ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية * - فهرس التراجم

XML CSV Excel API
تنزيل الملفات يتضمن الموافقة على هذه الشروط والسياسات

ترجمة معاني سورة: المرسلات   آية:

سورة المرسلات - ሱረቱ አል ሙርሰላት

وَٱلۡمُرۡسَلَٰتِ عُرۡفٗا
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣
التفاسير العربية:
فَٱلۡعَٰصِفَٰتِ عَصۡفٗا
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣
التفاسير العربية:
وَٱلنَّٰشِرَٰتِ نَشۡرٗا
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣
التفاسير العربية:
فَٱلۡفَٰرِقَٰتِ فَرۡقٗا
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣
التفاسير العربية:
فَٱلۡمُلۡقِيَٰتِ ذِكۡرًا
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣
التفاسير العربية:
عُذۡرًا أَوۡ نُذۡرًا
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٞ
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡
التفاسير العربية:
فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتۡ
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡
التفاسير العربية:
وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتۡ
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡
التفاسير العربية:
وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ نُسِفَتۡ
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡
التفاسير العربية:
وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتۡ
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡
التفاسير العربية:
لِأَيِّ يَوۡمٍ أُجِّلَتۡ
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤
التفاسير العربية:
لِيَوۡمِ ٱلۡفَصۡلِ
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡
التفاسير العربية:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡ {1}
{1} ይህ አንቀጽ በዚህ ምእራፍ ውስጥ 10 ግዜ ተደጋግሟል
التفاسير العربية:
أَلَمۡ نُهۡلِكِ ٱلۡأَوَّلِينَ
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?
التفاسير العربية:
ثُمَّ نُتۡبِعُهُمُ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡
التفاسير العربية:
كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
أَلَمۡ نَخۡلُقكُّم مِّن مَّآءٖ مَّهِينٖ
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?
التفاسير العربية:
فَجَعَلۡنَٰهُ فِي قَرَارٖ مَّكِينٍ
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡
التفاسير العربية:
إِلَىٰ قَدَرٖ مَّعۡلُومٖ
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡
التفاسير العربية:
فَقَدَرۡنَا فَنِعۡمَ ٱلۡقَٰدِرُونَ
መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ كِفَاتًا
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?
التفاسير العربية:
أَحۡيَآءٗ وَأَمۡوَٰتٗا
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡
التفاسير العربية:
وَجَعَلۡنَا فِيهَا رَوَٰسِيَ شَٰمِخَٰتٖ وَأَسۡقَيۡنَٰكُم مَّآءٗ فُرَاتٗا
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡
التفاسير العربية:
ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ ظِلّٖ ذِي ثَلَٰثِ شُعَبٖ
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡
التفاسير العربية:
لَّا ظَلِيلٖ وَلَا يُغۡنِي مِنَ ٱللَّهَبِ
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّهَا تَرۡمِي بِشَرَرٖ كَٱلۡقَصۡرِ
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡
التفاسير العربية:
كَأَنَّهُۥ جِمَٰلَتٞ صُفۡرٞ
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
هَٰذَا يَوۡمُ لَا يَنطِقُونَ
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡
التفاسير العربية:
وَلَا يُؤۡذَنُ لَهُمۡ فَيَعۡتَذِرُونَ
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِۖ جَمَعۡنَٰكُمۡ وَٱلۡأَوَّلِينَ
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡
التفاسير العربية:
فَإِن كَانَ لَكُمۡ كَيۡدٞ فَكِيدُونِ
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّ ٱلۡمُتَّقِينَ فِي ظِلَٰلٖ وَعُيُونٖ
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡
التفاسير العربية:
وَفَوَٰكِهَ مِمَّا يَشۡتَهُونَ
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡
التفاسير العربية:
كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡
التفاسير العربية:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
كُلُواْ وَتَمَتَّعُواْ قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجۡرِمُونَ
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱرۡكَعُواْ لَا يَرۡكَعُونَ
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡
التفاسير العربية:
وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
التفاسير العربية:
فَبِأَيِّ حَدِيثِۭ بَعۡدَهُۥ يُؤۡمِنُونَ
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
التفاسير العربية:
 
ترجمة معاني سورة: المرسلات
فهرس السور رقم الصفحة
 
ترجمة معاني القرآن الكريم - الترجمة الأمهرية - فهرس التراجم

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

إغلاق