የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም * - የትርጉሞች ማዉጫ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አል ቂያማህ   አንቀጽ:

ሱረቱ አል ቂያማህ

لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّا لَا وَزَرَ
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
 
የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አል ቂያማህ
የምዕራፎች ማውጫ የገፅ ቁጥር
 
የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም - የትርጉሞች ማዉጫ

ወደ አማርኛ በሸይኽ ሙሓመድ ሷዲቅ እና በሸይኽ ሙሓመድ ሣኒ ሓቢብ የተተረጎመ የቁርዓን መልዕክተ ትርጉም። በሩዋድ የትርጉም ማእከልም ተቆጣጣሪነት ማስተካከያ ተደርጎበታል። ዋናው የትርጉም ቅጅም ለአስተያየቶች፣ ተከታታይ ግምገማ እና መሻሻል ቀርቧል።

መዝጋት