Check out the new design

Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Eggo Amhariiwo - Akademii Afrik * - Tippudi firooji ɗii


Firo maanaaji Simoore: Simooee njomolaaji   Aaya:

አል ዐንከቡት

الٓمٓ
1. አሊፍ፤ ላም፤ ሚይም፤
Faccirooji aarabeeji:
أَحَسِبَ ٱلنَّاسُ أَن يُتۡرَكُوٓاْ أَن يَقُولُوٓاْ ءَامَنَّا وَهُمۡ لَا يُفۡتَنُونَ
2. ሰዎቹ አምነናል በማለታቸው ብቻ (ከአላህ በልዩ ልዩ ነገሮች) ሳይፈተኑ የሚተው መሰላቸውን?
Faccirooji aarabeeji:
وَلَقَدۡ فَتَنَّا ٱلَّذِينَ مِن قَبۡلِهِمۡۖ فَلَيَعۡلَمَنَّ ٱللَّهُ ٱلَّذِينَ صَدَقُواْ وَلَيَعۡلَمَنَّ ٱلۡكَٰذِبِينَ
3. እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትንም ህዝቦች በርግጥ ፈትነናል። እነዚያን እውነት የተናገሩትን አላህ በእርግጥ ያውቃል። ውሸታሞችንም ያውቃል።
Faccirooji aarabeeji:
أَمۡ حَسِبَ ٱلَّذِينَ يَعۡمَلُونَ ٱلسَّيِّـَٔاتِ أَن يَسۡبِقُونَاۚ سَآءَ مَا يَحۡكُمُونَ
4.ይልቁንም እነዚያ መጥፎዎችን ሥራዎች የሚሠሩት ሰዎች የሚያመልጡን መሰላቸውን? ያ የሚፈርዱት ፍርድ ከፋ::
Faccirooji aarabeeji:
مَن كَانَ يَرۡجُواْ لِقَآءَ ٱللَّهِ فَإِنَّ أَجَلَ ٱللَّهِ لَأٓتٖۚ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ
5. የአላህን መገናኘት ተስፋ የሚያደርግ ሰው ሁሉ የአላህ ቀጠሮ በእርግጥ መጪ ነው:: እርሱም ሰሚም ሁሉን አዋቂ ነው።
Faccirooji aarabeeji:
وَمَن جَٰهَدَ فَإِنَّمَا يُجَٰهِدُ لِنَفۡسِهِۦٓۚ إِنَّ ٱللَّهَ لَغَنِيٌّ عَنِ ٱلۡعَٰلَمِينَ
6. በአላህ መንገድ ላይ የታገለ ሰው የሚታገለው ለነፍሱ ብቻ ነው:: አላህ ከዓለማት ሁሉ በእርግጥ የተብቃቃ ነውና::
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَنُكَفِّرَنَّ عَنۡهُمۡ سَيِّـَٔاتِهِمۡ وَلَنَجۡزِيَنَّهُمۡ أَحۡسَنَ ٱلَّذِي كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
7. እነዚያም በአላህና በመልዕክተኛው ያመኑና መልካም ተግባራትንም የሠሩ መጥፎ ሥራዎቻቸውን ከእነርሱ ላይ እናብስላቸዋለን። በዚያም ይሠሩት በነበሩት መልካም ሥራ በእርግጥ እንመነዳቸዋለን።
Faccirooji aarabeeji:
وَوَصَّيۡنَا ٱلۡإِنسَٰنَ بِوَٰلِدَيۡهِ حُسۡنٗاۖ وَإِن جَٰهَدَاكَ لِتُشۡرِكَ بِي مَا لَيۡسَ لَكَ بِهِۦ عِلۡمٞ فَلَا تُطِعۡهُمَآۚ إِلَيَّ مَرۡجِعُكُمۡ فَأُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
8. የሰውን ልጅ ለወላጆቹ መልካም ተግባርን ሁሉ እንዲፈጽም አዘዝነው:: ወላጆችም ላንተም በእርሱ እውቀት የሌለህን ጣኦት በእኔ እንድታጋራው ቢያስገድዱህ አትታዘዛቸው:: መመለሻችሁ ወደ እኔ ነው:: ከዚያም ትሠሩት የነበራችሁትን ሁሉ እነግራችኋለሁ::
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَنُدۡخِلَنَّهُمۡ فِي ٱلصَّٰلِحِينَ
9. እነዚያንም በአላህ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ ሁሉ ከደጋጎቹ ውስጥ በእርግጥ እናስገባቸዋለን::
Faccirooji aarabeeji:
وَمِنَ ٱلنَّاسِ مَن يَقُولُ ءَامَنَّا بِٱللَّهِ فَإِذَآ أُوذِيَ فِي ٱللَّهِ جَعَلَ فِتۡنَةَ ٱلنَّاسِ كَعَذَابِ ٱللَّهِۖ وَلَئِن جَآءَ نَصۡرٞ مِّن رَّبِّكَ لَيَقُولُنَّ إِنَّا كُنَّا مَعَكُمۡۚ أَوَلَيۡسَ ٱللَّهُ بِأَعۡلَمَ بِمَا فِي صُدُورِ ٱلۡعَٰلَمِينَ
10. ከሰዎች መካከል «በአላህ አመንን።» የሚል ሰው አለ:: ከዚያ በአላህ በማመኑ ምክኒያት በተሰቃየ ጊዜ የሰዎችን ማሰቃየት እንደ አላህ ቅጣት ያደርጋል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከጌታህም እርዳታ ቢመጣ እኛ በእርግጥ ከናንተ ጋር ነበርን ይላሉ:: አላህ በዓለማት ሕዝብ ልቦች ውስጥ ያለውን ሁሉ አዋቂ አይደለምን?
