Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic * - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Al'waki'ah   Aya:

ሱረቱ አል ዋቂዓህ

إِذَا وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ
መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
لَيۡسَ لِوَقۡعَتِهَا كَاذِبَةٌ
ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
Tafsiran larabci:
خَافِضَةٞ رَّافِعَةٌ
ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
Tafsiran larabci:
إِذَا رُجَّتِ ٱلۡأَرۡضُ رَجّٗا
ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَبُسَّتِ ٱلۡجِبَالُ بَسّٗا
ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
Tafsiran larabci:
فَكَانَتۡ هَبَآءٗ مُّنۢبَثّٗا
የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
Tafsiran larabci:
وَكُنتُمۡ أَزۡوَٰجٗا ثَلَٰثَةٗ
ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
Tafsiran larabci:
فَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ
የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ
የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلسَّٰبِقُونَ
(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
أُوْلَٰٓئِكَ ٱلۡمُقَرَّبُونَ
እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
Tafsiran larabci:
ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَقَلِيلٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
عَلَىٰ سُرُرٖ مَّوۡضُونَةٖ
በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
Tafsiran larabci:
مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيۡهَا مُتَقَٰبِلِينَ
በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
Tafsiran larabci:
يَطُوفُ عَلَيۡهِمۡ وِلۡدَٰنٞ مُّخَلَّدُونَ
በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
Tafsiran larabci:
بِأَكۡوَابٖ وَأَبَارِيقَ وَكَأۡسٖ مِّن مَّعِينٖ
ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
لَّا يُصَدَّعُونَ عَنۡهَا وَلَا يُنزِفُونَ
ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
Tafsiran larabci:
وَفَٰكِهَةٖ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ
ከሚመርጡትም ዓይነት እሸቶች፡፡
Tafsiran larabci:
وَلَحۡمِ طَيۡرٖ مِّمَّا يَشۡتَهُونَ
ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
Tafsiran larabci:
وَحُورٌ عِينٞ
ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
Tafsiran larabci:
كَأَمۡثَٰلِ ٱللُّؤۡلُوِٕ ٱلۡمَكۡنُونِ
ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
Tafsiran larabci:
جَزَآءَۢ بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
Tafsiran larabci:
لَا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا تَأۡثِيمًا
በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
Tafsiran larabci:
إِلَّا قِيلٗا سَلَٰمٗا سَلَٰمٗا
ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ
የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
Tafsiran larabci:
فِي سِدۡرٖ مَّخۡضُودٖ
በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَطَلۡحٖ مَّنضُودٖ
(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
Tafsiran larabci:
وَظِلّٖ مَّمۡدُودٖ
በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
Tafsiran larabci:
وَمَآءٖ مَّسۡكُوبٖ
በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
Tafsiran larabci:
وَفَٰكِهَةٖ كَثِيرَةٖ
ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
Tafsiran larabci:
لَّا مَقۡطُوعَةٖ وَلَا مَمۡنُوعَةٖ
የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
Tafsiran larabci:
وَفُرُشٖ مَّرۡفُوعَةٍ
ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّآ أَنشَأۡنَٰهُنَّ إِنشَآءٗ
እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فَجَعَلۡنَٰهُنَّ أَبۡكَارًا
ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
عُرُبًا أَتۡرَابٗا
ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
Tafsiran larabci:
لِّأَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
Tafsiran larabci:
ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ
የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فِي سَمُومٖ وَحَمِيمٖ
በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَظِلّٖ مِّن يَحۡمُومٖ
ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
Tafsiran larabci:
لَّا بَارِدٖ وَلَا كَرِيمٍ
ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُتۡرَفِينَ
እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
Tafsiran larabci:
وَكَانُواْ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلۡحِنثِ ٱلۡعَظِيمِ
በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡
Tafsiran larabci:
وَكَانُواْ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
Tafsiran larabci:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
Tafsiran larabci:
قُلۡ إِنَّ ٱلۡأَوَّلِينَ وَٱلۡأٓخِرِينَ
በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
Tafsiran larabci:
لَمَجۡمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
ثُمَّ إِنَّكُمۡ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلۡمُكَذِّبُونَ
«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
Tafsiran larabci:
لَأٓكِلُونَ مِن شَجَرٖ مِّن زَقُّومٖ
« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
فَشَٰرِبُونَ عَلَيۡهِ مِنَ ٱلۡحَمِيمِ
«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
