የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም * - የትርጉሞች ማዉጫ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አል ኢንሺቃቅ   አንቀጽ:

ሱረቱ አል ኢንሺቃቅ

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتۡ
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا ٱلۡأَرۡضُ مُدَّتۡ
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَأَلۡقَتۡ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتۡ
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدۡحٗا فَمُلَٰقِيهِ
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَسَوۡفَ يُحَاسَبُ حِسَابٗا يَسِيرٗا
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورٗا
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهۡرِهِۦ
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَسَوۡفَ يَدۡعُواْ ثُبُورٗا
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَيَصۡلَىٰ سَعِيرًا
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنَّهُۥ كَانَ فِيٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورًا
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بَلَىٰٓۚ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرٗا
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلشَّفَقِ
(አትካዱ)፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلَّيۡلِ وَمَا وَسَقَ
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلۡقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
لَتَرۡكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٖ
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَمَا لَهُمۡ لَا يُؤۡمِنُونَ
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَإِذَا قُرِئَ عَلَيۡهِمُ ٱلۡقُرۡءَانُ لَا يَسۡجُدُونَۤ۩
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?) {1}
{1} እዚህ አንድ የትላዋ ሱጁድ ይደረጋል።
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ يُكَذِّبُونَ
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱللَّهُ أَعۡلَمُ بِمَا يُوعُونَ
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَبَشِّرۡهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ أَجۡرٌ غَيۡرُ مَمۡنُونِۭ
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
 
የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አል ኢንሺቃቅ
የምዕራፎች ማውጫ የገፅ ቁጥር
 
የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም - የትርጉሞች ማዉጫ

ወደ አማርኛ በሸይኽ ሙሓመድ ሷዲቅ እና በሸይኽ ሙሓመድ ሣኒ ሓቢብ የተተረጎመ የቁርዓን መልዕክተ ትርጉም። በሩዋድ የትርጉም ማእከልም ተቆጣጣሪነት ማስተካከያ ተደርጎበታል። ዋናው የትርጉም ቅጅም ለአስተያየቶች፣ ተከታታይ ግምገማ እና መሻሻል ቀርቧል።

መዝጋት