Faccirooji aarabeeji:
وَلَيَعۡلَمَنَّ ٱللَّهُ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَلَيَعۡلَمَنَّ ٱلۡمُنَٰفِقِينَ
11. አላህ እነዚያንም በትክክል ያመኑትን በእርግጥ ያውቃል:: መናፍቆቹንም ያውቃል::
Faccirooji aarabeeji:
وَقَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لِلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱتَّبِعُواْ سَبِيلَنَا وَلۡنَحۡمِلۡ خَطَٰيَٰكُمۡ وَمَا هُم بِحَٰمِلِينَ مِنۡ خَطَٰيَٰهُم مِّن شَيۡءٍۖ إِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ
12. እነዚያንም የካዱት ሰዎች ለእነዚያ ላመኑት «መንገዳችንን ተከተሉ:: ኃጢአቶቻችሁንም እንሸከማለን» አሉ:: እነርሱም ከኃጢአቶቻቸው ምንንም ተሸካሚዎች አይደሉም:: እነርሱ በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው።
Faccirooji aarabeeji:
وَلَيَحۡمِلُنَّ أَثۡقَالَهُمۡ وَأَثۡقَالٗا مَّعَ أَثۡقَالِهِمۡۖ وَلَيُسۡـَٔلُنَّ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ عَمَّا كَانُواْ يَفۡتَرُونَ
13. ሸክሞቻቸውንና ከሸክሞቻቸው ጋር ሌሎች ሸክሞችንም በእርግጥ ይሸከማሉ:: በትንሳኤም ቀን ይቀጥፉት ከነበሩት ሁሉ በእርግጥ ይጠየቃሉ::
Faccirooji aarabeeji:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا نُوحًا إِلَىٰ قَوۡمِهِۦ فَلَبِثَ فِيهِمۡ أَلۡفَ سَنَةٍ إِلَّا خَمۡسِينَ عَامٗا فَأَخَذَهُمُ ٱلطُّوفَانُ وَهُمۡ ظَٰلِمُونَ
14. ኑሕንም ወደ ህዝቦቹ በእርግጥ ላክነው:: በውስጣቸዉም ሺህ ዓመትን ሀምሳ ዓመት ሲቀር ተቀመጠ:: እነርሱ በዳዮች ሆነዉም የውሃው ማዕበል አጥለቀለቃቸው::
Faccirooji aarabeeji:
فَأَنجَيۡنَٰهُ وَأَصۡحَٰبَ ٱلسَّفِينَةِ وَجَعَلۡنَٰهَآ ءَايَةٗ لِّلۡعَٰلَمِينَ
15. ኑህንና የመርከቢቱን ጓዶች አዳንናቸው:: እርሷንም ለዓለማት ተዓምር አደረግናት::
Faccirooji aarabeeji:
وَإِبۡرَٰهِيمَ إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِ ٱعۡبُدُواْ ٱللَّهَ وَٱتَّقُوهُۖ ذَٰلِكُمۡ خَيۡرٞ لَّكُمۡ إِن كُنتُمۡ تَعۡلَمُونَ
16. መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ኢብራሒም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ የሆነውን (አስታውስ)። «አላህን ተገዙ ፍሩትም ይህን ማድረጋችሁ የምታውቁት ብትሆኑ ለናንተ በላጭ ነው።
Faccirooji aarabeeji:
إِنَّمَا تَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ أَوۡثَٰنٗا وَتَخۡلُقُونَ إِفۡكًاۚ إِنَّ ٱلَّذِينَ تَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ لَا يَمۡلِكُونَ لَكُمۡ رِزۡقٗا فَٱبۡتَغُواْ عِندَ ٱللَّهِ ٱلرِّزۡقَ وَٱعۡبُدُوهُ وَٱشۡكُرُواْ لَهُۥٓۖ إِلَيۡهِ تُرۡجَعُونَ
17. (ሰዎች ሆይ!) ከአላህ ሌላ የምትገዙት ጣኦታትን ብቻ ነው:: ውሸትንም ትቀጥፋላችሁ:: እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትገዟቸው ጣዖታት ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም:: ስለዚህ ሲሳይን ከአላህ ዘንድ ብቻ ፈልጉ:: ተገዙትም:: ለርሱም አመስግኑ ወደ እርሱም ትመለሳላችሁ::
Faccirooji aarabeeji:
وَإِن تُكَذِّبُواْ فَقَدۡ كَذَّبَ أُمَمٞ مِّن قَبۡلِكُمۡۖ وَمَا عَلَى ٱلرَّسُولِ إِلَّا ٱلۡبَلَٰغُ ٱلۡمُبِينُ
