Kilniojo Korano reikšmių vertimas - Amharų k. vertimas - Zain * - Vertimų turinys


Reikšmių vertimas Sūra: Sūra An-Naml   Aja (Korano eilutė):

ሱረቱ አን ነምል

طسٓۚ تِلۡكَ ءَايَٰتُ ٱلۡقُرۡءَانِ وَكِتَابٖ مُّبِينٍ
1. ጣ፤ ሲን፤ ይህ ከቁርኣኑና ከገላጩ መጽሐፍ አናቅጽ ነው።
Tafsyrai arabų kalba:
هُدٗى وَبُشۡرَىٰ لِلۡمُؤۡمِنِينَ
2. ለምዕምናን መሪና ብስራት ነው::
Tafsyrai arabų kalba:
ٱلَّذِينَ يُقِيمُونَ ٱلصَّلَوٰةَ وَيُؤۡتُونَ ٱلزَّكَوٰةَ وَهُم بِٱلۡأٓخِرَةِ هُمۡ يُوقِنُونَ
3. ለእነዚያ ሶላትን ለሚሰግዱት፤ ዘካንም ለሚሰጡ፤ እነርሱም በመጨረሻይቱ ሕይወት እነርሱ የሚያረጋግጡ ለሆኑት::
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ زَيَّنَّا لَهُمۡ أَعۡمَٰلَهُمۡ فَهُمۡ يَعۡمَهُونَ
4. እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት ለእነርሱ ክፉ ሥራዎቻቸውን ሸለምንላቸው:: ስለዚህ እነርሱ ይዋልላሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
أُوْلَٰٓئِكَ ٱلَّذِينَ لَهُمۡ سُوٓءُ ٱلۡعَذَابِ وَهُمۡ فِي ٱلۡأٓخِرَةِ هُمُ ٱلۡأَخۡسَرُونَ
5. እነርሱ እነዚያ ክፉ ቅጣት ያላባቸው ናቸው:: እነርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም እነርሱ በጣም ከከሳሪዎቹ ናቸው::
Tafsyrai arabų kalba:
وَإِنَّكَ لَتُلَقَّى ٱلۡقُرۡءَانَ مِن لَّدُنۡ حَكِيمٍ عَلِيمٍ
6. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንተም ቁርኣንን ጥበበኛና አዋቂ ከሆነው ጌታህ ዘንድ በእርግጥ ትስሰጣለህ::
Tafsyrai arabų kalba:
إِذۡ قَالَ مُوسَىٰ لِأَهۡلِهِۦٓ إِنِّيٓ ءَانَسۡتُ نَارٗا سَـَٔاتِيكُم مِّنۡهَا بِخَبَرٍ أَوۡ ءَاتِيكُم بِشِهَابٖ قَبَسٖ لَّعَلَّكُمۡ تَصۡطَلُونَ
7. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሙሳ ለቤተሰቦቹ «እኔ እሳትን አየሁ ከእርሷ ወሬን አመጣላችኋለሁ፤ ወይም ትሞቁ ዘንድ የተለኮሰ ችቦን አመጣላችኋለሁ» ባለ ጊዜ የሆነውን አውሳላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
فَلَمَّا جَآءَهَا نُودِيَ أَنۢ بُورِكَ مَن فِي ٱلنَّارِ وَمَنۡ حَوۡلَهَا وَسُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
8. በመጣትም ጊዜ እንዲህ በማለት ተጠራ፡- «በእሳቲቱ ያለው ሰውና በዙሪያዋ ያሉም ሰዎች ሁሉ ተባረኩ:: የዓለማትም ጌታ አላህ ጥራት ይገባው።
Tafsyrai arabų kalba:
يَٰمُوسَىٰٓ إِنَّهُۥٓ أَنَا ٱللَّهُ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡحَكِيمُ
