للإطلاع على الموقع بحلته الجديدة

ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - أكاديمية أفريقيا * - فهرس التراجم

PDF XML CSV Excel API
تنزيل الملفات يتضمن الموافقة على هذه الشروط والسياسات

ترجمة معاني سورة: عبس   آية:

سورة عبس - ዐበሰ

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
1. ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፤
التفاسير العربية:
أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ
2. ዓይነስውሩ ወደ እርሱ ስለመጣ።
التفاسير العربية:
وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምን ያሳውቅሃል? ምን አልባትም (ይህ አይነስውር ሰው ካንተ በሚሰማው ምክር ከኃጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል::
التفاسير العربية:
أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ
4. ወይም ሊገሰጽና ግሳጼይቱም ልትጠቅመው ይከጀላል::
التفاسير العربية:
أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ
5. ያ! ከአላህ የተብቃቃውን ሰውማ፤
التفاسير العربية:
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
6. አንተ ለእርሱ ትዘጋጃለህ።
التفاسير العربية:
وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
7. ባይጥራራ (ባያምን)፤ ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትሆን፤
التفاسير العربية:
وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ
8. ያ! እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
التفاسير العربية:
وَهُوَ يَخۡشَىٰ
9. እርሱ አላህን የሚፈራ ሲሆን፤
التفاسير العربية:
فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ
10. አንተ ከእርሱ ትዘናጋለህ::
التفاسير العربية:
كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ
11. ተከልከል፤ (ቁርኣን) ማስገንዘቢያ ነው::
التفاسير العربية:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
12. የፈለገ ሰው ሁሉ (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል::
التفاسير العربية:
فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ
13. በተከበሩት ጹሑፎች ውስጥ ነው::
التفاسير العربية:
مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ
14. ከፍ በተደረገች፤ ንጹህም በተደረገች (ጹሑፍ ውስጥ ነው)።
التفاسير العربية:
بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ
15. በጸሐፊዎች መላዕክት እጆች (ንጹህ የተደረገ)::
التفاسير العربية:
كِرَامِۭ بَرَرَةٖ
16. የተከበሩና ታዛዦች በሆኑት ጸሐፊዎች (እጆች)፤
التفاسير العربية:
قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ
17. ሰው ተረገመ። ምን ከሓዲ አደረገው?
التفاسير العربية:
مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ
18. (ጌታው) ከምን ነገር ፈጠረው?
التفاسير العربية:
مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
19. (አያስብምን?) ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነዉም::
التفاسير العربية:
ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
20. ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው::
التفاسير العربية:
ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ
21. ከዚያም ገደለው:: እንዲቀበርም አደረገው፤
التفاسير العربية:
ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
22. ከዚያ ማንሳቱን በፈለገ ጊዜ ያስነሳዋል::
التفاسير العربية:
كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ
23. በእውነት ያንን ጌታው ያዘዘውን ገና አልፈጸመም::
التفاسير العربية:
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
24. ሰው ወደ ምግቡ ይመልከት፤
التفاسير العربية:
أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا
25. እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መሆናችንን፤
التفاسير العربية:
ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا
26. ከዚያ ምድርን በደካማ ቡቃያ መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
التفاسير العربية:
فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا
27. በውስጧም እህልን ያበቀልን
التفاسير العربية:
وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا
28. ወይንም እርጥብ ሳርንም፤
التفاسير العربية:
وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا
29. የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
التفاسير العربية:
وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا
30. ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
التفاسير العربية:
وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا
31. ፍራፍሬንና፤ ገለባንም (ያበቀልን መሆናችንን ይመልከት)።
التفاسير العربية:
مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
32. ለእናንተም ለእንሰሶቻችሁም መጠቀሚያ ይሆን ዘንድ (ይህን ሰራን)::
التفاسير العربية:
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
33. አደንቋሪይቱ (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
التفاسير العربية:
يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ
34. ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
التفاسير العربية:
وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
35. ከእናቱም፤ ከአባቱም፤ (በሚሸሽበት ቀን)
التفاسير العربية:
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
36. ከሚስቱና ከልጁም፤ (በሚሸሽበት ቀን)
التفاسير العربية:
لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ
37. ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን ከሌላው የሚያብቃቃው ሁኔታ አለው::
التفاسير العربية:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ
38. ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች፤
التفاسير العربية:
ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ
39. ሳቂዎችና ተደሳቾች ናቸው::
التفاسير العربية:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ
40. ፊቶች ደግሞ በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትብያ አለባቸው።
التفاسير العربية:
تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ
41. ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
التفاسير العربية:
أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ
42. እነዚያ እነርሱ በአላህ ከሓዲያን እና በትዕዛዙ ላይ አመጸኞቹ ናቸው።
التفاسير العربية:
 
ترجمة معاني سورة: عبس
فهرس السور رقم الصفحة
 
ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - أكاديمية أفريقيا - فهرس التراجم

ترجمها محمد زين زهر الدين. صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

إغلاق