Check out the new design

Terjemahan makna Alquran Alkarim - Terjemahan Berbahasa Amhar - Akademi Afrika * - Daftar isi terjemahan


Terjemahan makna Surah: An-Naba`   Ayah:

አን ነበእ

عَمَّ يَتَسَآءَلُونَ
1. ከምን ነገር ይጠያየቃሉ?
Tafsir berbahasa Arab:
عَنِ ٱلنَّبَإِ ٱلۡعَظِيمِ
2. ከታላቁ ዜና (ቁርኣን) ይጠያየቃሉ።
Tafsir berbahasa Arab:
ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ مُخۡتَلِفُونَ
3. ስለዚያ እነርሱ በእርሱ ላይ ስለተለያዩበት (ስለተወዛገቡበት)::
Tafsir berbahasa Arab:
كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
4. ጉዳዩ እነርሱ እንደሚሉት አይደለም:: (ትክክለኛውን) ወደ ፊት ያውቃሉ::
Tafsir berbahasa Arab:
ثُمَّ كَلَّا سَيَعۡلَمُونَ
5. ከዚያም ይከልከሉ፤ (ትክክለኛውን) ወደ ፊት ያውቃሉ።
Tafsir berbahasa Arab:
أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ مِهَٰدٗا
6. ምድርን ምንጣፍ አላደርግንምን?
Tafsir berbahasa Arab:
وَٱلۡجِبَالَ أَوۡتَادٗا
7. ጋራዎችንም ችካሎች (አላደረግንምን)?
Tafsir berbahasa Arab:
وَخَلَقۡنَٰكُمۡ أَزۡوَٰجٗا
8. ጥንዶች አድርገንም ፈጠርናችሁ።
Tafsir berbahasa Arab:
وَجَعَلۡنَا نَوۡمَكُمۡ سُبَاتٗا
9. እንቅልፋችሁንም እረፍት አደረግን።
Tafsir berbahasa Arab:
وَجَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِبَاسٗا
10. ሌሊቱንም ልባስ አደረግን::
Tafsir berbahasa Arab:
وَجَعَلۡنَا ٱلنَّهَارَ مَعَاشٗا
11. ቀኑንም ለኑሮ መስሪያ (ለጉዳይ መከወኛ) አደረግን።
Tafsir berbahasa Arab:
وَبَنَيۡنَا فَوۡقَكُمۡ سَبۡعٗا شِدَادٗا
12. ከበላያቸሁም ሰባት ብርቱዎችን (ሰማያት) ገነባን።
Tafsir berbahasa Arab:
وَجَعَلۡنَا سِرَاجٗا وَهَّاجٗا
13. አንጸባራቂ ብርሃንንም አደርግንላችሁ።
Tafsir berbahasa Arab:
وَأَنزَلۡنَا مِنَ ٱلۡمُعۡصِرَٰتِ مَآءٗ ثَجَّاجٗا
14. ከአረገዙት ደመናዎችም የሚንቧቧ ውሃን አወረድን::
Tafsir berbahasa Arab:
لِّنُخۡرِجَ بِهِۦ حَبّٗا وَنَبَاتٗا
15.በእርሱ እህልንና ቅጠላ ቅጠልን፤ እናወጣ ዘንድ(አወረድን)።
Tafsir berbahasa Arab:
وَجَنَّٰتٍ أَلۡفَافًا
16. የተቆላለፉ አትክልቶችንም ::
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّ يَوۡمَ ٱلۡفَصۡلِ كَانَ مِيقَٰتٗا
17. (በህዝቦች መካከልም) የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው።
Tafsir berbahasa Arab:
يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَتَأۡتُونَ أَفۡوَاجٗا
18. (ይሀዉም) በቀንዱ በሚነፋበትና በቡድን በቡድን ሆናችሁም በምትመጡበት ቀን ነው።
Tafsir berbahasa Arab:
وَفُتِحَتِ ٱلسَّمَآءُ فَكَانَتۡ أَبۡوَٰبٗا
19. ሰማይም በምትከፈትና ባለ ብዙ ደጃፎችም በምትሆንበት ቀን፤
Tafsir berbahasa Arab:
وَسُيِّرَتِ ٱلۡجِبَالُ فَكَانَتۡ سَرَابًا
20. ጋራዎችም በሚናዱበትና እንደ ሲሪብዶም በሚሆንበትም ቀን ነው።
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتۡ مِرۡصَادٗا
21. ገሀነም (ለከሓዲያን) መጠባበቂያ ኬላ (ስፍራ) ናት::
Tafsir berbahasa Arab:
لِّلطَّٰغِينَ مَـَٔابٗا
22. ለህግ ተላላፊዎች መመላለሻ ስትሆን።
Tafsir berbahasa Arab:
لَّٰبِثِينَ فِيهَآ أَحۡقَابٗا
23. በውስጧ ብዙ ዘመናትን ነዋሪዎች ሲሆኑ፤
Tafsir berbahasa Arab:
لَّا يَذُوقُونَ فِيهَا بَرۡدٗا وَلَا شَرَابًا
24. በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጠንም አይቀምሱም (አያገኙም)።
Tafsir berbahasa Arab:
إِلَّا حَمِيمٗا وَغَسَّاقٗا
25. ሙቅ የፈላ ውሃንና እዥን እንጂ
Tafsir berbahasa Arab:
جَزَآءٗ وِفَاقًا
26. ተመጣጣኝን ምንዳ ይመነዳሉ።
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ لَا يَرۡجُونَ حِسَابٗا
27. ምርመራ (እንዳለባቸው) ቅንጣት አይጠብቁም ነበርና።
Tafsir berbahasa Arab:
وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَا كِذَّابٗا
28. በአናቅጻችንም ማስተባበልን አስተባበሉ።
Tafsir berbahasa Arab:
وَكُلَّ شَيۡءٍ أَحۡصَيۡنَٰهُ كِتَٰبٗا
29. ነገሩን ሁሉ የተፃፈ ሲሆን አጠቃለልነው።
Tafsir berbahasa Arab:
فَذُوقُواْ فَلَن نَّزِيدَكُمۡ إِلَّا عَذَابًا
30. «(የጃችሁን) ቅመሱም፤ ቅጣትን እንጂ ሌላን አንጨምርላችሁም» (ይባላሉም)።
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّ لِلۡمُتَّقِينَ مَفَازًا
31. ለጥንቅቆቹ (አላህን ለሚፈሩ) ስኬት አላቸው።
Tafsir berbahasa Arab:
حَدَآئِقَ وَأَعۡنَٰبٗا
32. አትክልቶችና ወይኖችም፤
Tafsir berbahasa Arab:
وَكَوَاعِبَ أَتۡرَابٗا
33. በእድሜ እኩያዎች የሆኑ ጡተ ጉችማዎችም፤
Tafsir berbahasa Arab:
وَكَأۡسٗا دِهَاقٗا
34. የተሞሉ ብርጭቆዎችም፤
Tafsir berbahasa Arab:
لَّا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا كِذَّٰبٗا
35. በውስጧ ትርፍ ቃልንም፤ ማስዋሸትንም አይሰሙም::
Tafsir berbahasa Arab:
جَزَآءٗ مِّن رَّبِّكَ عَطَآءً حِسَابٗا
36. ከጌታህ የሆነን ምንዳ፤ በቂ ስጦታን ተሰጡ::
Tafsir berbahasa Arab:
رَّبِّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا ٱلرَّحۡمَٰنِۖ لَا يَمۡلِكُونَ مِنۡهُ خِطَابٗا
37. የሰማያትና የምድር በመካከላቸዉም ላለው ሁሉ ጌታ ከሆነውና በጣም አዛኝ ከሆነው ተመነዱ፤ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም::
Tafsir berbahasa Arab:
يَوۡمَ يَقُومُ ٱلرُّوحُ وَٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ صَفّٗاۖ لَّا يَتَكَلَّمُونَ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَقَالَ صَوَابٗا
38. መልአኩ (ጅብሪል) እና ሌሎች መላዕክትም የተሰለፉ ሆነው በሚቆሙበት ቀን አረህማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ብቻ ቢሆን እንጂ መነጋገርን አይችሉም።
Tafsir berbahasa Arab:
ذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمُ ٱلۡحَقُّۖ فَمَن شَآءَ ٱتَّخَذَ إِلَىٰ رَبِّهِۦ مَـَٔابًا
39. ያ! የእውነት ቀን ነው። የፈለገ ሰው ወደ ጌታው በመልካም ተግባር መመለስን ተግባሩ አድርጎ ይይዛል።
Tafsir berbahasa Arab:
إِنَّآ أَنذَرۡنَٰكُمۡ عَذَابٗا قَرِيبٗا يَوۡمَ يَنظُرُ ٱلۡمَرۡءُ مَا قَدَّمَتۡ يَدَاهُ وَيَقُولُ ٱلۡكَافِرُ يَٰلَيۡتَنِي كُنتُ تُرَٰبَۢا
40. እኛ ቅርብ የሆነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ። ሰዎች ሁሉ በሁለት እጆቻቸው ያስቀደሙትን በግልጽ የሚያይበትና ከሓዲያን ሁሉ «ዋ ምኞቴ! ምንነው አፈር በሆንኩ ባልተቀሰቀስኩኝ» የሚሉበት ቀን።
Tafsir berbahasa Arab:
 
Terjemahan makna Surah: An-Naba`
Daftar surah Nomor Halaman
 
Terjemahan makna Alquran Alkarim - Terjemahan Berbahasa Amhar - Akademi Afrika - Daftar isi terjemahan

Terjemahan oleh Muhammad Zain Zahreddin. Diterbitkan oleh Akademi Afrika.

Tutup