Check out the new design

Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Muhammad Sadiq * - Translations’ Index

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Translation of the meanings Surah: Al-‘Alaq   Ayah:

አል ዐለቅ

ٱقۡرَأۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلَّذِي خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡{1}
{1} ይህ አንቀጽና ቀጥሎ ያሉት ከቁርአን መጀመሪያ የወረዱ አንቀጾች ናቸው። በኑር ተራራ ላይ በምገኘው የሂራእ ዋሻ ውስጥ ነቢዩ ሰ/ዐ/ወ/ ኸልዋ ወጥተው እያሉ ነው የወረደባቸው። (ቡኻሪና ሙስሊም፤ የወህይ አጀማመር ምእራፍ)
Arabic explanations of the Qur’an:
خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِنۡ عَلَقٍ
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
ٱقۡرَأۡ وَرَبُّكَ ٱلۡأَكۡرَمُ
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
Arabic explanations of the Qur’an:
ٱلَّذِي عَلَّمَ بِٱلۡقَلَمِ
ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
عَلَّمَ ٱلۡإِنسَٰنَ مَا لَمۡ يَعۡلَمۡ
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّآ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لَيَطۡغَىٰٓ
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
أَن رَّءَاهُ ٱسۡتَغۡنَىٰٓ
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجۡعَىٰٓ
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يَنۡهَىٰ
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰٓ
ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
أَرَءَيۡتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلۡهُدَىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
Arabic explanations of the Qur’an:
أَوۡ أَمَرَ بِٱلتَّقۡوَىٰٓ
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
أَرَءَيۡتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
أَلَمۡ يَعۡلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ
አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّا لَئِن لَّمۡ يَنتَهِ لَنَسۡفَعَۢا بِٱلنَّاصِيَةِ
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
نَاصِيَةٖ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٖ
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
فَلۡيَدۡعُ نَادِيَهُۥ
ሸንጎውንም ይጥራ፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
سَنَدۡعُ ٱلزَّبَانِيَةَ
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّا لَا تُطِعۡهُ وَٱسۡجُدۡۤ وَٱقۡتَرِب۩
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡ {1}
{1} እዚህ የንባብ ሱጁድ አለ። ይህ የመጨረሻ ሱጁድ ነው።
Arabic explanations of the Qur’an:
 
Translation of the meanings Surah: Al-‘Alaq
Surahs’ Index Page Number
 
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Muhammad Sadiq - Translations’ Index

Translated by Sh. Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib and developed under the supervision of Rowwad Translation Center. The original translation is available for review, evaluation, and continuous development.

close