18. ብታስተባብሉም ከፊታችሁ የነበሩት ህዝቦች በእርግጥ አስተባብለዋል:: በመልዕክተኛዉም ላይ ግልጽ ማድረስ እንጂ ሌላ የለበትም::
Faccirooji aarabeeji:
أَوَلَمۡ يَرَوۡاْ كَيۡفَ يُبۡدِئُ ٱللَّهُ ٱلۡخَلۡقَ ثُمَّ يُعِيدُهُۥٓۚ إِنَّ ذَٰلِكَ عَلَى ٱللَّهِ يَسِيرٞ
19. አላህ መፍጠርን እንዴት እንደሚጀምርና ከዚያ እንዴት እንደሚመልሰው አይመለከቱምን? ይህ በአላህ ላይ ቀላል ነው::
Faccirooji aarabeeji:
قُلۡ سِيرُواْ فِي ٱلۡأَرۡضِ فَٱنظُرُواْ كَيۡفَ بَدَأَ ٱلۡخَلۡقَۚ ثُمَّ ٱللَّهُ يُنشِئُ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأٓخِرَةَۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيۡءٖ قَدِيرٞ
20. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «በምድር ላይ ሂዱ:: እናም መፍጠርን እንዴት እንደጀመረ ተመልከቱ:: ከዚያም አላህ የመጨረሻይቱን መነሳት ያስነሳል:: አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና።» በላቸው::
Faccirooji aarabeeji:
يُعَذِّبُ مَن يَشَآءُ وَيَرۡحَمُ مَن يَشَآءُۖ وَإِلَيۡهِ تُقۡلَبُونَ
21. የሚሻውን ሰው ይቀጣል:: የሚሻውንም ሰው ያዝንለታል ወደ እርሱም ትመለሳላችሁ::
Faccirooji aarabeeji:
وَمَآ أَنتُم بِمُعۡجِزِينَ فِي ٱلۡأَرۡضِ وَلَا فِي ٱلسَّمَآءِۖ وَمَا لَكُم مِّن دُونِ ٱللَّهِ مِن وَلِيّٖ وَلَا نَصِيرٖ
22. እናንተ በምድርም ሆነ በሰማይ የምታቅቱ አይደላችሁም። ከአላህም ሌላ ወዳጅም ተከላካይም ምንም የላችሁም።
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلَّذِينَ كَفَرُواْ بِـَٔايَٰتِ ٱللَّهِ وَلِقَآئِهِۦٓ أُوْلَٰٓئِكَ يَئِسُواْ مِن رَّحۡمَتِي وَأُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ عَذَابٌ أَلِيمٞ
23. እነዚያም በአላህ አናቅጽና በመገናኘቱ የካዱ እነዚያ ከእዝነቴ ተስፋን ቆረጡ:: እነዚያም ለእነርሱ አሳማሚ ቅጣት አለባቸው::
Faccirooji aarabeeji:
فَمَا كَانَ جَوَابَ قَوۡمِهِۦٓ إِلَّآ أَن قَالُواْ ٱقۡتُلُوهُ أَوۡ حَرِّقُوهُ فَأَنجَىٰهُ ٱللَّهُ مِنَ ٱلنَّارِۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَٰتٖ لِّقَوۡمٖ يُؤۡمِنُونَ
24. የህዝቦቹም መልስ፡- «ግደሉት ወይም አቃጥሉት።» ማለት እንጂ ሌላ አልነበረም። ከዚያም ከእሳቲቱ አላህ አዳነው። በዚህ ውስጥ ለሚያምኑ ሕዝቦች ብዙ ተዐምራት አሉበት።
Faccirooji aarabeeji:
وَقَالَ إِنَّمَا ٱتَّخَذۡتُم مِّن دُونِ ٱللَّهِ أَوۡثَٰنٗا مَّوَدَّةَ بَيۡنِكُمۡ فِي ٱلۡحَيَوٰةِ ٱلدُّنۡيَاۖ ثُمَّ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ يَكۡفُرُ بَعۡضُكُم بِبَعۡضٖ وَيَلۡعَنُ بَعۡضُكُم بَعۡضٗا وَمَأۡوَىٰكُمُ ٱلنَّارُ وَمَا لَكُم مِّن نَّٰصِرِينَ
25. (ኢብራሂም) አለ፡- «ከአላህ ሌላ ጣኦታትን አማልክት የያዛችሁት በቅርቢቱ ህይወት በመካከላችሁ ለመዋደድ ብቻ ነው። ከዚያም በትንሳኤ ቀን ከፊላችሁ በከፊሉ ይክዳል:: ከፊላችሁም ከፊሉን ይረግማል:: መኖሪያችሁም እሳት ናት:: ለእናንተም ከረዳቶች ምንም የላችሁም።»
Faccirooji aarabeeji:
۞ فَـَٔامَنَ لَهُۥ لُوطٞۘ وَقَالَ إِنِّي مُهَاجِرٌ إِلَىٰ رَبِّيٓۖ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡحَكِيمُ
26. ከዚያም ሉጥ ለእርሱ አመነ:: (ኢብራሂምም) «እኔ ወደ ጌታዬ ተሰዳጅ ነኝ:: እነሆ እርሱ አላህ ሁሉን አሸናፊና ጥበበኛ ነውና።» አለ።
