ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - زين * - فهرس التراجم


ترجمة معاني سورة: القيامة   آية:

سورة القيامة - ሱረቱ አል ቂያማህ

لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ
1. (ሁኔታው ከሓዲያን እንደሚሉት አይደለም):: በትንሳኤ ቀን እምላለሁ::
التفاسير العربية:
وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ
2. (ሁኔታው ከሓዲያን እንደሚሉት አይደለም):: ራሷን ወቃሽ በሆነች ነፍስም እምላለሁ::
التفاسير العربية:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ
3. (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ።) ሰው አጥንቶችን ለመሰብሰባችን ይጠራጠራልን?
التفاسير العربية:
بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ
4. እንዴታ ጣቶቹንም ፊት እንደነበሩት በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንሆን (እንሰበስባቸዋለን)።
التفاسير العربية:
بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ
5. ይልቁን ሰው በፊቱ ባለ ነገር በትንሳኤ ቀን ሊያስተባብል ይፈልጋል::
التفاسير العربية:
يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ
6. «የትንሳኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል።
التفاسير العربية:
فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ
7. ዓይንም በዋለለ ጊዜ::
التفاسير العربية:
وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ
8. ጨረቃም በጨለመ ጊዜ::
التفاسير العربية:
وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ
9. ጸሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፤
التفاسير العربية:
يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ
10. ሰው በዚያን ቀን «መሸሻው የት ነው?» ይላል።
التفاسير العربية:
كَلَّا لَا وَزَرَ
11. «ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም።
التفاسير العربية:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ
12. በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው።» ይባላል።
التفاسير العربية:
يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
13. ሰው በዚያን ቀን ያስቀደመውም ያስቆየውም ሁሉ ይነገረዋል።
التفاسير العربية:
بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ
14. በእርግጥ ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው::
التفاسير العربية:
وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
15. ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣ እንኳን (አይሰማም)።
التفاسير العربية:
لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ
16. በቁርኣን ንባብ ልትቸኩል ብለህ ምላስህን አታላውስ::
التفاسير العربية:
إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ
17. በልብህ ውስጥ መሰብሰቡና ማስነበቡ በኛ ላይ ነውና::
التفاسير العربية:
فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ
18. ባነበብነው ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል።
التفاسير العربية:
ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ
19. ከዚያም (ላንተ) ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው።
التفاسير العربية:
كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ
20. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከመጣደፍ ተከልከል፤ ይልቁንም (ሰዎች ስትባሉ) ፈጣኒቱን ዓለም ትወዳላችሁ::
التفاسير العربية:
وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
21. የመጨረሻይቱን ዓለም (ግን) ትተዋላችሁ።
التفاسير العربية:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ
22. (የተወሰኑ) ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው።
التفاسير العربية:
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ
23. ወደ ጌታቸው ተመልካቾችም ናቸው::
التفاسير العربية:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ
24. (ሌሎች) ፊቶች ደግሞ በዚያ ቀን አጨፍጋጊዎች ናቸው።
التفاسير العربية:
تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ
25. በእነርሱም ላይ አደጋ እንደሚሰራባቸው ያረጋገጣሉ::
التفاسير العربية:
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ
26. (ሙስሊሞች አስተውሉ።) (ነፍስ) ወደ ጉሮሮ በደረሰች፤
التفاسير العربية:
وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ
27. «አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፤
التفاسير العربية:
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ
28. (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መለየት መሆኑን ባረጋገጠ ጊዜ፤
التفاسير العربية:
وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
29. ባትም ከባት በተጣበቀች ጊዜ፤
التفاسير العربية:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ
30. በዚያ ቀን መነዳት ወደ ጌታህ (ፍርድ) ብቻ ነው።
التفاسير العربية:
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
31. እናም (ከሀዲው) አላመነምም፤ አልሰገደምም።
التفاسير العربية:
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
32. ግን በአላህ አስተባበለ፤ ከእምነት ዞረም::
التفاسير العربية:
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
33. ከዚያም እየተንጎማለለ ወደ ቤተሰቡ ሄደ።
التفاسير العربية:
أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ
34. (የምትጠላውን ነገር) ላንተው ይሁን፤ ላንተ ተገቢህም ነው።
التفاسير العربية:
ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ
35. ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ላንተ የተገባህም ነው።
التفاسير العربية:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى
36. ሰው እንደፈለገ እንዲኖር ልቅ ሆኖ የሚተው ይመስለዋልን?
التفاسير العربية:
أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ
37. የሚፈስ ከሆነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
التفاسير العربية:
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
38. ከዚያ የረጋ ደም ሆነ:: ከዚያ አላህ ሰው አድርጎ ፈጠረው፤ አስተካከለዉም::
التفاسير العربية:
فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
39. ከእርሱም ሁለት ዓይነቶች ወንድና ሴትን አደረገ።
التفاسير العربية:
أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ
40. (ታዲያ) ይህ ሀያል (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
التفاسير العربية:
 
ترجمة معاني سورة: القيامة
فهرس السور رقم الصفحة
 
ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - زين - فهرس التراجم

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

إغلاق