Check out the new design

Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Africa Academy * - Translations’ Index


Translation of the meanings Surah: Al-Infitār   Ayah:

አል ኢንፊጣር

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتۡ
1. ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِذَا ٱلۡكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتۡ
2. ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ فُجِّرَتۡ
3. ባህሮችም በተከፈቱና በተደባለቁ ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِذَا ٱلۡقُبُورُ بُعۡثِرَتۡ
4. መቃብሮችም በተገለባበጡና ሙታን በተነሱ ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّا قَدَّمَتۡ وَأَخَّرَتۡ
5. (ያኔ) ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያዘገየችውን ታውቃለች።
Arabic explanations of the Qur’an:
يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ
6. አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
Arabic explanations of the Qur’an:
ٱلَّذِي خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ
7. በዚያ በፈጠረህ፤ አካለ ሙሉም ባደረገህ፤ ባስተካከለህም፤
Arabic explanations of the Qur’an:
فِيٓ أَيِّ صُورَةٖ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ
8. በማንኛውም (እርሱ) በፈለገው ቅርጽ በገጣጠመህ ጌታህ ምን አታለለህ?
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّا بَلۡ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ
9 (ሰዎች ሆይ!) ተከልከሉ፤ በእውነት በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِنَّ عَلَيۡكُمۡ لَحَٰفِظِينَ
10. በእናንተ ላይ ጠባቂዎች ያሉባችሁ ስትሆኑ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
كِرَامٗا كَٰتِبِينَ
11. የተከበሩ ጸሐፊዎች የሆኑ (ተጠባባቂዎች)፤
Arabic explanations of the Qur’an:
يَعۡلَمُونَ مَا تَفۡعَلُونَ
12. የምትሰሩትን (ሁሉ) ያውቃሉ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ ٱلۡأَبۡرَارَ لَفِي نَعِيمٖ
13. (እውነተኞቹ) ደጋጎች በእርግጥም በገነት ውስጥ ናቸው።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِنَّ ٱلۡفُجَّارَ لَفِي جَحِيمٖ
14.ከሓዲያንም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው::
Arabic explanations of the Qur’an:
يَصۡلَوۡنَهَا يَوۡمَ ٱلدِّينِ
15.በፍርዱ ቀን ይገቧታል::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَا هُمۡ عَنۡهَا بِغَآئِبِينَ
16.እነርሱም (ምን ጊዜም) ከእርሷ ራቂዎች አይደሉም::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የፍርዱ ቀን ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ مَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
18. ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደሆነ ምን አሳወቅህ?
Arabic explanations of the Qur’an:
يَوۡمَ لَا تَمۡلِكُ نَفۡسٞ لِّنَفۡسٖ شَيۡـٔٗاۖ وَٱلۡأَمۡرُ يَوۡمَئِذٖ لِّلَّهِ
19. (እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግ የማትችልበት ቀን ነው:: ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው::
Arabic explanations of the Qur’an:
 
Translation of the meanings Surah: Al-Infitār
Surahs’ Index Page Number
 
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Africa Academy - Translations’ Index

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

close