Faccirooji aarabeeji:
وَوَهَبۡنَا لَهُۥٓ إِسۡحَٰقَ وَيَعۡقُوبَ وَجَعَلۡنَا فِي ذُرِّيَّتِهِ ٱلنُّبُوَّةَ وَٱلۡكِتَٰبَ وَءَاتَيۡنَٰهُ أَجۡرَهُۥ فِي ٱلدُّنۡيَاۖ وَإِنَّهُۥ فِي ٱلۡأٓخِرَةِ لَمِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
27. ለእርሱም ኢስሐቅንና ያዕቆብን ሰጠነው በዘሩም ውስጥ ነብይነትንና መጽሐፍን አደረግን:: ምንዳውንም በቅርቢቱ ዓለም ሰጠነው:: እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከደጋጎቹ ነው::
Faccirooji aarabeeji:
وَلُوطًا إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ إِنَّكُمۡ لَتَأۡتُونَ ٱلۡفَٰحِشَةَ مَا سَبَقَكُم بِهَا مِنۡ أَحَدٖ مِّنَ ٱلۡعَٰلَمِينَ
28. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሉጥንም ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ አስታውስ: «እናንተ ጠያፍን ሥራ ትሰራላችሁን? በእርሷ ከዓለማት አንድም ሰው አልቀደማችሁም።
Faccirooji aarabeeji:
أَئِنَّكُمۡ لَتَأۡتُونَ ٱلرِّجَالَ وَتَقۡطَعُونَ ٱلسَّبِيلَ وَتَأۡتُونَ فِي نَادِيكُمُ ٱلۡمُنكَرَۖ فَمَا كَانَ جَوَابَ قَوۡمِهِۦٓ إِلَّآ أَن قَالُواْ ٱئۡتِنَا بِعَذَابِ ٱللَّهِ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
29. «እናንተ በእርግጥ ወንዶችን ትመጣላችሁን? መንገድንም ትቆርጣላችሁን? በሸንጓችሁም የሚነወርን ነገር ትሠራላችሁን?» አላቸው:: የሕዝቦቹም መልስ «ከእውነተኞቹ እንደሆንክ የአላህን ቅጣት አምጣብን።» ማለት እንጂ ሌላ አልነበረም።
Faccirooji aarabeeji:
قَالَ رَبِّ ٱنصُرۡنِي عَلَى ٱلۡقَوۡمِ ٱلۡمُفۡسِدِينَ
30. «ጌታዬ ሆይ! በአመጸኞች ሕዝቦች ላይ እርዳኝ።» አለ::
Faccirooji aarabeeji:
وَلَمَّا جَآءَتۡ رُسُلُنَآ إِبۡرَٰهِيمَ بِٱلۡبُشۡرَىٰ قَالُوٓاْ إِنَّا مُهۡلِكُوٓاْ أَهۡلِ هَٰذِهِ ٱلۡقَرۡيَةِۖ إِنَّ أَهۡلَهَا كَانُواْ ظَٰلِمِينَ
31. መልዕክተኞቻችንም ወደ ኢብራሂም በብስራት በመጡ ጊዜ «እኛ የዚችን ከተማ ሰዎች አጥፊዎች ነን ሰዎችዋ በዳዮች ነበሩና።» አሉት።
Faccirooji aarabeeji:
قَالَ إِنَّ فِيهَا لُوطٗاۚ قَالُواْ نَحۡنُ أَعۡلَمُ بِمَن فِيهَاۖ لَنُنَجِّيَنَّهُۥ وَأَهۡلَهُۥٓ إِلَّا ٱمۡرَأَتَهُۥ كَانَتۡ مِنَ ٱلۡغَٰبِرِينَ
32. «በእርሷ ውስጥ ሉጥ አለ እኮ?» አላቸው:: «እኛ በውስጧ ያለውን ካንተ ይበልጥ አዋቂ ነን:: እርሱንማ በእርግጥ እናድነዋለን:: ቤተሰቦቹንም ጭምር ሚስቱ ብቻ ስትቀር እርሷ በጥፋቱ ውስጥ ከሚቀሩት ናት።» አሉት::
Faccirooji aarabeeji:
وَلَمَّآ أَن جَآءَتۡ رُسُلُنَا لُوطٗا سِيٓءَ بِهِمۡ وَضَاقَ بِهِمۡ ذَرۡعٗاۖ وَقَالُواْ لَا تَخَفۡ وَلَا تَحۡزَنۡ إِنَّا مُنَجُّوكَ وَأَهۡلَكَ إِلَّا ٱمۡرَأَتَكَ كَانَتۡ مِنَ ٱلۡغَٰبِرِينَ
33. መልዕክተኞቻችንም ወደ ሉጥ በመጡት ጊዜ በነሱ ምክንያት አዘነ:: በእነርሱም ልቡ ተጨነቀ። አሉትም: «አትፍራ። አትዘንም። እኛ አዳኞችህ ነን:: ቤተሰቦችህንም ሚስትህ ብቻ ስትቀር:: እርሷ ግን በጥፋቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ ናት።
Faccirooji aarabeeji:
إِنَّا مُنزِلُونَ عَلَىٰٓ أَهۡلِ هَٰذِهِ ٱلۡقَرۡيَةِ رِجۡزٗا مِّنَ ٱلسَّمَآءِ بِمَا كَانُواْ يَفۡسُقُونَ