9. «ሙሳ ሆይ! እነሆ እኔ አሸናፊዉና ጥበበኛው (አምላክህ) አላህ ነኝ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَأَلۡقِ عَصَاكَۚ فَلَمَّا رَءَاهَا تَهۡتَزُّ كَأَنَّهَا جَآنّٞ وَلَّىٰ مُدۡبِرٗا وَلَمۡ يُعَقِّبۡۚ يَٰمُوسَىٰ لَا تَخَفۡ إِنِّي لَا يَخَافُ لَدَيَّ ٱلۡمُرۡسَلُونَ
10. «በትርህንም ጣል» (ተባለና ጣለም):: እርሷ እንደ ትንሽ እባብ በፍጥነት ስትስለከለክ ባያትም ጊዜ ፊቱን አዙሮ ሸሸ:: አልተመለሰምም:: «ሙሳ ሆይ! አትፍራ:: መልዕክተኞች እኔ ዘንድ ፈጽሞ አይፈሩምና።
Tafsyrai arabų kalba:
إِلَّا مَن ظَلَمَ ثُمَّ بَدَّلَ حُسۡنَۢا بَعۡدَ سُوٓءٖ فَإِنِّي غَفُورٞ رَّحِيمٞ
11. «ግን የበደለ ሰው ከዚያም ከመጥፎ ሥራው በኋላ መልካምን የለወጠ እኔ መሓሪ፤ አዛኝ ነኝ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَأَدۡخِلۡ يَدَكَ فِي جَيۡبِكَ تَخۡرُجۡ بَيۡضَآءَ مِنۡ غَيۡرِ سُوٓءٖۖ فِي تِسۡعِ ءَايَٰتٍ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ وَقَوۡمِهِۦٓۚ إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَوۡمٗا فَٰسِقِينَ
12. «እጅህንም በአንገትየህ ውስጥ አስገባ ያለ ነውር (ወይም ያለ ለምጽ) ነጭ ሆና ትወጣለችና በዘጠኝ ታዐምራት ወደ ፈርዖንና ወደ ሕዝቦቹ ሂድ እነርሱ አመጸኞች ህዝቦች ናቸውና።»
Tafsyrai arabų kalba:
فَلَمَّا جَآءَتۡهُمۡ ءَايَٰتُنَا مُبۡصِرَةٗ قَالُواْ هَٰذَا سِحۡرٞ مُّبِينٞ
13. ተዓምራታችንም ግልጽ ሆና በመጣቻቸው ጊዜ «ይህ ግልጽ ድግምት ነው።» አሉ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَجَحَدُواْ بِهَا وَٱسۡتَيۡقَنَتۡهَآ أَنفُسُهُمۡ ظُلۡمٗا وَعُلُوّٗاۚ فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُفۡسِدِينَ
14. ነፍሶቻቸዉም ያረጋገጧት ሲሆኑ ለበደልና ለኩራት በእርሷ ካዱ:: የአበላሾችም ፍጻሜ እንዴት እንደነበረ ተመልከት::
Tafsyrai arabų kalba:
وَلَقَدۡ ءَاتَيۡنَا دَاوُۥدَ وَسُلَيۡمَٰنَ عِلۡمٗاۖ وَقَالَا ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ ٱلَّذِي فَضَّلَنَا عَلَىٰ كَثِيرٖ مِّنۡ عِبَادِهِ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
15. ለዳውድና ለሱለይማንም እውቀትን በእርግጥ ሰጠናቸው:: «ምስጋና ሁሉ ለአላህ ለዚያ ከአማኞች ባሮቹ በብዙዎቹ ላይ ላበለጠን ይገባው።» አሉም።
Tafsyrai arabų kalba:
وَوَرِثَ سُلَيۡمَٰنُ دَاوُۥدَۖ وَقَالَ يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ عُلِّمۡنَا مَنطِقَ ٱلطَّيۡرِ وَأُوتِينَا مِن كُلِّ شَيۡءٍۖ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَضۡلُ ٱلۡمُبِينُ
