Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic * - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Almursala   Aya:

ሱረቱ አል ሙርሰላት

وَٱلۡمُرۡسَلَٰتِ عُرۡفٗا
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
Tafsiran larabci:
فَٱلۡعَٰصِفَٰتِ عَصۡفٗا
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
Tafsiran larabci:
وَٱلنَّٰشِرَٰتِ نَشۡرٗا
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
Tafsiran larabci:
فَٱلۡفَٰرِقَٰتِ فَرۡقٗا
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
Tafsiran larabci:
فَٱلۡمُلۡقِيَٰتِ ذِكۡرًا
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
Tafsiran larabci:
عُذۡرًا أَوۡ نُذۡرًا
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٞ
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
Tafsiran larabci:
فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتۡ
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتۡ
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ نُسِفَتۡ
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتۡ
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
Tafsiran larabci:
لِأَيِّ يَوۡمٍ أُجِّلَتۡ
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
Tafsiran larabci:
لِيَوۡمِ ٱلۡفَصۡلِ
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
Tafsiran larabci:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡ {1}
{1} ይህ አንቀጽ በዚህ ምእራፍ ውስጥ 10 ግዜ ተደጋግሟል
Tafsiran larabci:
أَلَمۡ نُهۡلِكِ ٱلۡأَوَّلِينَ
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
Tafsiran larabci:
ثُمَّ نُتۡبِعُهُمُ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
Tafsiran larabci:
كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
أَلَمۡ نَخۡلُقكُّم مِّن مَّآءٖ مَّهِينٖ
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
Tafsiran larabci:
فَجَعَلۡنَٰهُ فِي قَرَارٖ مَّكِينٍ
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
Tafsiran larabci:
إِلَىٰ قَدَرٖ مَّعۡلُومٖ
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡
Tafsiran larabci:
فَقَدَرۡنَا فَنِعۡمَ ٱلۡقَٰدِرُونَ
መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ كِفَاتًا
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
Tafsiran larabci:
أَحۡيَآءٗ وَأَمۡوَٰتٗا
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
وَجَعَلۡنَا فِيهَا رَوَٰسِيَ شَٰمِخَٰتٖ وَأَسۡقَيۡنَٰكُم مَّآءٗ فُرَاتٗا
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
Tafsiran larabci:
ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ ظِلّٖ ذِي ثَلَٰثِ شُعَبٖ
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
لَّا ظَلِيلٖ وَلَا يُغۡنِي مِنَ ٱللَّهَبِ
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّهَا تَرۡمِي بِشَرَرٖ كَٱلۡقَصۡرِ
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
Tafsiran larabci:
كَأَنَّهُۥ جِمَٰلَتٞ صُفۡرٞ
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
هَٰذَا يَوۡمُ لَا يَنطِقُونَ
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡
Tafsiran larabci:
وَلَا يُؤۡذَنُ لَهُمۡ فَيَعۡتَذِرُونَ
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِۖ جَمَعۡنَٰكُمۡ وَٱلۡأَوَّلِينَ
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
Tafsiran larabci:
فَإِن كَانَ لَكُمۡ كَيۡدٞ فَكِيدُونِ
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّ ٱلۡمُتَّقِينَ فِي ظِلَٰلٖ وَعُيُونٖ
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَفَوَٰكِهَ مِمَّا يَشۡتَهُونَ
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
Tafsiran larabci:
كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
Tafsiran larabci:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
كُلُواْ وَتَمَتَّعُواْ قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجۡرِمُونَ
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱرۡكَعُواْ لَا يَرۡكَعُونَ
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
Tafsiran larabci:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
Tafsiran larabci:
فَبِأَيِّ حَدِيثِۭ بَعۡدَهُۥ يُؤۡمِنُونَ
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
Tafsiran larabci:
 
Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Almursala
Teburin Jerin Sunayen Surori Lambar shafi
 
Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - Fassara da Yaren Amharic - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

Rufewa