Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic * - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Alkiyama   Aya:

ሱረቱ አል ቂያማህ

لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Tafsiran larabci:
وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Tafsiran larabci:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
Tafsiran larabci:
بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
Tafsiran larabci:
بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Tafsiran larabci:
يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Tafsiran larabci:
فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Tafsiran larabci:
كَلَّا لَا وَزَرَ
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Tafsiran larabci:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
Tafsiran larabci:
بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Tafsiran larabci:
وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
Tafsiran larabci:
لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Tafsiran larabci:
فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Tafsiran larabci:
ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Tafsiran larabci:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Tafsiran larabci:
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Tafsiran larabci:
وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
Tafsiran larabci:
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
Tafsiran larabci:
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Tafsiran larabci:
أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Tafsiran larabci:
ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
Tafsiran larabci:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
Tafsiran larabci:
أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
Tafsiran larabci:
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
Tafsiran larabci:
فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
Tafsiran larabci:
أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
Tafsiran larabci:
 
Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Alkiyama
Teburin Jerin Sunayen Surori Lambar shafi
 
Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

Rufewa