Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic * - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Al'rahman   Aya:

ሱረቱ አር ረሕማን

ٱلرَّحۡمَٰنُ
አል-ረሕማን፤
Tafsiran larabci:
عَلَّمَ ٱلۡقُرۡءَانَ
ቁርኣንን አስተማረ፡፡
Tafsiran larabci:
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ
ሰውን ፈጠረ፡፡
Tafsiran larabci:
عَلَّمَهُ ٱلۡبَيَانَ
መናገርን አስተማረው፡፡
Tafsiran larabci:
ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ بِحُسۡبَانٖ
ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
وَٱلنَّجۡمُ وَٱلشَّجَرُ يَسۡجُدَانِ
ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
Tafsiran larabci:
وَٱلسَّمَآءَ رَفَعَهَا وَوَضَعَ ٱلۡمِيزَانَ
ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
Tafsiran larabci:
أَلَّا تَطۡغَوۡاْ فِي ٱلۡمِيزَانِ
በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَقِيمُواْ ٱلۡوَزۡنَ بِٱلۡقِسۡطِ وَلَا تُخۡسِرُواْ ٱلۡمِيزَانَ
መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
Tafsiran larabci:
وَٱلۡأَرۡضَ وَضَعَهَا لِلۡأَنَامِ
ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
Tafsiran larabci:
فِيهَا فَٰكِهَةٞ وَٱلنَّخۡلُ ذَاتُ ٱلۡأَكۡمَامِ
በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
Tafsiran larabci:
وَٱلۡحَبُّ ذُو ٱلۡعَصۡفِ وَٱلرَّيۡحَانُ
የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِن صَلۡصَٰلٖ كَٱلۡفَخَّارِ
ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
Tafsiran larabci:
وَخَلَقَ ٱلۡجَآنَّ مِن مَّارِجٖ مِّن نَّارٖ
ጃንንም ከእሳት ከኾነ ነበልባል ፈጠረው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
رَبُّ ٱلۡمَشۡرِقَيۡنِ وَرَبُّ ٱلۡمَغۡرِبَيۡنِ
የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
مَرَجَ ٱلۡبَحۡرَيۡنِ يَلۡتَقِيَانِ
ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
Tafsiran larabci:
بَيۡنَهُمَا بَرۡزَخٞ لَّا يَبۡغِيَانِ
(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Tafsiran larabci:
يَخۡرُجُ مِنۡهُمَا ٱللُّؤۡلُؤُ وَٱلۡمَرۡجَانُ
ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
وَلَهُ ٱلۡجَوَارِ ٱلۡمُنشَـَٔاتُ فِي ٱلۡبَحۡرِ كَٱلۡأَعۡلَٰمِ
እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
كُلُّ مَنۡ عَلَيۡهَا فَانٖ
በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
وَيَبۡقَىٰ وَجۡهُ رَبِّكَ ذُو ٱلۡجَلَٰلِ وَٱلۡإِكۡرَامِ
የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
يَسۡـَٔلُهُۥ مَن فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۚ كُلَّ يَوۡمٍ هُوَ فِي شَأۡنٖ
በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
Tafsiran larabci:
سَنَفۡرُغُ لَكُمۡ أَيُّهَ ٱلثَّقَلَانِ
እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
يَٰمَعۡشَرَ ٱلۡجِنِّ وَٱلۡإِنسِ إِنِ ٱسۡتَطَعۡتُمۡ أَن تَنفُذُواْ مِنۡ أَقۡطَارِ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ فَٱنفُذُواْۚ لَا تَنفُذُونَ إِلَّا بِسُلۡطَٰنٖ
የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
يُرۡسَلُ عَلَيۡكُمَا شُوَاظٞ مِّن نَّارٖ وَنُحَاسٞ فَلَا تَنتَصِرَانِ
በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فَإِذَا ٱنشَقَّتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ وَرۡدَةٗ كَٱلدِّهَانِ
ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُسۡـَٔلُ عَن ذَنۢبِهِۦٓ إِنسٞ وَلَا جَآنّٞ
በዚያም ቀን ሰውም ጃንም ከኃጢኣቱ ገና አይጠየቅም፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
يُعۡرَفُ ٱلۡمُجۡرِمُونَ بِسِيمَٰهُمۡ فَيُؤۡخَذُ بِٱلنَّوَٰصِي وَٱلۡأَقۡدَامِ
ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
هَٰذِهِۦ جَهَنَّمُ ٱلَّتِي يُكَذِّبُ بِهَا ٱلۡمُجۡرِمُونَ
ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
يَطُوفُونَ بَيۡنَهَا وَبَيۡنَ حَمِيمٍ ءَانٖ
በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
وَلِمَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ جَنَّتَانِ
በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
ذَوَاتَآ أَفۡنَانٖ
የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فِيهِمَا عَيۡنَانِ تَجۡرِيَانِ
በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فِيهِمَا مِن كُلِّ فَٰكِهَةٖ زَوۡجَانِ
በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ فُرُشِۭ بَطَآئِنُهَا مِنۡ إِسۡتَبۡرَقٖۚ وَجَنَى ٱلۡجَنَّتَيۡنِ دَانٖ
የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فِيهِنَّ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ
በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
كَأَنَّهُنَّ ٱلۡيَاقُوتُ وَٱلۡمَرۡجَانُ
ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
هَلۡ جَزَآءُ ٱلۡإِحۡسَٰنِ إِلَّا ٱلۡإِحۡسَٰنُ
የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን?
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
وَمِن دُونِهِمَا جَنَّتَانِ
ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
Tafsiran larabci:
مُدۡهَآمَّتَانِ
ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فِيهِمَا عَيۡنَانِ نَضَّاخَتَانِ
በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فِيهِمَا فَٰكِهَةٞ وَنَخۡلٞ وَرُمَّانٞ
በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
فِيهِنَّ خَيۡرَٰتٌ حِسَانٞ
በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
حُورٞ مَّقۡصُورَٰتٞ فِي ٱلۡخِيَامِ
በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
لَمۡ يَطۡمِثۡهُنَّ إِنسٞ قَبۡلَهُمۡ وَلَا جَآنّٞ
ከነርሱ በፊት ሰውም ጃንም አልገሰሳቸውም፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
Tafsiran larabci:
مُتَّكِـِٔينَ عَلَىٰ رَفۡرَفٍ خُضۡرٖ وَعَبۡقَرِيٍّ حِسَانٖ
በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكُمَا تُكَذِّبَانِ
ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
Tafsiran larabci:
تَبَٰرَكَ ٱسۡمُ رَبِّكَ ذِي ٱلۡجَلَٰلِ وَٱلۡإِكۡرَامِ
የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
Tafsiran larabci:
 
Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Al'rahman
Teburin Jerin Sunayen Surori Lambar shafi
 
Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

Rufewa