ترجمهٔ معانی قرآن کریم - الترجمة الأمهرية - زين * - لیست ترجمه ها


ترجمهٔ معانی سوره: سوره قلم   آیه:

ሱረቱ አል ቀለም

نٓۚ وَٱلۡقَلَمِ وَمَا يَسۡطُرُونَ
1. ኑን፤ በብዕር እና በዚያም በሱ በሚጽፉት ሁሉ እምላለሁ::
تفسیرهای عربی:
مَآ أَنتَ بِنِعۡمَةِ رَبِّكَ بِمَجۡنُونٖ
2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንተ በጌታህ ጸጋ ምክኒያት ዕብድ አይደለህም::
تفسیرهای عربی:
وَإِنَّ لَكَ لَأَجۡرًا غَيۡرَ مَمۡنُونٖ
3. ላንተም ከጌታህ የማይቋረጥ ምንዳ (የልፋት ዋጋ) በእርግጥ አለህ::
تفسیرهای عربی:
وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٖ
4. አንተም በታላቅ ጸባይ ላይ ነህ::
تفسیرهای عربی:
فَسَتُبۡصِرُ وَيُبۡصِرُونَ
5. ወደ ፊት አንተም ታያለህ፤ እነርሱም ያያሉ፤
تفسیرهای عربی:
بِأَييِّكُمُ ٱلۡمَفۡتُونُ
6. ዕብደት በማንኛችሁ እንዳለ (እብዱ ማን እንደሆነ)::
تفسیرهای عربی:
إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِٱلۡمُهۡتَدِينَ
7. ጌታህ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው አዋቂ ነው። ወደ ቀናው መንገድ ተመሪዎችንም አዋቂ ነው::
تفسیرهای عربی:
فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِينَ
8. ስለዚህ ለአስተባባዩች (ሁሉ) አትታዘዝ::
تفسیرهای عربی:
وَدُّواْ لَوۡ تُدۡهِنُ فَيُدۡهِنُونَ
9. (አስተባባዩች) ብትመሳሰላቸውና እነርሱም ቢመሳሰሉህ ተመኙ::
تفسیرهای عربی:
وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافٖ مَّهِينٍ
10. መሓለኛን ወራዳን ሁሉ አትታዘዝ።
تفسیرهای عربی:
هَمَّازٖ مَّشَّآءِۭ بِنَمِيمٖ
11. ሰውን አነዋሪን፤ ነገር አሳባቂን፤
تفسیرهای عربی:
مَّنَّاعٖ لِّلۡخَيۡرِ مُعۡتَدٍ أَثِيمٍ
12.ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፤ ወሰን አላፊን፤ ኃጢአተኛንም፤
تفسیرهای عربی:
عُتُلِّۭ بَعۡدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ
13. ልበ ደረቅን ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ የዝሙት ልጅ ዲቃላን (አትታዘዝ)::
تفسیرهای عربی:
أَن كَانَ ذَا مَالٖ وَبَنِينَ
14. የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመሆኑ (ያስተባብላል)።
تفسیرهای عربی:
إِذَا تُتۡلَىٰ عَلَيۡهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
15. በእርሱ ላይ እንቀፆቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል::
تفسیرهای عربی:
سَنَسِمُهُۥ عَلَى ٱلۡخُرۡطُومِ
16. በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክትን እናደርግበታለን::
تفسیرهای عربی:
إِنَّا بَلَوۡنَٰهُمۡ كَمَا بَلَوۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡجَنَّةِ إِذۡ أَقۡسَمُواْ لَيَصۡرِمُنَّهَا مُصۡبِحِينَ
17. እኛ እነዚያን የአትክልቲቱን ባለቤቶች ማልደው ፍሬዋን ሊለቅሟት (አላህ ቢሻ ሳይሉ) በማሉ ጊዜ እንደሞከርን ሁሉ የመካ ሰዎችንም ሞከርናቸው::
تفسیرهای عربی:
وَلَا يَسۡتَثۡنُونَ
18. (በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
تفسیرهای عربی:
فَطَافَ عَلَيۡهَا طَآئِفٞ مِّن رَّبِّكَ وَهُمۡ نَآئِمُونَ
19.እነርሱ የተኙ ሆነዉም ሳሉ ከጌታህ የሆነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት::
تفسیرهای عربی:
فَأَصۡبَحَتۡ كَٱلصَّرِيمِ
20. እንደ ሌሊት ጨለማ የከሰለች ሆና አነጋች (አደረች)።
تفسیرهای عربی:
فَتَنَادَوۡاْ مُصۡبِحِينَ
21.ያነጉም ሆነው ተጠራሩ
تفسیرهای عربی:
أَنِ ٱغۡدُواْ عَلَىٰ حَرۡثِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰرِمِينَ
22. "ቆራጮች እንደ ሆናችሁ ወደ እርሻችሁ ለመሄድ ማልዱ በማለት" (ተጠራሩ)::
تفسیرهای عربی:
فَٱنطَلَقُواْ وَهُمۡ يَتَخَٰفَتُونَ
23. እነርሱ የሚያሾካሾኩ ሆነው ሄዱም::
تفسیرهای عربی:
أَن لَّا يَدۡخُلَنَّهَا ٱلۡيَوۡمَ عَلَيۡكُم مِّسۡكِينٞ
24. ዛሬ በእናንተ ላይ አንድም ድሃ እንዳይገባት በማለትና
تفسیرهای عربی:
وَغَدَوۡاْ عَلَىٰ حَرۡدٖ قَٰدِرِينَ
25. ድሆችን በመከልከልም ላይ በሀሳባቸው ቻዮች ሆነው ማለዱ::
تفسیرهای عربی:
فَلَمَّا رَأَوۡهَا قَالُوٓاْ إِنَّا لَضَآلُّونَ
26. ከዚያ ተቃጥላ ባዩዋት ጊዜ (እንዲህ) አሉ: «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን፤
تفسیرهای عربی:
بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ
27. «ይልቁንም እኛ ከአላህ የተከለከልን እደለ ቢሶች ነን» አሉ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ أَوۡسَطُهُمۡ أَلَمۡ أَقُل لَّكُمۡ لَوۡلَا تُسَبِّحُونَ
28. (ከመካከላቸው) ትክክለኛቸው (አስተዋያቸው)፡- «እናንተ አላህን ለምን አታጠሩም (አታወሱም) አላልኳችሁም ነበርን?» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالُواْ سُبۡحَٰنَ رَبِّنَآ إِنَّا كُنَّا ظَٰلِمِينَ
29. «(ሁላቸዉም) ጌታችን ጥራት ይገባው፤ እኛ በዳዩች ነበርን» አሉ።
تفسیرهای عربی:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَلَٰوَمُونَ
30. እርስ በራሳቸው የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ::
تفسیرهای عربی:
قَالُواْ يَٰوَيۡلَنَآ إِنَّا كُنَّا طَٰغِينَ
31. «ዋ፤ጥፋታችን፤ እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን» አሉ::
تفسیرهای عربی:
عَسَىٰ رَبُّنَآ أَن يُبۡدِلَنَا خَيۡرٗا مِّنۡهَآ إِنَّآ إِلَىٰ رَبِّنَا رَٰغِبُونَ
32. «ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል:: እኛ ወደ ጌታችን ከጃዩች ነን» አሉ::
تفسیرهای عربی:
كَذَٰلِكَ ٱلۡعَذَابُۖ وَلَعَذَابُ ٱلۡأٓخِرَةِ أَكۡبَرُۚ لَوۡ كَانُواْ يَعۡلَمُونَ
33. (የአላህ) ቅጣቱ ልክ እንደዚሁ ነው:: የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ከዚህ የበለጠ ከባድ ነው:: የሚያውቁ ቢሆኑ ኖሮ (ከዚህ ቅጣት በተጠነቀቁ ነበር)::
تفسیرهای عربی:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمۡ جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
34. ለጥንቁቆች በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው::
تفسیرهای عربی:
أَفَنَجۡعَلُ ٱلۡمُسۡلِمِينَ كَٱلۡمُجۡرِمِينَ
35. ሙስሊሞችን እንደ ከሓዲያን እናደርጋለን? (አናደርግም)::
تفسیرهای عربی:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
36. ለእናንተ ምን (አስረጂ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ( ምን ነካችሁ)::
تفسیرهای عربی:
أَمۡ لَكُمۡ كِتَٰبٞ فِيهِ تَدۡرُسُونَ
37. በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
تفسیرهای عربی:
إِنَّ لَكُمۡ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ
38. በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁን? (የሚል)::
تفسیرهای عربی:
أَمۡ لَكُمۡ أَيۡمَٰنٌ عَلَيۡنَا بَٰلِغَةٌ إِلَىٰ يَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ إِنَّ لَكُمۡ لَمَا تَحۡكُمُونَ
39. ወይስ «ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ» በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሳኤ ቀን ደራሽ የሆኑ መሐላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
تفسیرهای عربی:
سَلۡهُمۡ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ
40. በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
تفسیرهای عربی:
أَمۡ لَهُمۡ شُرَكَآءُ فَلۡيَأۡتُواْ بِشُرَكَآئِهِمۡ إِن كَانُواْ صَٰدِقِينَ
41. ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) ተጋሪዎች አሏቸውን? እውነተኞችም እንደሆኑ ተጋሪዎቻቸውን ያምጡ::