16. ሱለይማንም ዳውድን ወረሰ:: አለም «ሰዎች ሆይ የበራሪን ንግግር (የወፍን ቋንቋ) ተስተማርን ከነገሩም ሁሉ ተሰጠን ይህ እርሱ በእርግጥ ግልጽ የሆነ ችሮታ ነው።»
Tafsyrai arabų kalba:
وَحُشِرَ لِسُلَيۡمَٰنَ جُنُودُهُۥ مِنَ ٱلۡجِنِّ وَٱلۡإِنسِ وَٱلطَّيۡرِ فَهُمۡ يُوزَعُونَ
17. ለሱለይማንም ከአጋንንት ከሰዉም ከበራሪም የሆኑት ሰራዊቶቹ ተሰበሰቡ:: እነርሱም ይከመከማሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
حَتَّىٰٓ إِذَآ أَتَوۡاْ عَلَىٰ وَادِ ٱلنَّمۡلِ قَالَتۡ نَمۡلَةٞ يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّمۡلُ ٱدۡخُلُواْ مَسَٰكِنَكُمۡ لَا يَحۡطِمَنَّكُمۡ سُلَيۡمَٰنُ وَجُنُودُهُۥ وَهُمۡ لَا يَشۡعُرُونَ
18. በጉንዳንም ሸለቆ በመጡ ጊዜ አንዲት ጉንዳን፡- «እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ:: ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲሆኑ እንዳይሰባብሯችሁ።» አለች።
Tafsyrai arabų kalba:
فَتَبَسَّمَ ضَاحِكٗا مِّن قَوۡلِهَا وَقَالَ رَبِّ أَوۡزِعۡنِيٓ أَنۡ أَشۡكُرَ نِعۡمَتَكَ ٱلَّتِيٓ أَنۡعَمۡتَ عَلَيَّ وَعَلَىٰ وَٰلِدَيَّ وَأَنۡ أَعۡمَلَ صَٰلِحٗا تَرۡضَىٰهُ وَأَدۡخِلۡنِي بِرَحۡمَتِكَ فِي عِبَادِكَ ٱلصَّٰلِحِينَ
19. ከንግግርዋም እየሳቀ ጥርሱን ፈገግ አደረገ። «ጌታዬ ሆይ! ያቺን በእኔና በወላጆቼ ላይ የለገስካትን ጸጋህን እንዳመሰግን የምትወደውንም በጎ ሥራ እንድሠራ ምራኝ፤ በችሮታህም በመልካሞቹ ባሮችህ ውስጥ አስገባኝ።» አለ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَتَفَقَّدَ ٱلطَّيۡرَ فَقَالَ مَالِيَ لَآ أَرَى ٱلۡهُدۡهُدَ أَمۡ كَانَ مِنَ ٱلۡغَآئِبِينَ
20. በራሪዎቹንም ተመለከተ:: ከዚያ «ሁድሁድን ለምን አላየሁትም! በእውነት ከራቁት ነበርን?
Tafsyrai arabų kalba:
لَأُعَذِّبَنَّهُۥ عَذَابٗا شَدِيدًا أَوۡ لَأَاْذۡبَحَنَّهُۥٓ أَوۡ لَيَأۡتِيَنِّي بِسُلۡطَٰنٖ مُّبِينٖ
21. «ብርቱን ቅጣት በእርግጥ እቀጣዋለሁ:: ወይም በእርግጥ አርደዋለሁ:: ወይም ግልጽ የሆነ አስረጅን ያቀርብልኛል።» አለ።
Tafsyrai arabų kalba:
فَمَكَثَ غَيۡرَ بَعِيدٖ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمۡ تُحِطۡ بِهِۦ وَجِئۡتُكَ مِن سَبَإِۭ بِنَبَإٖ يَقِينٍ
22. (ሁድሁድ የተባለው ወፍ) እሩቅ ያልሆነንም ጊዜ ቆየ:: ከዚያም አለ «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنِّي وَجَدتُّ ٱمۡرَأَةٗ تَمۡلِكُهُمۡ وَأُوتِيَتۡ مِن كُلِّ شَيۡءٖ وَلَهَا عَرۡشٌ عَظِيمٞ
