আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ * - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ৱাক্বিয়াহ   আয়াত:

ሱረቱ አል ዋቂዓህ

إِذَا وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَيۡسَ لِوَقۡعَتِهَا كَاذِبَةٌ
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
خَافِضَةٞ رَّافِعَةٌ
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِذَا رُجَّتِ ٱلۡأَرۡضُ رَجّٗا
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَبُسَّتِ ٱلۡجِبَالُ بَسّٗا
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَكَانَتۡ هَبَآءٗ مُّنۢبَثّٗا
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكُنتُمۡ أَزۡوَٰجٗا ثَلَٰثَةٗ
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلسَّٰبِقُونَ
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أُوْلَٰٓئِكَ ٱلۡمُقَرَّبُونَ
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَقَلِيلٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَلَىٰ سُرُرٖ مَّوۡضُونَةٖ
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيۡهَا مُتَقَٰبِلِينَ
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
يَطُوفُ عَلَيۡهِمۡ وِلۡدَٰنٞ مُّخَلَّدُونَ
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بِأَكۡوَابٖ وَأَبَارِيقَ وَكَأۡسٖ مِّن مَّعِينٖ
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا يُصَدَّعُونَ عَنۡهَا وَلَا يُنزِفُونَ
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفَٰكِهَةٖ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ
ከሚመርጡትም ዓይነት እሸቶች፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَحۡمِ طَيۡرٖ مِّمَّا يَشۡتَهُونَ
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَحُورٌ عِينٞ
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَأَمۡثَٰلِ ٱللُّؤۡلُوِٕ ٱلۡمَكۡنُونِ
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
جَزَآءَۢ بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا تَأۡثِيمًا
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِلَّا قِيلٗا سَلَٰمٗا سَلَٰمٗا
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي سِدۡرٖ مَّخۡضُودٖ
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَطَلۡحٖ مَّنضُودٖ
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَظِلّٖ مَّمۡدُودٖ
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَمَآءٖ مَّسۡكُوبٖ
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفَٰكِهَةٖ كَثِيرَةٖ
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا مَقۡطُوعَةٖ وَلَا مَمۡنُوعَةٖ
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفُرُشٖ مَّرۡفُوعَةٍ
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّآ أَنشَأۡنَٰهُنَّ إِنشَآءٗ
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَجَعَلۡنَٰهُنَّ أَبۡكَارًا
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عُرُبًا أَتۡرَابٗا
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لِّأَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي سَمُومٖ وَحَمِيمٖ
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَظِلّٖ مِّن يَحۡمُومٖ
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا بَارِدٖ وَلَا كَرِيمٍ
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُتۡرَفِينَ
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكَانُواْ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلۡحِنثِ ٱلۡعَظِيمِ
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكَانُواْ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
قُلۡ إِنَّ ٱلۡأَوَّلِينَ وَٱلۡأٓخِرِينَ
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَمَجۡمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ إِنَّكُمۡ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلۡمُكَذِّبُونَ
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَأٓكِلُونَ مِن شَجَرٖ مِّن زَقُّومٖ
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَشَٰرِبُونَ عَلَيۡهِ مِنَ ٱلۡحَمِيمِ
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَشَٰرِبُونَ شُرۡبَ ٱلۡهِيمِ
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
هَٰذَا نُزُلُهُمۡ يَوۡمَ ٱلدِّينِ
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَحۡنُ خَلَقۡنَٰكُمۡ فَلَوۡلَا تُصَدِّقُونَ
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُم مَّا تُمۡنُونَ
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ تَخۡلُقُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡخَٰلِقُونَ
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَحۡنُ قَدَّرۡنَا بَيۡنَكُمُ ٱلۡمَوۡتَ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ أَمۡثَٰلَكُمۡ وَنُنشِئَكُمۡ فِي مَا لَا تَعۡلَمُونَ
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَقَدۡ عَلِمۡتُمُ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُولَىٰ فَلَوۡلَا تَذَكَّرُونَ
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُم مَّا تَحۡرُثُونَ
የምትዘሩትንም አያችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ تَزۡرَعُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلزَّٰرِعُونَ
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَوۡ نَشَآءُ لَجَعَلۡنَٰهُ حُطَٰمٗا فَظَلۡتُمۡ تَفَكَّهُونَ
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّا لَمُغۡرَمُونَ
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلۡمَآءَ ٱلَّذِي تَشۡرَبُونَ
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ أَنزَلۡتُمُوهُ مِنَ ٱلۡمُزۡنِ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنزِلُونَ
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَوۡ نَشَآءُ جَعَلۡنَٰهُ أُجَاجٗا فَلَوۡلَا تَشۡكُرُونَ
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِي تُورُونَ
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ أَنشَأۡتُمۡ شَجَرَتَهَآ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنشِـُٔونَ
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَحۡنُ جَعَلۡنَٰهَا تَذۡكِرَةٗ وَمَتَٰعٗا لِّلۡمُقۡوِينَ
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
۞ فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوۡ تَعۡلَمُونَ عَظِيمٌ
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُۥ لَقُرۡءَانٞ كَرِيمٞ
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي كِتَٰبٖ مَّكۡنُونٖ
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَبِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ أَنتُم مُّدۡهِنُونَ
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَتَجۡعَلُونَ رِزۡقَكُمۡ أَنَّكُمۡ تُكَذِّبُونَ
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَلَوۡلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلۡحُلۡقُومَ
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَنتُمۡ حِينَئِذٖ تَنظُرُونَ
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَنَحۡنُ أَقۡرَبُ إِلَيۡهِ مِنكُمۡ وَلَٰكِن لَّا تُبۡصِرُونَ
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَلَوۡلَآ إِن كُنتُمۡ غَيۡرَ مَدِينِينَ
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
تَرۡجِعُونَهَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَرَوۡحٞ وَرَيۡحَانٞ وَجَنَّتُ نَعِيمٖ
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَلَٰمٞ لَّكَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُكَذِّبِينَ ٱلضَّآلِّينَ
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَنُزُلٞ مِّنۡ حَمِيمٖ
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَتَصۡلِيَةُ جَحِيمٍ
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ ٱلۡيَقِينِ
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
 
অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ৱাক্বিয়াহ
ছুৰাৰ তালিকা পৃষ্ঠা নং
 
আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

বন্ধ