Terjemahan makna Alquran Alkarim - Terjemahan Berbahasa Amhar * - Daftar isi terjemahan

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Terjemahan makna Surah: Surah Al-Qalam   Ayah:

ሱረቱ አል ቀለም

نٓۚ وَٱلۡقَلَمِ وَمَا يَسۡطُرُونَ
ኑን፤ በብርእ እምላለሁ በዚያም (መልአኮች) በሚጽፉት፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
مَآ أَنتَ بِنِعۡمَةِ رَبِّكَ بِمَجۡنُونٖ
አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَإِنَّ لَكَ لَأَجۡرًا غَيۡرَ مَمۡنُونٖ
ላንተም (ከጌታህ) የማይቋረጥ ዋጋ በእርግጥ አልለህ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَإِنَّكَ لَعَلَىٰ خُلُقٍ عَظِيمٖ
አንተም በታላቅ ጠባይ ላይ ነህ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَسَتُبۡصِرُ وَيُبۡصِرُونَ
ወደፊትም ታያለህ፤ ያያሉም፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
بِأَييِّكُمُ ٱلۡمَفۡتُونُ
ዕብደት በማንኛችሁ እንዳልለ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِٱلۡمُهۡتَدِينَ
ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም ተመሪዎቹን ዐዋቂ ነው፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮችም አትታዝዙ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَدُّواْ لَوۡ تُدۡهِنُ فَيُدۡهِنُونَ
ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافٖ مَّهِينٍ
መሃለኛን ወራዳንም ሁሉ አትታዘዝ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
هَمَّازٖ مَّشَّآءِۭ بِنَمِيمٖ
ሰውን አነዋሪንና በማሳበቅ ኼያጅን፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
مَّنَّاعٖ لِّلۡخَيۡرِ مُعۡتَدٍ أَثِيمٍ
ለበጎ ነገር በጣም ከልካይን፣ ወሰን አላፊን፣ ኃጢአተኛን፤
Tafsir berbahasa Arab:
عُتُلِّۭ بَعۡدَ ذَٰلِكَ زَنِيمٍ
ልበ ደረቅን፣ ከዚህ በኋላ ዲቃላን (ሁሉ አትታዘዝ)፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَن كَانَ ذَا مَالٖ وَبَنِينَ
የገንዘብና የልጆች ባለቤት በመኾኑ (ያስተባብላል)፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
إِذَا تُتۡلَىٰ عَلَيۡهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
سَنَسِمُهُۥ عَلَى ٱلۡخُرۡطُومِ
በአፍንጫው ላይ በእርግጥ (የሚነወርበት) ምልክት እናደርግበታለን፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّا بَلَوۡنَٰهُمۡ كَمَا بَلَوۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡجَنَّةِ إِذۡ أَقۡسَمُواْ لَيَصۡرِمُنَّهَا مُصۡبِحِينَ
እኛ የአትክልቲቱን ባለቤቶቸ እንደ ሞከርን (የመካን ሰዎች) ሞከርናቸው፡፡ ማልደው (ፍሬዋን) ሊለቅሟት በማሉ ጊዜ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَلَا يَسۡتَثۡنُونَ
(በመሓላቸው) አያስቀሩምም፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَطَافَ عَلَيۡهَا طَآئِفٞ مِّن رَّبِّكَ وَهُمۡ نَآئِمُونَ
እነርሱ የተኙ ኾነውም ሳሉ ከጌታህ የኾነ ዟሪ በእርሷ ላይ ዞረባት፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَأَصۡبَحَتۡ كَٱلصَّرِيمِ
እንደ ሌሊት ጨለማም ኾና አነጋች፤ (ከሰለች)፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَتَنَادَوۡاْ مُصۡبِحِينَ
ያነጉም ኾነው ተጠራሩ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَنِ ٱغۡدُواْ عَلَىٰ حَرۡثِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰرِمِينَ
«ቆራጮች እንደ ኾናችሁ በእርሻቸሁ ላይ ማልዱ» በማለት፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَٱنطَلَقُواْ وَهُمۡ يَتَخَٰفَتُونَ
እነርሱ የሚንሾካሾኩ ኾነው ኼዱም፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَن لَّا يَدۡخُلَنَّهَا ٱلۡيَوۡمَ عَلَيۡكُم مِّسۡكِينٞ
ዛሬ በእናንተ ላይ ድኻ እንዳይገባት በማለት፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَغَدَوۡاْ عَلَىٰ حَرۡدٖ قَٰدِرِينَ
(ድኾችን) በመከልከልም ላይ (በሐሳባቸው) ቻዮች ኾነው ማለዱ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَلَمَّا رَأَوۡهَا قَالُوٓاْ إِنَّا لَضَآلُّونَ
(ተቃጥላ) ባዩዋትም ጊዜ «እኛ በእርግጥ ተሳሳቾች ነን» አሉ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ
«ይልቁንም እኛ የተከለከልን ነን» አሉ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
قَالَ أَوۡسَطُهُمۡ أَلَمۡ أَقُل لَّكُمۡ لَوۡلَا تُسَبِّحُونَ
ትክክለኛቸው «ለእናንተ አላህን ለምን አታጠሩም አላልኳችሁምን?» አላቸው፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
قَالُواْ سُبۡحَٰنَ رَبِّنَآ إِنَّا كُنَّا ظَٰلِمِينَ
«ጌታችን ጥራት ይገባው፡፡ እኛ በዳዮች ነበርን፤» አሉ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَلَٰوَمُونَ
የሚወቃቀሱም ኾነው ከፊሎቻቸው በከፊሉ ላይ መጡ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
قَالُواْ يَٰوَيۡلَنَآ إِنَّا كُنَّا طَٰغِينَ
«ዋ ጥፋታችን! እኛ ድንበር አላፊዎች ነበርን፤» አሉ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
عَسَىٰ رَبُّنَآ أَن يُبۡدِلَنَا خَيۡرٗا مِّنۡهَآ إِنَّآ إِلَىٰ رَبِّنَا رَٰغِبُونَ
«ጌታችን ከእርሷ የተሻለን (አትክልት) ሊለውጠን ይከጀላል፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ከጃዮች ነን፤» (አሉ)፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
كَذَٰلِكَ ٱلۡعَذَابُۖ وَلَعَذَابُ ٱلۡأٓخِرَةِ أَكۡبَرُۚ لَوۡ كَانُواْ يَعۡلَمُونَ
ቅጣቱ እንደዚሁ ነው፡፡ የመጨረሻይቱም ዓለም ቅጣት ታላቅ ነው፡፡ የሚያውቁት በኾኑ ኖሮ (በተጠነቀቁ ነበር)፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ عِندَ رَبِّهِمۡ جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
ለጥንቁቆቹ በጌታቸው ዘንድ መጠቀሚያ ገነቶች አሏቸው፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَفَنَجۡعَلُ ٱلۡمُسۡلِمِينَ كَٱلۡمُجۡرِمِينَ
ሙስሊሞቹን እንደ ከሓዲዎች እናደርጋለን?
Tafsir berbahasa Arab:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَمۡ لَكُمۡ كِتَٰبٞ فِيهِ تَدۡرُسُونَ
በእውነቱ ለእናንተ በእርሱ የምታጠኑበት መጽሐፍ አላችሁን?
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّ لَكُمۡ فِيهِ لَمَا تَخَيَّرُونَ
በውስጡ ለእናንተ የምትመርጡት አላችሁ (የሚል)
Tafsir berbahasa Arab:
أَمۡ لَكُمۡ أَيۡمَٰنٌ عَلَيۡنَا بَٰلِغَةٌ إِلَىٰ يَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ إِنَّ لَكُمۡ لَمَا تَحۡكُمُونَ
ወይስ ለእናንተ የምትፈርዱት አላችሁ በማለት (ቃል ኪዳን የገባንላችሁ) እስከ ትንሣኤ ቀን ደራሽ የኾኑ መሓላዎች ለእናንተ በእኛ ላይ አሏችሁን?
Tafsir berbahasa Arab:
سَلۡهُمۡ أَيُّهُم بِذَٰلِكَ زَعِيمٌ
በዚህ ማንኛቸው ተያያዥ እንደ ኾነ ጠይቃቸው፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَمۡ لَهُمۡ شُرَكَآءُ فَلۡيَأۡتُواْ بِشُرَكَآئِهِمۡ إِن كَانُواْ صَٰدِقِينَ
ወይስ ለእነርሱ (በፍርዳቸው ተስማሚ) «ተጋሪዎች» አሏቸውን? እውነተኞችም እንደኾኑ «ተጋሪዎቻቸውን» ያምጡ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
