Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - الترجمة الأمهرية - زين * - Teburin Bayani kan wasu Fassarori


Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Al'a'ala   Aya:

ሱረቱ አል አዕላ

سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى
1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የዚያን ከሁሉ በላይ የሆነውን ጌታህን ስም አጥራ (አሞግስ)።
Tafsiran larabci:
ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ
2. ያ ሁሉን ነገር የፈጠረውንና ያስተካከለውን፤
Tafsiran larabci:
وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ
3. ያን የወሰነውን ነገርንም ሁሉ ለተፈጠረለት የመራውን፤
Tafsiran larabci:
وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ
4. ያም ግጦሽን ለምለም አርጎ ያወጣውን፤
Tafsiran larabci:
فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ
5.(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
Tafsiran larabci:
سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፤
Tafsiran larabci:
إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ
7. አላህ ከፈለገው ነገር በስተቀር፤ እናም እርሱ ግልጹንም የሚሸሽገውንም ሁሉ ያውቃልና፤
Tafsiran larabci:
وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ
8. ለገሪቱም (ሕይወት እስላምን ትከተል ዘንድ) እናገራሃለን።
Tafsiran larabci:
فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ
9. (ሰዎችንም) ገስፅ፤ ግሳፄይቱ ብትጠቅም።
Tafsiran larabci:
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ
10. (አላህን) የሚፈራ በእርግጥ ይገሰፃል።
Tafsiran larabci:
وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى
11. መናጢዉም ይርቃታል::
Tafsiran larabci:
ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
12. ያ! ታላቂቱን እሳት የሚገባው፤
Tafsiran larabci:
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
13. ከዚያም በእርሷ ውስጥ የማይሞትና ህያዉም የማይሆነው።
Tafsiran larabci:
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
14. (አላህን ከማመፅ) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፤
Tafsiran larabci:
وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
15. የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ::
Tafsiran larabci:
بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
16. ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ታስቀድማላችሁ፤
Tafsiran larabci:
وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
17. (ሰዎች ሆይ!) መጨረሻይቱ ሕይወት በላጭና፤ ዘወታሪ ሆና ሳለ።
Tafsiran larabci:
إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
18. ይህ በቀደምቶቹም መጻሕፍት ውስጥ ያለ ነው።
Tafsiran larabci:
صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
19. በኢብራሂምና በሙሳ መጽሐፍት ውስጥ የሰፈረ እውነታ ነው።
Tafsiran larabci:
 
Fassarar Ma'anoni Sura: Suratu Al'a'ala
Teburin Jerin Sunayen Surori Lambar shafi
 
Fassarar Ma'anonin Alqura'ni - الترجمة الأمهرية - زين - Teburin Bayani kan wasu Fassarori

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

Rufewa