تفسیرهای عربی:
يَوۡمَ يُكۡشَفُ عَن سَاقٖ وَيُدۡعَوۡنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ فَلَا يَسۡتَطِيعُونَ
42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ያን ባት የሚገለጥበትን፤ (ከሓዲያን) ወደ መስገድ የሚጠሩበትና የማይችሉበትን ቀን (አስታውስ)::
تفسیرهای عربی:
خَٰشِعَةً أَبۡصَٰرُهُمۡ تَرۡهَقُهُمۡ ذِلَّةٞۖ وَقَدۡ كَانُواْ يُدۡعَوۡنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ وَهُمۡ سَٰلِمُونَ
43. ዓይኖቻቸው የፈሩ፤ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲሆኑ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን):: እነርሱ (በምድረ ዓለም) ደህና ሆነው ሳሉ ወደ ስግድት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ::
تفسیرهای عربی:
فَذَرۡنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِۖ سَنَسۡتَدۡرِجُهُم مِّنۡ حَيۡثُ لَا يَعۡلَمُونَ
44. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በመሆኑም እኔን በዚህ ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተወኝ፤ (ለእነርሱ እኔ እበቃሃለሁ):: ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን::
تفسیرهای عربی:
وَأُمۡلِي لَهُمۡۚ إِنَّ كَيۡدِي مَتِينٌ
45. እነርሱንም አዘገያቸዋለሁ:: (ዘዴዬ) ብቀላየ ብርቱ ነውና::
تفسیرهای عربی:
أَمۡ تَسۡـَٔلُهُمۡ أَجۡرٗا فَهُم مِّن مَّغۡرَمٖ مُّثۡقَلُونَ
46. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ወይንስ በእውነቱ (በማስተማርህ) ዋጋን እንዲከፍሉህ ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
تفسیرهای عربی:
أَمۡ عِندَهُمُ ٱلۡغَيۡبُ فَهُمۡ يَكۡتُبُونَ
47. ወይስ ከእነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር እውቀት አለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
تفسیرهای عربی:
فَٱصۡبِرۡ لِحُكۡمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ ٱلۡحُوتِ إِذۡ نَادَىٰ وَهُوَ مَكۡظُومٞ
48. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ)፤ ለጌታህ (ዉሳኔ) ፍርድ ታገስ:: (በመበሳጨትና ባለ መታገስ) እንደ ዓሳው ባለቤት እንደ (ነብዩ ዩኑስ) አትሁን:: እርሱ በጭንቀት የተሞላ ሆኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ
تفسیرهای عربی:
لَّوۡلَآ أَن تَدَٰرَكَهُۥ نِعۡمَةٞ مِّن رَّبِّهِۦ لَنُبِذَ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ مَذۡمُومٞ
49. ከጌታው የሆነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ሆኖ በተጣለ ነበር::
تفسیرهای عربی:
فَٱجۡتَبَٰهُ رَبُّهُۥ فَجَعَلَهُۥ مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
50. ጌታዉም (በነብይነት) መረጠው:: ከደጋጎችም አደረገው::
تفسیرهای عربی:
وَإِن يَكَادُ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لَيُزۡلِقُونَكَ بِأَبۡصَٰرِهِمۡ لَمَّا سَمِعُواْ ٱلذِّكۡرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُۥ لَمَجۡنُونٞ
51. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነሆ እነዚያ በአላህ የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው (ሊያጠፉህ) ይቃረባሉ፤ «እርሱም በእርግጥ እብድ ነዉም» ይላሉ::
تفسیرهای عربی:
وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ
52.እርሱ ግን ለዓለማት መገሰጫ (ገሳጭ) እንጂ ሌላ አይደለም::
تفسیرهای عربی:
 
ترجمهٔ معانی سوره: سوره قلم
فهرست سوره ها شماره صفحه
 
ترجمهٔ معانی قرآن کریم - الترجمة الأمهرية - زين - لیست ترجمه ها

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

بستن