23. «እኔ የምትገዛቸው የሆነችን ሴት ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችን አገኘሁ:: ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አላት።
Tafsyrai arabų kalba:
وَجَدتُّهَا وَقَوۡمَهَا يَسۡجُدُونَ لِلشَّمۡسِ مِن دُونِ ٱللَّهِ وَزَيَّنَ لَهُمُ ٱلشَّيۡطَٰنُ أَعۡمَٰلَهُمۡ فَصَدَّهُمۡ عَنِ ٱلسَّبِيلِ فَهُمۡ لَا يَهۡتَدُونَ
24. «እርስዋንም ሕዝቦችዋንም ከአላህ ሌላ ለጸሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው። ሰይጣንም ለእነርሱ ሥራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል። ከእውነተኛዉም መንገድ አግዷቸዋል:: ስለዚህ እነርሱ ወደ እውነት አይመሩም።
Tafsyrai arabų kalba:
أَلَّاۤ يَسۡجُدُواْۤ لِلَّهِ ٱلَّذِي يُخۡرِجُ ٱلۡخَبۡءَ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَيَعۡلَمُ مَا تُخۡفُونَ وَمَا تُعۡلِنُونَ
25. «ለዚያም በሰማያትና በምድር ዉስጥ የተደበቀውን ለሚያወጣው የምትሸሽጉትንና የምትገልጹትንም ሁሉ ለሚያውቀው አላህ እንዳይሰግዱ ሰይጣን አግዷቸዋል።
Tafsyrai arabų kalba:
ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ رَبُّ ٱلۡعَرۡشِ ٱلۡعَظِيمِ۩
26. «አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም:: የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው።» (አለ) {1}
{1} እዚህ የንባብ ሱጁድ (ሱጁዱ ትላወህ) ይደረጋል።
Tafsyrai arabų kalba:
۞ قَالَ سَنَنظُرُ أَصَدَقۡتَ أَمۡ كُنتَ مِنَ ٱلۡكَٰذِبِينَ
27. ሱለይማንም አለ፡- «እውነት እንደ ተናገርክ ወይም ከውሸታሞቹ እንደሆንክ ወደ ፊት እናያለን።
Tafsyrai arabų kalba:
ٱذۡهَب بِّكِتَٰبِي هَٰذَا فَأَلۡقِهۡ إِلَيۡهِمۡ ثُمَّ تَوَلَّ عَنۡهُمۡ فَٱنظُرۡ مَاذَا يَرۡجِعُونَ
28. «ይህንን ደብዳቤዬን ይዘህ ሂድ:: ወደ እነርሱም ጣለው ከዚያ ከእነርሱ ዘወር በልና ምን እንደሚመልሱም ተመልከት።»
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَتۡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمَلَؤُاْ إِنِّيٓ أُلۡقِيَ إِلَيَّ كِتَٰبٞ كَرِيمٌ
29. እርሷም በደረሳት ጊዜ አለች፡- «እናንተ መማክርቶች ሆይ! እኔ ክብር ያለው ጽሑፍ ወደ እኔ ተጣለ።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّهُۥ مِن سُلَيۡمَٰنَ وَإِنَّهُۥ بِسۡمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحۡمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
30. «እርሱ ከሱለይማን ነው። እርሱም በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
Tafsyrai arabų kalba:
