Check out the new design

የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የአማርኛ ትርጉም - በመሐመድ ሳዲቅ * - የትርጉሞች ማዉጫ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: አሽ ሸምስ   አንቀጽ:

አሽ ሸምስ

وَٱلشَّمۡسِ وَضُحَىٰهَا
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلۡقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰهَا
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا طَحَىٰهَا
በምድሪቱም በዘረጋትም፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَنَفۡسٖ وَمَا سَوَّىٰهَا
በነፍስም ባስተካከላትም፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَأَلۡهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقۡوَىٰهَا
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن زَكَّىٰهَا
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَقَدۡ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ بِطَغۡوَىٰهَآ
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشۡقَىٰهَا
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَقَالَ لَهُمۡ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقۡيَٰهَا
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمۡدَمَ عَلَيۡهِمۡ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمۡ فَسَوَّىٰهَا
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَا يَخَافُ عُقۡبَٰهَا
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አይፈራም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
 
የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: አሽ ሸምስ
የምዕራፎች ማውጫ የገፅ ቁጥር
 
የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የአማርኛ ትርጉም - በመሐመድ ሳዲቅ - የትርጉሞች ማዉጫ

በሸይኽ ሙሐመድ ሷዲቅ እና በሸይኽ ሙሐመድ ሣኒ ሓቢብ የተተረጎመ። በሩዋድ የትርጉም ማእከል ቁጥጥር ስር ዝግጁ ሲሆን ዋናው የትርጉም ቅጅ ለአስተያየቶች፣ ተከታታይ ግምገማ እና መሻሻል ቀርቧል።

መዝጋት