يَوۡمَ يُكۡشَفُ عَن سَاقٖ وَيُدۡعَوۡنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ فَلَا يَسۡتَطِيعُونَ
ባት የሚገለጥበትን (ከሓዲዎች) ወደ መስገድም የሚጥጠሩበትንና የማይችሉበት ቀን (አስታውስ)፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
خَٰشِعَةً أَبۡصَٰرُهُمۡ تَرۡهَقُهُمۡ ذِلَّةٞۖ وَقَدۡ كَانُواْ يُدۡعَوۡنَ إِلَى ٱلسُّجُودِ وَهُمۡ سَٰلِمُونَ
ዓይኖቻቸው የፈሩ ውርደት የምትሸፍናቸው ሲኾኑ፤ (ወደ ስግደት የሚጠሩበትን)፤ እነርሱም (በምድረ ዓለም) ደህና ኾነው ሳሉ ወደ ስግደት በእርግጥ ይጠሩ ነበሩ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَذَرۡنِي وَمَن يُكَذِّبُ بِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِۖ سَنَسۡتَدۡرِجُهُم مِّنۡ حَيۡثُ لَا يَعۡلَمُونَ
በዚህም ንግግር ከሚያስተባብሉት ሰዎች ጋር ተዎኝ፡፡ (እነርሱን እኔ እበቃሃለሁ)፡፡ ከማያውቁት ስፍራ አዘናግተን እንይዛቸዋለን፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَأُمۡلِي لَهُمۡۚ إِنَّ كَيۡدِي مَتِينٌ
እነርሱንም አዘገያለሁ፡፡ ዘዴዬ ብርቱ ነውና፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
أَمۡ تَسۡـَٔلُهُمۡ أَجۡرٗا فَهُم مِّن مَّغۡرَمٖ مُّثۡقَلُونَ
በእውነቱ ዋጋን ትጠይቃቸዋለህን? ስለዚህ እነርሱ ከዕዳ የተከበዱ ናቸውን?
Tafsir berbahasa Arab:
أَمۡ عِندَهُمُ ٱلۡغَيۡبُ فَهُمۡ يَكۡتُبُونَ
ወይስ እነርሱ ዘንድ የሩቁ ምስጢር ዕውቀት አልለን? ስለዚህ እነርሱ ይጽፋሉን?
Tafsir berbahasa Arab:
فَٱصۡبِرۡ لِحُكۡمِ رَبِّكَ وَلَا تَكُن كَصَاحِبِ ٱلۡحُوتِ إِذۡ نَادَىٰ وَهُوَ مَكۡظُومٞ
ለጌታህም ፍርድ ታገሥ፤ (በመበሳጨትና ባለ መታገሥ) እንደ ዓሣው ባለቤትም (እንደ ዮናስ) አትኹን፡፡ እርሱ በጭንቀት የተመላ ኾኖ (ጌታውን) በተጣራ ጊዜ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
لَّوۡلَآ أَن تَدَٰرَكَهُۥ نِعۡمَةٞ مِّن رَّبِّهِۦ لَنُبِذَ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ مَذۡمُومٞ
ከጌታው የኾነ ጸጋ ባላገኘው ኖሮ በምድረ በዳ ተወቃሽ ኾኖ በተጣለ ነበር፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
فَٱجۡتَبَٰهُ رَبُّهُۥ فَجَعَلَهُۥ مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታውም (በነቢይነት) መረጠው፡፡ ከደጋጎቹም አደረገው፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَإِن يَكَادُ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ لَيُزۡلِقُونَكَ بِأَبۡصَٰرِهِمۡ لَمَّا سَمِعُواْ ٱلذِّكۡرَ وَيَقُولُونَ إِنَّهُۥ لَمَجۡنُونٞ
እነሆ እነዚያም የካዱት ሰዎች ቁርኣኑን በሰሙ ጊዜ በዓይኖቻቸው ሊጥሉህ (ሊያጠፉህ) ይቀርባሉ፡፡ «እርሱም በእርግጥ ዕብድ ነው» ይላሉ፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
وَمَا هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ
ግን እርሱ (ቁርኣን) ለዓለማት መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
Tafsir berbahasa Arab:
 
Terjemahan makna Surah: Surah Al-Qalam
Daftar surah Nomor Halaman
 
Terjemahan makna Alquran Alkarim - Terjemahan Berbahasa Amhar - Daftar isi terjemahan

Terjemahan makna Al-Qur`ān Al-Karīm ke bahasa Amhar oleh Muhammad Sadiq dan Muhammad Al-Sani Habib. Sudah dikoreksi di bawah pengawasan Markaz Ruwād Terjemah. Teks terjemahan asli masih bisa ditampilkan untuk diberi masukan, evaluasi dan pengembangan.

Tutup