أَلَّا تَعۡلُواْ عَلَيَّ وَأۡتُونِي مُسۡلِمِينَ
31. «‹በእኔ ላይ አትኩሩ:: ታዛዦችም ሆናችሁ ወደ እኔ ኑ› የሚል ነው።»
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَتۡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمَلَؤُاْ أَفۡتُونِي فِيٓ أَمۡرِي مَا كُنتُ قَاطِعَةً أَمۡرًا حَتَّىٰ تَشۡهَدُونِ
32. «እናንተ መማክርቶች ሆይ! በነገሬ የሚበጀውን ንገሩኝ እስከምትነግሩኝ ድረስ አንድንም ነገር ቆራጭ አይደለሁምና» አለች።
Tafsyrai arabų kalba:
قَالُواْ نَحۡنُ أُوْلُواْ قُوَّةٖ وَأُوْلُواْ بَأۡسٖ شَدِيدٖ وَٱلۡأَمۡرُ إِلَيۡكِ فَٱنظُرِي مَاذَا تَأۡمُرِينَ
33. «እኛ የሃይል ባለቤቶች የብርቱ ጦርም ባለቤቶች ነን:: ግን ትዕዛዙ ከወደ አንቺ ብቻ ነው። ምን እንደምታዝዢንም አስተውይ» አሏት::
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَتۡ إِنَّ ٱلۡمُلُوكَ إِذَا دَخَلُواْ قَرۡيَةً أَفۡسَدُوهَا وَجَعَلُوٓاْ أَعِزَّةَ أَهۡلِهَآ أَذِلَّةٗۚ وَكَذَٰلِكَ يَفۡعَلُونَ
34. እርሷም አለች፡- «ንጉሶች ከተማን በሃይል በገቡባት ጊዜ ያበላሿታል የተከበሩ ሰዎቿንም ወራዶች ያደርጋሉ:: ልክ እንደዚሁ ነው የሚያደርጉት።
Tafsyrai arabų kalba:
وَإِنِّي مُرۡسِلَةٌ إِلَيۡهِم بِهَدِيَّةٖ فَنَاظِرَةُۢ بِمَ يَرۡجِعُ ٱلۡمُرۡسَلُونَ
35. «እኔም ወደ እነርሱ ገጸበረከትን የምልክና መልዕክተኞቹ በምን እንደሚመልሱ የምጠባበቅ ነኝ።»
Tafsyrai arabų kalba:
فَلَمَّا جَآءَ سُلَيۡمَٰنَ قَالَ أَتُمِدُّونَنِ بِمَالٖ فَمَآ ءَاتَىٰنِۦَ ٱللَّهُ خَيۡرٞ مِّمَّآ ءَاتَىٰكُمۚ بَلۡ أَنتُم بِهَدِيَّتِكُمۡ تَفۡرَحُونَ
36. መልዕክተኛው ሱለይማንን በመጣውም ጊዜ አለ፡- «በገንዘብ ትረዱኛላችሁን? አላህም የሰጠን ከሰጣችሁ የበለጠ ነው:: ይልቁንም እናንተ በገጸበረከታችሁ ትደሰታላችሁ።
Tafsyrai arabų kalba:
ٱرۡجِعۡ إِلَيۡهِمۡ فَلَنَأۡتِيَنَّهُم بِجُنُودٖ لَّا قِبَلَ لَهُم بِهَا وَلَنُخۡرِجَنَّهُم مِّنۡهَآ أَذِلَّةٗ وَهُمۡ صَٰغِرُونَ
37. «ወደ እነርሱ ተመለስ:: ለእነርሱም በእርሷ ችሎታ በሌላቸው ሰራዊት እንመጣባቸዋለን:: ከእርሷም እነርሱ የተዋረዱ ሆነው በእርግጥ እናወጣቸዋለን።» አለ።
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَ يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمَلَؤُاْ أَيُّكُمۡ يَأۡتِينِي بِعَرۡشِهَا قَبۡلَ أَن يَأۡتُونِي مُسۡلِمِينَ
38. «እናንተ መኳንንቶች ሆይ! ሙስሊሞች ሆነው ወደ እኔ ሳይመጡ በፊት ዙፋኗን የሚያመጣልኝ ማንኛችሁ ነው?» አለ::
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَ عِفۡرِيتٞ مِّنَ ٱلۡجِنِّ أَنَا۠ ءَاتِيكَ بِهِۦ قَبۡلَ أَن تَقُومَ مِن مَّقَامِكَۖ وَإِنِّي عَلَيۡهِ لَقَوِيٌّ أَمِينٞ
