجَعَلَ فِيهَا سِرَٰجٗا وَقَمَرٗا مُّنِيرٗا
61. ያ በሰማይ ቡሩጆችን ያደረገና በእርሷም አንጸባራቂን ጸሐይ አብሪ ጨረቃንም የፈጠረ ጌታ ክብሩ በጣም ላቀ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَهُوَ ٱلَّذِي جَعَلَ ٱلَّيۡلَ وَٱلنَّهَارَ خِلۡفَةٗ لِّمَنۡ أَرَادَ أَن يَذَّكَّرَ أَوۡ أَرَادَ شُكُورٗا
62. እርሱም ያ ያመለጠውን ስራ ማስታወስን ለሚፈልግ ወይም ማመስገንን ለሚፈልግ ሌሊትንና ቀንን ተተካኪ ያደረገ ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَعِبَادُ ٱلرَّحۡمَٰنِ ٱلَّذِينَ يَمۡشُونَ عَلَى ٱلۡأَرۡضِ هَوۡنٗا وَإِذَا خَاطَبَهُمُ ٱلۡجَٰهِلُونَ قَالُواْ سَلَٰمٗا
63. የአር-ረህማን ባሮች እነዚያ በምድር ላይ በዝግታ የሚሄዱት፤ ባለጌዎችም (በክፉ) ባነጋገሯቸው ጊዜ ሰላም የሚሉት ናቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ يَبِيتُونَ لِرَبِّهِمۡ سُجَّدٗا وَقِيَٰمٗا
64. እነዚያም ለጌታቸው በግንባራቸው ተደፊዎችና ቋሚዎች (ሰጋጆች) ሆነው የሚያድሩት ናቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ يَقُولُونَ رَبَّنَا ٱصۡرِفۡ عَنَّا عَذَابَ جَهَنَّمَۖ إِنَّ عَذَابَهَا كَانَ غَرَامًا
65. እነዚያም (እንዲህ) የሚሉት ናቸው: «ጌታችን ሆይ! የገሀነምን ቅጣት ከእኛ ላይ መልስልን ቅጣቷ የማይለይለቅ ነውና።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهَا سَآءَتۡ مُسۡتَقَرّٗا وَمُقَامٗا
66. «እርሷ መርጊያና መቀመጫ ለመሆን ከፋች!» የሚሉት ናቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ إِذَآ أَنفَقُواْ لَمۡ يُسۡرِفُواْ وَلَمۡ يَقۡتُرُواْ وَكَانَ بَيۡنَ ذَٰلِكَ قَوَامٗا
67. እነዚያም በለገሱ ጊዜ የማያባክኑት የማይቆጥቡትም ናቸው:: በዚህም መካከል ልግስናቸው ትክክለኛ የሆነ ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ لَا يَدۡعُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ وَلَا يَقۡتُلُونَ ٱلنَّفۡسَ ٱلَّتِي حَرَّمَ ٱللَّهُ إِلَّا بِٱلۡحَقِّ وَلَا يَزۡنُونَۚ وَمَن يَفۡعَلۡ ذَٰلِكَ يَلۡقَ أَثَامٗا
68. እነዚያም ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማይገዙት፤ ያችንም አላህ እርም ያደርጋትን ነፍስ ያለ ህግ የማይገድሉ እና የማያመነዝሩት ናቸው:: ይህንን የሚፈጽም ሰው ወንጀለኛ ይሆናል::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
يُضَٰعَفۡ لَهُ ٱلۡعَذَابُ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ وَيَخۡلُدۡ فِيهِۦ مُهَانًا
69. በትንሳኤ ቀን ቅጣት ይደራረብበታል:: በእርሱም ውስጥ የተዋረደ ሆኖ ዘልአለሙን ይኖራል::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا مَن تَابَ وَءَامَنَ وَعَمِلَ عَمَلٗا صَٰلِحٗا فَأُوْلَٰٓئِكَ يُبَدِّلُ ٱللَّهُ سَيِّـَٔاتِهِمۡ حَسَنَٰتٖۗ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورٗا رَّحِيمٗا
70. ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም የሰራ ሰው ብቻ ሲቀር እነዚያም አላህ መጥፎ ስራዎቻቸውን በመልካም ስራዎች ይለውጣል:: አላህም እጅግ መሓሪና አዛኝ ነው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَمَن تَابَ وَعَمِلَ صَٰلِحٗا فَإِنَّهُۥ يَتُوبُ إِلَى ٱللَّهِ مَتَابٗا
71. ተጸጽቶ የተመለሰና መልካምን ተግባር የሰራ እርሱ በአላህ ዘንድ የተወደደን መመለስ ወደ አላህ ይመለሳል::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ لَا يَشۡهَدُونَ ٱلزُّورَ وَإِذَا مَرُّواْ بِٱللَّغۡوِ مَرُّواْ كِرَامٗا
72. እነዚያ በሐሰት የማይጣዱ፤ በውድቅ ቃል (ተናጋሪ) አጠገብም ባለፉ ጊዜ የተከበሩ ሆነው የሚያልፉ ናቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ إِذَا ذُكِّرُواْ بِـَٔايَٰتِ رَبِّهِمۡ لَمۡ يَخِرُّواْ عَلَيۡهَا صُمّٗا وَعُمۡيَانٗا
73. እነዚያም በጌታቸው አናቅጽ በተገሠጹ ጊዜ (የተረዱ ተቀባዮች ሆነው እንጂ) ደንቆሮዎችና እውሮች ሆነው በእርሷ ላይ የማይደፉት ናቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلَّذِينَ يَقُولُونَ رَبَّنَا هَبۡ لَنَا مِنۡ أَزۡوَٰجِنَا وَذُرِّيَّٰتِنَا قُرَّةَ أَعۡيُنٖ وَٱجۡعَلۡنَا لِلۡمُتَّقِينَ إِمَامًا
74. እነዚያ «ጌታችን ሆይ! ከሚስቶቻችንና ከዘሮቻችን ለዓይኖች መርጊያን ለእኛ ስጠን፤ አላህን ለሚፈሩትም መሪ አድርገን።» የሚሉ ናቸው::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أُوْلَٰٓئِكَ يُجۡزَوۡنَ ٱلۡغُرۡفَةَ بِمَا صَبَرُواْ وَيُلَقَّوۡنَ فِيهَا تَحِيَّةٗ وَسَلَٰمًا
75. እነዚያ በመታገሳቸው የገነትን ሰገነቶች ይመነዳሉ:: በእርሷም ውስጥ ውዳሴንና ሰላምታን ይሰጣሉ::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
خَٰلِدِينَ فِيهَاۚ حَسُنَتۡ مُسۡتَقَرّٗا وَمُقَامٗا
76. በእርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ሆነው (ይሰጣሉ):: መርጊያና መኖሪያይቱ ገነት አማረች::
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قُلۡ مَا يَعۡبَؤُاْ بِكُمۡ رَبِّي لَوۡلَا دُعَآؤُكُمۡۖ فَقَدۡ كَذَّبۡتُمۡ فَسَوۡفَ يَكُونُ لِزَامَۢا
77. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ) «ጸሎታችሁ ባልነበረ ኖሮ ጌታዬ እናንተን ከምንም አይቆጥራችሁም ነበር:: አስተባበላችሁ:: እናም ወደ ፊት ቅጣት ያዣችሁ ይሆናል።» በላቸው።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
 
Übersetzung der Bedeutungen Surah / Kapitel: Al-Furqân
Suren/ Kapiteln Liste Nummer der Seite
 
Übersetzung der Bedeutungen von dem heiligen Quran - الترجمة الأمهرية - زين - Übersetzungen

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

Schließen