34. «እኛ በዚህ ከተማ ሰዎች ላይ ያምጹ በነበሩበት ምክንያት ከሰማይ ቅጣትን አውራጆች ነን።» (አሉት)
Faccirooji aarabeeji:
وَلَقَد تَّرَكۡنَا مِنۡهَآ ءَايَةَۢ بَيِّنَةٗ لِّقَوۡمٖ يَعۡقِلُونَ
35. በእርግጥም ለሚያስቡ ሰዎች ሁሉ ከእርሷ ግልጽ ምልክትን ተውን (አስቀረን)::
Faccirooji aarabeeji:
وَإِلَىٰ مَدۡيَنَ أَخَاهُمۡ شُعَيۡبٗا فَقَالَ يَٰقَوۡمِ ٱعۡبُدُواْ ٱللَّهَ وَٱرۡجُواْ ٱلۡيَوۡمَ ٱلۡأٓخِرَ وَلَا تَعۡثَوۡاْ فِي ٱلۡأَرۡضِ مُفۡسِدِينَ
36. ወደ መድየንም ወንድማቸውን ሹዐይብን ላክን። «ህዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ:: የመጨረሻውንም ቀን ፍሩ:: በምድርም ውስጥ የምታጠፉ ሆናችሁ አታበላሹ።» አላቸው።
Faccirooji aarabeeji:
فَكَذَّبُوهُ فَأَخَذَتۡهُمُ ٱلرَّجۡفَةُ فَأَصۡبَحُواْ فِي دَارِهِمۡ جَٰثِمِينَ
37. እናም አስተባበሉትና የምድር መንቀጥቀጥ ያዘቻቸው፡፡ ባገራቸዉም ውስጥ ተንከፍረው አደሩ (አነጉ)።
Faccirooji aarabeeji:
وَعَادٗا وَثَمُودَاْ وَقَد تَّبَيَّنَ لَكُم مِّن مَّسَٰكِنِهِمۡۖ وَزَيَّنَ لَهُمُ ٱلشَّيۡطَٰنُ أَعۡمَٰلَهُمۡ فَصَدَّهُمۡ عَنِ ٱلسَّبِيلِ وَكَانُواْ مُسۡتَبۡصِرِينَ
38. ዓድንና ሠሙድንም አጠፋን:: የመኖሪያዎቻቸውን ፍርስራሾች በማየት መጥፋታቸው ለእናንተ በእውነት ተገለጠላችሁ:: ሰይጣንም ሥራዎቻቸውን ለእነርሱ ሸለመላቸው:: ከመንገድም አገዳቸው:: የማስተዋልም ባለቤቶች ነበሩ:: ግን አላስተዋሉም::
Faccirooji aarabeeji:
وَقَٰرُونَ وَفِرۡعَوۡنَ وَهَٰمَٰنَۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مُّوسَىٰ بِٱلۡبَيِّنَٰتِ فَٱسۡتَكۡبَرُواْ فِي ٱلۡأَرۡضِ وَمَا كَانُواْ سَٰبِقِينَ
39. ቃሩንንም ፈርዖንንም ሃማንንም አጠፋን:: ሙሳም በተዐምራት በእርግጥ መጣባቸው:: በምድርም ላይ ኮሩ:: አምላጮችም አልነበሩም::
Faccirooji aarabeeji:
فَكُلًّا أَخَذۡنَا بِذَنۢبِهِۦۖ فَمِنۡهُم مَّنۡ أَرۡسَلۡنَا عَلَيۡهِ حَاصِبٗا وَمِنۡهُم مَّنۡ أَخَذَتۡهُ ٱلصَّيۡحَةُ وَمِنۡهُم مَّنۡ خَسَفۡنَا بِهِ ٱلۡأَرۡضَ وَمِنۡهُم مَّنۡ أَغۡرَقۡنَاۚ وَمَا كَانَ ٱللَّهُ لِيَظۡلِمَهُمۡ وَلَٰكِن كَانُوٓاْ أَنفُسَهُمۡ يَظۡلِمُونَ
40. ሁሉንም በኃጢአቱ ያዝነው:: ከእነርሱም ውስጥ ጠጠርን ያዘለ ነፍስን የላክንበት አለ:: ከእነርሱም ውስጥ ጩኸት የያዘችው አለ:: ከእነርሱም ውስጥ በእርሱ ምድርን የደረባንበት አለ:: ከእነርሱም ውስጥ ያሰመጥነው አለ:: አላህ የሚበድላቸው አልነበረም:: ግን ነፍሶቻቸውን የሚበድሉ ነበሩ::
Faccirooji aarabeeji:
مَثَلُ ٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِ ٱللَّهِ أَوۡلِيَآءَ كَمَثَلِ ٱلۡعَنكَبُوتِ ٱتَّخَذَتۡ بَيۡتٗاۖ وَإِنَّ أَوۡهَنَ ٱلۡبُيُوتِ لَبَيۡتُ ٱلۡعَنكَبُوتِۚ لَوۡ كَانُواْ يَعۡلَمُونَ
41. የእነዚያ ከአላህ ሌላ ረዳቶችን (ጣኦታትን) የያዙ ሰዎች ምሳሌ ቤትን እንደሠራች ሸረሪት ብጤ ነው:: ከቤቶችም ሁሉ በጣም ደካማው የሸረሪት ቤት ነው:: ቢያውቁ ኖሮ አማልክት አድርገው አይገዟቸዉም ነበር::
Faccirooji aarabeeji:
إِنَّ ٱللَّهَ يَعۡلَمُ مَا يَدۡعُونَ مِن دُونِهِۦ مِن شَيۡءٖۚ وَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡحَكِيمُ
42. አላህ ያንን ከእርሱ ሌላ የሚገዙትን ማንኛውንም ያውቃል:: እርሱም ሁሉን አሸናፊዉና ጥበበኛው ነው::
Faccirooji aarabeeji:
وَتِلۡكَ ٱلۡأَمۡثَٰلُ نَضۡرِبُهَا لِلنَّاسِۖ وَمَا يَعۡقِلُهَآ إِلَّا ٱلۡعَٰلِمُونَ
43. እነዚህንም ምሳሌዎች ለሰዎች እንገልጻቸዋለን:: ከሊቃውንቶቹም በስተቀር ሌሎችአያውቋትም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
خَلَقَ ٱللَّهُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ بِٱلۡحَقِّۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗ لِّلۡمُؤۡمِنِينَ
44. አላህም ሰማያትንና ምድርን እውነተኛ ሆኖ ፈጠረ፤ በዚህ ውስጥ ለአማኞች ተዐምር አለበት።
Faccirooji aarabeeji:
ٱتۡلُ مَآ أُوحِيَ إِلَيۡكَ مِنَ ٱلۡكِتَٰبِ وَأَقِمِ ٱلصَّلَوٰةَۖ إِنَّ ٱلصَّلَوٰةَ تَنۡهَىٰ عَنِ ٱلۡفَحۡشَآءِ وَٱلۡمُنكَرِۗ وَلَذِكۡرُ ٱللَّهِ أَكۡبَرُۗ وَٱللَّهُ يَعۡلَمُ مَا تَصۡنَعُونَ
45. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከመጽሐፉ ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ:: ሶላትንም ደንቡን ጠብቀህ ስገድ:: ሶላት ከመጥፎና ከሚጠላ ነገር ሁሉ ትከለክላለችና:: አላህን ማውሳት ከመልካም ነገር ሁሉ በላጭ ነው:: አላህም የምትሠሩትን ስራ ሁሉ ያውቃል::
Faccirooji aarabeeji:
۞ وَلَا تُجَٰدِلُوٓاْ أَهۡلَ ٱلۡكِتَٰبِ إِلَّا بِٱلَّتِي هِيَ أَحۡسَنُ إِلَّا ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ مِنۡهُمۡۖ وَقُولُوٓاْ ءَامَنَّا بِٱلَّذِيٓ أُنزِلَ إِلَيۡنَا وَأُنزِلَ إِلَيۡكُمۡ وَإِلَٰهُنَا وَإِلَٰهُكُمۡ وَٰحِدٞ وَنَحۡنُ لَهُۥ مُسۡلِمُونَ
46. (እናንተ ያመናችሁ ሆይ!) ከእነርሱ እነዚያን የበደሉትን ሲቀር የመጽሐፉ ባለቤቶችን በዚያች እርሷ መልካም በሆነችው ክርክር እንጂ አትከራከሩ:። በሉም፡- «በዚያ ወደ እኛ በተወረደው ወደ እናንተም በተወረደው አመንን:: አምላካችንም አምላካችሁም አንድ ነው:: እኛም ለእርሱ ታዛዦች ነን።»
Faccirooji aarabeeji:
وَكَذَٰلِكَ أَنزَلۡنَآ إِلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَۚ فَٱلَّذِينَ ءَاتَيۡنَٰهُمُ ٱلۡكِتَٰبَ يُؤۡمِنُونَ بِهِۦۖ وَمِنۡ هَٰٓؤُلَآءِ مَن يُؤۡمِنُ بِهِۦۚ وَمَا يَجۡحَدُ بِـَٔايَٰتِنَآ إِلَّا ٱلۡكَٰفِرُونَ
47. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እንደዚሁም ወደ አንተ መጽሐፍን አወረድን:: እነዚያም መጽሐፍን የሰጠናቸው በእርሱ ያምናሉ:: ከእነዚህም (ከመካ) ሰዎች በእርሱ የሚያምኑ አሉ:: በተዓምራታችንም ከሓዲያን እንጂ ማንም አይክድም::
Faccirooji aarabeeji:
وَمَا كُنتَ تَتۡلُواْ مِن قَبۡلِهِۦ مِن كِتَٰبٖ وَلَا تَخُطُّهُۥ بِيَمِينِكَۖ إِذٗا لَّٱرۡتَابَ ٱلۡمُبۡطِلُونَ
48. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእርሱ በፊትም መጽሐፍን የምታነብ በቀኝህም የምትጽፈው አልነበርክም:: ያን ጊዜ አጥፊዎቹ በእርግጥ በተጠራጠሩ ነበር::
Faccirooji aarabeeji:
بَلۡ هُوَ ءَايَٰتُۢ بَيِّنَٰتٞ فِي صُدُورِ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡعِلۡمَۚ وَمَا يَجۡحَدُ بِـَٔايَٰتِنَآ إِلَّا ٱلظَّٰلِمُونَ
49. አይደለም:: እርሱ (ቁርኣን) በእነዚያ እውቀትን በተሰጡት ሰዎች ልቦች ውስጥ የጠለቀ ግልፆች አናቅጽ ነው:: በአናቅጻችንም በዳዮቹ እንጂ ሌላው አይክድም::
Faccirooji aarabeeji:
وَقَالُواْ لَوۡلَآ أُنزِلَ عَلَيۡهِ ءَايَٰتٞ مِّن رَّبِّهِۦۚ قُلۡ إِنَّمَا ٱلۡأٓيَٰتُ عِندَ ٱللَّهِ وَإِنَّمَآ أَنَا۠ نَذِيرٞ مُّبِينٌ
50. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያን «በእርሱ ላይ ከጌታው ዘንድ ተዐምራት ለምን አልተወረዱም?» አሉ:: »ተዐምራት ከአላህ ዘንድ ብቻ ናቸው:: እኔም ግልጽ አስፈራሪ ብቻ ነኝ።» በላቸው::
Faccirooji aarabeeji:
أَوَلَمۡ يَكۡفِهِمۡ أَنَّآ أَنزَلۡنَا عَلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ يُتۡلَىٰ عَلَيۡهِمۡۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَرَحۡمَةٗ وَذِكۡرَىٰ لِقَوۡمٖ يُؤۡمِنُونَ
51. እኛ መጽሐፉን በእነርሱ ላይ የሚነበብ ሆኖ ባንተ ላይ ማውረዳችን አይበቃቸዉምን? በዚህ ውስጥ ለሚያምኑ ሕዝቦች ሁሉ ችሮታና ግሳጼ አለበት::
Faccirooji aarabeeji:
قُلۡ كَفَىٰ بِٱللَّهِ بَيۡنِي وَبَيۡنَكُمۡ شَهِيدٗاۖ يَعۡلَمُ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۗ وَٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ بِٱلۡبَٰطِلِ وَكَفَرُواْ بِٱللَّهِ أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡخَٰسِرُونَ
52. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «በእኔና በእናንተ መካከል መስካሪ በአላህ በቃ:: በሰማያትና በምድር ያለውን ሁሉ ያውቃል።» በላቸው:: እነዚያም በብላሽ ነገር ያመኑና በአላህ የካዱ እነዚያ እነርሱ ከሳሪዎቹ ናቸው።
Faccirooji aarabeeji:
وَيَسۡتَعۡجِلُونَكَ بِٱلۡعَذَابِ وَلَوۡلَآ أَجَلٞ مُّسَمّٗى لَّجَآءَهُمُ ٱلۡعَذَابُۚ وَلَيَأۡتِيَنَّهُم بَغۡتَةٗ وَهُمۡ لَا يَشۡعُرُونَ
53. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በቅጣትም ያስቸኩሉሃል! የተወሰነም ጊዜ ባልነበረ ኖሮ ቅጣቱ በመጣባቸው ነበር:: እነርሱ የማያውቁ ሲሆኑም በድንገት በእርግጥ ይመጣባቸዋል::
Faccirooji aarabeeji:
يَسۡتَعۡجِلُونَكَ بِٱلۡعَذَابِ وَإِنَّ جَهَنَّمَ لَمُحِيطَةُۢ بِٱلۡكَٰفِرِينَ
54. በቅጣት ያስቸኩሉሃል! ገሀነምም ከሓዲያንን በእርግጥ ከባቢ ናት::
Faccirooji aarabeeji:
يَوۡمَ يَغۡشَىٰهُمُ ٱلۡعَذَابُ مِن فَوۡقِهِمۡ وَمِن تَحۡتِ أَرۡجُلِهِمۡ وَيَقُولُ ذُوقُواْ مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
55. ቅጣቱ ከበላያቸው ከእግሮቻቸዉም ሥር በሚሸፍናቸው ቀን «ትሰሩት የነበራችሁትን ቅመሱ።» በሚላቸዉም ቀን ትከባቸዋለች።
Faccirooji aarabeeji:
يَٰعِبَادِيَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِنَّ أَرۡضِي وَٰسِعَةٞ فَإِيَّٰيَ فَٱعۡبُدُونِ
56. እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት:: ብትቸገሩ ተሰደዱ እኔንም ብቻ ተገዙኝ::
Faccirooji aarabeeji:
كُلُّ نَفۡسٖ ذَآئِقَةُ ٱلۡمَوۡتِۖ ثُمَّ إِلَيۡنَا تُرۡجَعُونَ
57. ነፍስ ሁሉ ሞትን ቀማሽ ናት:: ከዚያም ወደ እኛ ትመለሳላችሁ::
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَنُبَوِّئَنَّهُم مِّنَ ٱلۡجَنَّةِ غُرَفٗا تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَاۚ نِعۡمَ أَجۡرُ ٱلۡعَٰمِلِينَ
58. እነዚያም በአላህ ያመኑና መልካም ስራዎችን የሠሩ ከገነት በስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ሰገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲሆኑ በእርግጥ እናሰፍራቸዋለን:: የሠራተኞችም ምንዳ ምንኛ አማረ!
