আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - الترجمة الأمهرية - زين * - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ


অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-আ'লা   আয়াত:

ሱረቱ አል አዕላ

سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى
1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የዚያን ከሁሉ በላይ የሆነውን ጌታህን ስም አጥራ (አሞግስ)።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ
2. ያ ሁሉን ነገር የፈጠረውንና ያስተካከለውን፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ
3. ያን የወሰነውን ነገርንም ሁሉ ለተፈጠረለት የመራውን፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ
4. ያም ግጦሽን ለምለም አርጎ ያወጣውን፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ
5.(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ
7. አላህ ከፈለገው ነገር በስተቀር፤ እናም እርሱ ግልጹንም የሚሸሽገውንም ሁሉ ያውቃልና፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ
8. ለገሪቱም (ሕይወት እስላምን ትከተል ዘንድ) እናገራሃለን።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ
9. (ሰዎችንም) ገስፅ፤ ግሳፄይቱ ብትጠቅም።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ
10. (አላህን) የሚፈራ በእርግጥ ይገሰፃል።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى
11. መናጢዉም ይርቃታል::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
12. ያ! ታላቂቱን እሳት የሚገባው፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
13. ከዚያም በእርሷ ውስጥ የማይሞትና ህያዉም የማይሆነው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
14. (አላህን ከማመፅ) የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
15. የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
16. ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ታስቀድማላችሁ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
17. (ሰዎች ሆይ!) መጨረሻይቱ ሕይወት በላጭና፤ ዘወታሪ ሆና ሳለ።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
18. ይህ በቀደምቶቹም መጻሕፍት ውስጥ ያለ ነው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
19. በኢብራሂምና በሙሳ መጽሐፍት ውስጥ የሰፈረ እውነታ ነው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
 
অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-আ'লা
ছুৰাৰ তালিকা পৃষ্ঠা নং
 
আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - الترجمة الأمهرية - زين - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

বন্ধ