የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም * - የትርጉሞች ማዉጫ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አል ሙደሲር   አንቀጽ:

ሱረቱ አል ሙደሲር

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
قُمۡ فَأَنذِرۡ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
ጌታህንም አክብር፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
ልብስህንም አጥራ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስ።
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَبَنِينَ شُهُودٗا
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ نَظَرَ
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
የአረብኛ ቁርኣን ማብራሪያ:
 
የይዘት ትርጉም ምዕራፍ: ሱረቱ አል ሙደሲር
የምዕራፎች ማውጫ የገፅ ቁጥር
 
የቅዱስ ቁርዓን ይዘት ትርጉም - የ አማርኛ ቋንቋ ትርጉም - የትርጉሞች ማዉጫ

ወደ አማርኛ በሸይኽ ሙሓመድ ሷዲቅ እና በሸይኽ ሙሓመድ ሣኒ ሓቢብ የተተረጎመ የቁርዓን መልዕክተ ትርጉም። በሩዋድ የትርጉም ማእከልም ተቆጣጣሪነት ማስተካከያ ተደርጎበታል። ዋናው የትርጉም ቅጅም ለአስተያየቶች፣ ተከታታይ ግምገማ እና መሻሻል ቀርቧል።

መዝጋት