Faccirooji aarabeeji:
ٱلَّذِينَ صَبَرُواْ وَعَلَىٰ رَبِّهِمۡ يَتَوَكَّلُونَ
59. እነርሱ እነዚያ የታገሱ በጌታቸዉም ላይ የሚመኩ ናቸው፡
Faccirooji aarabeeji:
وَكَأَيِّن مِّن دَآبَّةٖ لَّا تَحۡمِلُ رِزۡقَهَا ٱللَّهُ يَرۡزُقُهَا وَإِيَّاكُمۡۚ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ
60. ከተንቀሳቃሽ ፍጡራን ምግባቸውን የማይሸከሙ ብዙ ናቸው:: አላህ ይመግባቸዋል:: እናንተንም ይመግባል:: እርሱ ሰሚና አዋቂ ነውና::
Faccirooji aarabeeji:
وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَسَخَّرَ ٱلشَّمۡسَ وَٱلۡقَمَرَ لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۖ فَأَنَّىٰ يُؤۡفَكُونَ
61. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ ጸሐይንና ጨረቃንም የገራ ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው በእርግጥ ”አላህ ነው“ ይሉሃል:: ታዲያ እንዴት ይመለሳሉ።
Faccirooji aarabeeji:
ٱللَّهُ يَبۡسُطُ ٱلرِّزۡقَ لِمَن يَشَآءُ مِنۡ عِبَادِهِۦ وَيَقۡدِرُ لَهُۥٓۚ إِنَّ ٱللَّهَ بِكُلِّ شَيۡءٍ عَلِيمٞ
62. አላህ ከባሮቹ ለሚሻው ሲሳይን ያሰፋል:: ለእርሱም ያጠባል:: አላህ በነገሩ ሁሉ አዋቂ ነውና::
Faccirooji aarabeeji:
وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّن نَّزَّلَ مِنَ ٱلسَّمَآءِ مَآءٗ فَأَحۡيَا بِهِ ٱلۡأَرۡضَ مِنۢ بَعۡدِ مَوۡتِهَا لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُۚ قُلِ ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِۚ بَلۡ أَكۡثَرُهُمۡ لَا يَعۡقِلُونَ
63. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሰማይ ውሃን ያወረደና በእርሱም ምድርን ከሞተች በኋላ ሕያው ያደረጋት ማን እንደሆነ ብትጠይቃቸው "አላህ ነው" ይሉሃል:: "ስለዚህ ምስጋና ሁሉ ለአላህ ነው።“ በላቸው:: ግን አብዛኞቻቸው ይህን አያውቁም።
Faccirooji aarabeeji:
وَمَا هَٰذِهِ ٱلۡحَيَوٰةُ ٱلدُّنۡيَآ إِلَّا لَهۡوٞ وَلَعِبٞۚ وَإِنَّ ٱلدَّارَ ٱلۡأٓخِرَةَ لَهِيَ ٱلۡحَيَوَانُۚ لَوۡ كَانُواْ يَعۡلَمُونَ
64. ይህም የቅርቢቱ ሕይወት መታለያና ጨዋታ እንጂ ሌላ አይደለም:: የመጨረሻይቱም አገር እርሷ በእርግጥ የዘላለም ህይወት አገር ናት:: የሚያውቁ ቢሆኑ ኖሮ ጠፊይቱን ሕይወት አይመርጡም ነበር::
Faccirooji aarabeeji:
فَإِذَا رَكِبُواْ فِي ٱلۡفُلۡكِ دَعَوُاْ ٱللَّهَ مُخۡلِصِينَ لَهُ ٱلدِّينَ فَلَمَّا نَجَّىٰهُمۡ إِلَى ٱلۡبَرِّ إِذَا هُمۡ يُشۡرِكُونَ
65. በመርከቦች ውስጥ በተሳፈሩ ጊዜም አላህን መገዛትን ለእርሱ ብቻ ያጠሩ ሆነው ይጠሩታል:: ወደ የብስ በማውጣት ባዳናቸው ጊዜ ግን ወዲያውኑ እነርሱ ጣዖትን ያጋራሉ::
Faccirooji aarabeeji:
لِيَكۡفُرُواْ بِمَآ ءَاتَيۡنَٰهُمۡ وَلِيَتَمَتَّعُواْۚ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ
66. በሰጠናቸው ጸጋ ሊክዱና ሊጠቃቀሙ ያጋራሉ፤ ወደ ፊትም የሚጠብቃቸውን ያውቃሉ።
Faccirooji aarabeeji:
أَوَلَمۡ يَرَوۡاْ أَنَّا جَعَلۡنَا حَرَمًا ءَامِنٗا وَيُتَخَطَّفُ ٱلنَّاسُ مِنۡ حَوۡلِهِمۡۚ أَفَبِٱلۡبَٰطِلِ يُؤۡمِنُونَ وَبِنِعۡمَةِ ٱللَّهِ يَكۡفُرُونَ
67. ሰዎቹ ከየዙሪያቸው ሲነጠቁ እኛ አገራቸውን ጸጥተኛ ክልል ማድረጋችንን አያዩምን? በውድቅ ነገር ያምናሉን? በአላህም ጸጋ ይክዳሉን?
Faccirooji aarabeeji:
وَمَنۡ أَظۡلَمُ مِمَّنِ ٱفۡتَرَىٰ عَلَى ٱللَّهِ كَذِبًا أَوۡ كَذَّبَ بِٱلۡحَقِّ لَمَّا جَآءَهُۥٓۚ أَلَيۡسَ فِي جَهَنَّمَ مَثۡوٗى لِّلۡكَٰفِرِينَ
68. በአላህ ላይ ውሸትን ከቀጣጠፈ ሰው ወይም እውነት በመጣለት ጊዜ ከአስዋሸ ሰው ይበልጥ ራሱን በዳይ ማነው? በገሀነም ውስጥ ለከሓዲያን መኖሪያ የለምን?(አለ)
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلَّذِينَ جَٰهَدُواْ فِينَا لَنَهۡدِيَنَّهُمۡ سُبُلَنَاۚ وَإِنَّ ٱللَّهَ لَمَعَ ٱلۡمُحۡسِنِينَ
69. እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ ህዝቦችን መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን:: አላህ በእርግጥ ከበጎ ሰሪዎች ጋር ነውና፡:
Faccirooji aarabeeji:
 
Firo maanaaji Simoore: Simooee njomolaaji
Tippudi cimooje Tonngoode hello ngoo
 
Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Eggo Amhariiwo - Akademii Afrik - Tippudi firooji ɗii

Eggo mum - Muhammad Zain Zahr al-Din. E haala Akademii Afrik.

Uddude