કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - એમ્હારિક ભાષાંતર - ઝૈન * - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા


શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: અન્ નાઝિઆત   આયત:

ሱረቱ አን ናዚዓት

وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا
1. (ነፍስን (ሩህን)) በኃይል መንጫቂዎች በሆኑት፤
અરબી તફસીરો:
وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا
2. በቀስታ መምዘዝን መዛዦች በሆኑትም፤
અરબી તફસીરો:
وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا
3. መዋኘትንም ዋኚዎች በሆኑት፤
અરબી તફસીરો:
فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا
4. መቅደምንም ቀዳሚዎች በሆኑት፤
અરબી તફસીરો:
فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا
5. ጉዳይንም አስተናባሪዎች በሆኑት መላዕክት እምላለሁ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)።
અરબી તફસીરો:
يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ
6. (ይህም የሚሆነው) ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤
અરબી તફસીરો:
تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ
7. ተከታይቱም በምትከተላት ቀን (ትቀሰቀሳላችሁ)።
અરબી તફસીરો:
قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ
8. በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው::
અરબી તફસીરો:
أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ
9. ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው።
અરબી તફસીરો:
يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ
10. «እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ሁኔታ ተመላሾች ነን እንዴ?» ይላሉ።
અરબી તફસીરો:
أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ
11. የበሰበሱ አጥንቶች በሆንን ጊዜ እንደገና እንቀሰቀሳለን?
અરબી તફસીરો:
قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ
12. «እንዲያማ ከሆነ ያች የኪሳራ መመለስ ናታ!» ይላሉ።
અરબી તફસીરો:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ
13. እርሷን (እውን የምታደርጋት) አንዲት ጩኸት ብቻ ናት።
અરબી તફસીરો:
فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ
14. ወዲያውኑ በንቃት ላይ ናቸው።
અરબી તફસીરો:
هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
15. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሙሳ ወሬ መጣልህን?
અરબી તફસીરો:
إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى
16. ጌታው በተቀደሰው ጡዋ ሸለቆ በጠራው ጊዜ፤
અરબી તફસીરો:
ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
17. ወደ ፈርዖን ሂድ፤ ወሰን አልፏልና::
અરબી તફસીરો:
فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ
18. (እንዲህም) በለው: «እራስህን ለማጥራት ታስባለህን?
અરબી તફસીરો:
وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ
19. ጌታህንም ትፈራ ዘንድ መንገዱን ልመራህ፤ (ታስባለህን?)»
અરબી તફસીરો:
فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
20. (ሙሳ ለፈርዖን) ታላቁንም ተዐምር አሳየው።
અરબી તફસીરો:
فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
21. አስተባበለም፤ አመጸም፤
અરબી તફસીરો:
ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ
22. ከዚያ ለመጥፋት የሚተጋ ሆኖ ዞረ::
અરબી તફસીરો:
فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
23. (ህዝቡን) ሰበሰበም ተጣራም።
અરબી તફસીરો:
فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ
24. እኔ «ታላቁ ጌታችሁ ነኝ» አለም።
અરબી તફસીરો:
فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ
25. አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ ቃል ቅጣት ያዘው::
અરબી તફસીરો:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ
26. በዚህ ውስጥ አላህን ለሚፈሩ በእርግጥ ማስጠንቀቂያ አለበት።
અરબી તફસીરો:
ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا
27. በአፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት::
અરબી તફસીરો:
رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا
28. ከፍታዋን አጓነ አስተካከላትም።
અરબી તફસીરો:
وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا
29. ሌሊቷንም ሸፈነ፤ ቀኗንም ግልጽ አደረገ።
અરબી તફસીરો:
وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ
30. ምድርንም ከዚያ በኋላ ዘረጋት።
અરબી તફસીરો:
أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا
31. ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ::
અરબી તફસીરો:
وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا
32. ጋራዎችንም አደላደላቸው።
અરબી તફસીરો:
مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
33. ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጣቀሚያ ይሆን ዘንድ (ይሄን አደረገ)።
અરબી તફસીરો:
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ
34. ታላቂቱም መዓት በመጣች ጊዜ፤
અરબી તફસીરો:
يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ
35. ሰው ሁሉ የሰራውን የሚያስታውስበት ቀን፤
અરબી તફસીરો:
وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
36. ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፤
અરબી તફસીરો:
فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
37. የካደ ሰውማ፤
અરબી તફસીરો:
وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
38. ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፤
અરબી તફસીરો:
فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
39. በእርግጥ መኖሪያው ጀሀነም ናት።
અરબી તફસીરો:
وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ
40. በጌታው ፊት መቆምን የፈራና ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለማ፤
અરબી તફસીરો:
فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
41. በእርግጥ መኖሪያው ገነት ናት።
અરબી તફસીરો:
يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا
42. ስለሰዓቲቱም መነሻዋ መቼ እንደሆነ ይጠይቁሃል።
અરબી તફસીરો:
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ
43. (ለመሆኑ አንተ ስለዚያች እለት) በመወሳቷ ምን ላይ አለህበትና?
અરબી તફસીરો:
إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ
44. የእርሷ ጉዳይ የሚመለሰው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::
અરબી તફસીરો:
إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا
45. አንተ ያለብህ ለሚፈራት ሰው ሁሉ ስለ እርሷ (ከወዲሁ) ማስጠንቀቅ ነው።
અરબી તફસીરો:
كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا
46. እነርሱ የሚያይዋት ቀን የአንዲትን ቀን ምሽት ወይም ረፋዷን እንጂ ያልቆዩ ይመስላሉ::
અરબી તફસીરો:
 
શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: અન્ નાઝિઆત
સૂરહ માટે અનુક્રમણિકા પેજ નંબર
 
કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - એમ્હારિક ભાષાંતર - ઝૈન - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા

અમ્હેરિક ભાષાતર

બંધ કરો