আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ * - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-মুদ্দাচ্ছিৰ   আয়াত:

ሱረቱ አል ሙደሲር

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
قُمۡ فَأَنذِرۡ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
ጌታህንም አክብር፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
ልብስህንም አጥራ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስ።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَبَنِينَ شُهُودٗا
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ نَظَرَ
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
 
অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-মুদ্দাচ্ছিৰ
ছুৰাৰ তালিকা পৃষ্ঠা নং
 
আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

বন্ধ