فَشَٰرِبُونَ شُرۡبَ ٱلۡهِيمِ
«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
Tafsiran larabci:
هَٰذَا نُزُلُهُمۡ يَوۡمَ ٱلدِّينِ
ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
Tafsiran larabci:
نَحۡنُ خَلَقۡنَٰكُمۡ فَلَوۡلَا تُصَدِّقُونَ
እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
Tafsiran larabci:
أَفَرَءَيۡتُم مَّا تُمۡنُونَ
(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
Tafsiran larabci:
ءَأَنتُمۡ تَخۡلُقُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡخَٰلِقُونَ
እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
Tafsiran larabci:
نَحۡنُ قَدَّرۡنَا بَيۡنَكُمُ ٱلۡمَوۡتَ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ
እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡
Tafsiran larabci:
عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ أَمۡثَٰلَكُمۡ وَنُنشِئَكُمۡ فِي مَا لَا تَعۡلَمُونَ
ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
Tafsiran larabci:
وَلَقَدۡ عَلِمۡتُمُ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُولَىٰ فَلَوۡلَا تَذَكَّرُونَ
የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
Tafsiran larabci:
أَفَرَءَيۡتُم مَّا تَحۡرُثُونَ
የምትዘሩትንም አያችሁን?
Tafsiran larabci:
ءَأَنتُمۡ تَزۡرَعُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلزَّٰرِعُونَ
እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
Tafsiran larabci:
لَوۡ نَشَآءُ لَجَعَلۡنَٰهُ حُطَٰمٗا فَظَلۡتُمۡ تَفَكَّهُونَ
ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّا لَمُغۡرَمُونَ
«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
Tafsiran larabci:
بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ
«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
Tafsiran larabci:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلۡمَآءَ ٱلَّذِي تَشۡرَبُونَ
ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
Tafsiran larabci:
ءَأَنتُمۡ أَنزَلۡتُمُوهُ مِنَ ٱلۡمُزۡنِ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنزِلُونَ
እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
Tafsiran larabci:
لَوۡ نَشَآءُ جَعَلۡنَٰهُ أُجَاجٗا فَلَوۡلَا تَشۡكُرُونَ
ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
Tafsiran larabci:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِي تُورُونَ
ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
Tafsiran larabci:
ءَأَنتُمۡ أَنشَأۡتُمۡ شَجَرَتَهَآ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنشِـُٔونَ
እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
Tafsiran larabci:
نَحۡنُ جَعَلۡنَٰهَا تَذۡكِرَةٗ وَمَتَٰعٗا لِّلۡمُقۡوِينَ
እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
Tafsiran larabci:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
Tafsiran larabci:
۞ فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ
በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
Tafsiran larabci:
وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوۡ تَعۡلَمُونَ عَظِيمٌ
እርሱም ብታወቁ ታላቅ መሓላ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّهُۥ لَقُرۡءَانٞ كَرِيمٞ
እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فِي كِتَٰبٖ مَّكۡنُونٖ
በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ
የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
Tafsiran larabci:
تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
أَفَبِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ أَنتُم مُّدۡهِنُونَ
በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
Tafsiran larabci:
وَتَجۡعَلُونَ رِزۡقَكُمۡ أَنَّكُمۡ تُكَذِّبُونَ
ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
Tafsiran larabci:
فَلَوۡلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلۡحُلۡقُومَ
(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَنتُمۡ حِينَئِذٖ تَنظُرُونَ
እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
Tafsiran larabci:
وَنَحۡنُ أَقۡرَبُ إِلَيۡهِ مِنكُمۡ وَلَٰكِن لَّا تُبۡصِرُونَ
እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
Tafsiran larabci:
فَلَوۡلَآ إِن كُنتُمۡ غَيۡرَ مَدِينِينَ
የማትዳኙም ከኾናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
تَرۡجِعُونَهَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
Tafsiran larabci:
فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ
(ሟቹ) ከባለሟሎቹ ቢኾንማ፡፡
Tafsiran larabci:
فَرَوۡحٞ وَرَيۡحَانٞ وَجَنَّتُ نَعِيمٖ
(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
ከቀኝ ጓዶችም ቢኾንማ፡፡
Tafsiran larabci:
فَسَلَٰمٞ لَّكَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
Tafsiran larabci:
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُكَذِّبِينَ ٱلضَّآلِّينَ
ከሚያስዋሹት ጠማማዎችም ቢኾንማ፡፡
Tafsiran larabci:
فَنُزُلٞ مِّنۡ حَمِيمٖ
ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
Tafsiran larabci:
وَتَصۡلِيَةُ جَحِيمٍ
በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ ٱلۡيَقِينِ
ይህ እርሱ እርግጠኛ እውነት ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
Tafsiran larabci:
 
Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Al'waki'ah
Teburin Jerin Sunayen Surori Lambar shafi
 
Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

Rufewa