Check out the new design

Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Eggo Amhariiwo - Akademii Afrik * - Tippudi firooji ɗii


Firo maanaaji Simoore: Simoore Al-ahkaaf   Aaya:
وَإِذَا حُشِرَ ٱلنَّاسُ كَانُواْ لَهُمۡ أَعۡدَآءٗ وَكَانُواْ بِعِبَادَتِهِمۡ كَٰفِرِينَ
6. ሰዎችም በተሰበሰቡ ጊዜ ጣኦቶቹ ለእነርሱ ጠላቶች ይሆናሉ:: እነርሱን መገዛታቸውንም ይክዳሉ::
Faccirooji aarabeeji:
وَإِذَا تُتۡلَىٰ عَلَيۡهِمۡ ءَايَٰتُنَا بَيِّنَٰتٖ قَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لِلۡحَقِّ لَمَّا جَآءَهُمۡ هَٰذَا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
7. በእነርሱም ላይ አንቀፆቻችን ግልፆች ሆነው በተነበቡ ጊዜ እነዚያ እውነቱ በመጣላቸው ጊዜ የካዱት ክፍሎች «ይህ ግልጽ ድግምት ነው» አሉ።
Faccirooji aarabeeji:
أَمۡ يَقُولُونَ ٱفۡتَرَىٰهُۖ قُلۡ إِنِ ٱفۡتَرَيۡتُهُۥ فَلَا تَمۡلِكُونَ لِي مِنَ ٱللَّهِ شَيۡـًٔاۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَا تُفِيضُونَ فِيهِۚ كَفَىٰ بِهِۦ شَهِيدَۢا بَيۡنِي وَبَيۡنَكُمۡۖ وَهُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلرَّحِيمُ
8. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይልቁንም «(ሙሐመድ ራሱ) ቀጠፈው» ይላሉን? «ብቀጥፈው ኖሮ እኔን ከአላህ ቅጣት ለማዳን በምንም አትችሉም:: እርሱ ያንን የምትቀባዥሩበትን ነገር ሁሉ አዋቂ ነው:: በእኔና በእናንተ መካከል መስካሪነት እሱው በቃ:: እርሱ መሀሪ እና አዛኝ ነውና» በላቸው።
Faccirooji aarabeeji:
قُلۡ مَا كُنتُ بِدۡعٗا مِّنَ ٱلرُّسُلِ وَمَآ أَدۡرِي مَا يُفۡعَلُ بِي وَلَا بِكُمۡۖ إِنۡ أَتَّبِعُ إِلَّا مَا يُوحَىٰٓ إِلَيَّ وَمَآ أَنَا۠ إِلَّا نَذِيرٞ مُّبِينٞ
9. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከመልዕክተኞች የተለየሁ ብጤ የሌለኝ አይደለሁም:: በእኔም በእናንተም ላይ ምን እንደሚሰራብንም አላውቅም:: ወደ እኔ የሚወረደውን እንጂ ሌላን መመሪያ አልከተልም:: እኔም ግልጽ አስፈራሪ እንጂ ሌላ አይደለሁም» በላቸው::
Faccirooji aarabeeji:
قُلۡ أَرَءَيۡتُمۡ إِن كَانَ مِنۡ عِندِ ٱللَّهِ وَكَفَرۡتُم بِهِۦ وَشَهِدَ شَاهِدٞ مِّنۢ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ عَلَىٰ مِثۡلِهِۦ فَـَٔامَنَ وَٱسۡتَكۡبَرۡتُمۡۚ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي ٱلۡقَوۡمَ ٱلظَّٰلِمِينَ
10. «(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እስቲ ንገሩኝ ቁርኣኑ ከአላህ ዘንድ ቢሆንና በእርሱ ብትክዱ ከኢስራኢል ልጆች የሆነ መስካሪ ደግሞ በቢጤው ቢያምንና በእርሱ ላይ ቢመሰክር እናንተ (ግን) ብትኮሩ (በዳይ አትሆኑምን)? አላህ በእርግጥ በደለኛ ህዝቦችን ሁሉ አያቀናም» በላቸው።
Faccirooji aarabeeji:
وَقَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لِلَّذِينَ ءَامَنُواْ لَوۡ كَانَ خَيۡرٗا مَّا سَبَقُونَآ إِلَيۡهِۚ وَإِذۡ لَمۡ يَهۡتَدُواْ بِهِۦ فَسَيَقُولُونَ هَٰذَآ إِفۡكٞ قَدِيمٞ
11. እነዚያም የካዱት ሰዎች ስላመኑት ሰዎች «እምነቱ መልካም ነገር በሆነ ኖሮ ወደ እርሱ ባልቀደሙን ነበር» አሉ:: በእርሱም ባልተቀኑ ጊዜ «ይህ ቁርኣን ጥንታዊ ቅጥፈት ነው» ይላሉ::
Faccirooji aarabeeji:
وَمِن قَبۡلِهِۦ كِتَٰبُ مُوسَىٰٓ إِمَامٗا وَرَحۡمَةٗۚ وَهَٰذَا كِتَٰبٞ مُّصَدِّقٞ لِّسَانًا عَرَبِيّٗا لِّيُنذِرَ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَبُشۡرَىٰ لِلۡمُحۡسِنِينَ
12. ከፊቱም የሙሳን መጽሐፍ ለሰዎች መሪና የአላህ ጸጋ ሲሆን እንዳወረድን አላየህምን? ይህ ቁርኣን እነዚያን የበደሉትን ሊያስፈራራ በዐረብኛ ቋንቋ የወረደ ሲሆን የፊቶቹንም መጽሐፍት አረጋጋጭ እና ለበጎ አድራጊዎችም ሁሉ የብስራት መጽሐፍ ነው::
Faccirooji aarabeeji:
إِنَّ ٱلَّذِينَ قَالُواْ رَبُّنَا ٱللَّهُ ثُمَّ ٱسۡتَقَٰمُواْ فَلَا خَوۡفٌ عَلَيۡهِمۡ وَلَا هُمۡ يَحۡزَنُونَ
13. «እነዚያ ጌታችን አላህ ነው» ያሉና ከዚያም በዚሁ ቃላቸው ላይ ቀጥ ያሉ ሰዎች ሁሉ በእነርሱ ላይ ምንም (ይደርስብናል ብለው) ፍርሀት የለባቸዉም:: ምንም (ነገር ያመልጠናል ብለው) አያዝኑምም::
Faccirooji aarabeeji:
أُوْلَٰٓئِكَ أَصۡحَٰبُ ٱلۡجَنَّةِ خَٰلِدِينَ فِيهَا جَزَآءَۢ بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
14. እነዚያ የገነት ጓዶች ናቸው:: በእርሷ ውስጥ ዘወታሪዎች ሲሆኑ በዚያ በዱንያ ይሰሩት በነበሩት መልካም ተግባር ምክንያት ያገኙት ምንዳ ነው።
Faccirooji aarabeeji:
 
Firo maanaaji Simoore: Simoore Al-ahkaaf
Tippudi cimooje Tonngoode hello ngoo
 
Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Eggo Amhariiwo - Akademii Afrik - Tippudi firooji ɗii

Eggo mum - Muhammad Zain Zahr al-Din. E haala Akademii Afrik.

Uddude