39. ከጋኔን ሃይለኛው «ከችሎትህ ከመነሳትህ በፊት እኔ እርሱን አመጣልሃለሁ:: እኔም በእርሱ ላይ ብርቱ ታማኝ ነኝ።» አለ።
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَ ٱلَّذِي عِندَهُۥ عِلۡمٞ مِّنَ ٱلۡكِتَٰبِ أَنَا۠ ءَاتِيكَ بِهِۦ قَبۡلَ أَن يَرۡتَدَّ إِلَيۡكَ طَرۡفُكَۚ فَلَمَّا رَءَاهُ مُسۡتَقِرًّا عِندَهُۥ قَالَ هَٰذَا مِن فَضۡلِ رَبِّي لِيَبۡلُوَنِيٓ ءَأَشۡكُرُ أَمۡ أَكۡفُرُۖ وَمَن شَكَرَ فَإِنَّمَا يَشۡكُرُ لِنَفۡسِهِۦۖ وَمَن كَفَرَ فَإِنَّ رَبِّي غَنِيّٞ كَرِيمٞ
40. ያ እርሱ ዘንድ ከመጽሐፉ ጥልቅ ዕውቀት ያለው ሰው «የተገለጸው ዓይንህ ወደ አንተ ከመመለሱ በፊት እኔ እርሱን አመጣልሃለሁ።» አለ:: እንደዚሁም አደረገ:: እርሱ ዘንድ ረግቶ ባየዉም ጊዜ «ይህ ከጌታዬ ችሮታ ነው። የማመሰግን ወይም የምክድ መሆኔን ሊሞክረኝ ቸረልኝ:: አላህን ያመሰገነ ሁሉ የሚያመሰግነው ለራሱ ነው:: አላህን የካደም ሰው ሁሉ ጌታዬ ከእርሱ ተብቃቂ፤ ቸር ነው።» አለ::
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَ نَكِّرُواْ لَهَا عَرۡشَهَا نَنظُرۡ أَتَهۡتَدِيٓ أَمۡ تَكُونُ مِنَ ٱلَّذِينَ لَا يَهۡتَدُونَ
41. «ዙፋኗን ለእርሷ አሳስቱ ታውቀው እንደሆነ ወይም ከእነዚያ ከማያውቁት ትሆን እንደሆነ እናያለን።» አላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
فَلَمَّا جَآءَتۡ قِيلَ أَهَٰكَذَا عَرۡشُكِۖ قَالَتۡ كَأَنَّهُۥ هُوَۚ وَأُوتِينَا ٱلۡعِلۡمَ مِن قَبۡلِهَا وَكُنَّا مُسۡلِمِينَ
42. በመጣችም ጊዜ፡- «ዙፋንሽ እንደዚህ ነውን?» ተባለች «እርሱ ልክ እርሱን ነው የመሰለኝ።» አለች። ሱለይማንም አለ: «ከእርሷ በፊትም እውቀትን ተሰጠን:: ሙስሊሞችም ነበርን።
Tafsyrai arabų kalba:
وَصَدَّهَا مَا كَانَت تَّعۡبُدُ مِن دُونِ ٱللَّهِۖ إِنَّهَا كَانَتۡ مِن قَوۡمٖ كَٰفِرِينَ
43. «ከአላህ ሌላ ትገዛው የነበረችውንም ከለከላት:: እርሷ ከከሓዲያን ሕዝቦች ነበረችና።»
Tafsyrai arabų kalba:
قِيلَ لَهَا ٱدۡخُلِي ٱلصَّرۡحَۖ فَلَمَّا رَأَتۡهُ حَسِبَتۡهُ لُجَّةٗ وَكَشَفَتۡ عَن سَاقَيۡهَاۚ قَالَ إِنَّهُۥ صَرۡحٞ مُّمَرَّدٞ مِّن قَوَارِيرَۗ قَالَتۡ رَبِّ إِنِّي ظَلَمۡتُ نَفۡسِي وَأَسۡلَمۡتُ مَعَ سُلَيۡمَٰنَ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
44. «ሕንጻውን ግቢ።» ተባለች:: ባየችዉም ጊዜ ባህር ነው ብላ ጠረጠረችው:: ከባቶቿም ገለጠች:: «እርሱ ከመስተዋት የተለሰለሰ ህንጻ ነው።» አሏት:: «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ ከሱለይማንም ጋር ሆኜ ለዓለማት ጌታ ለአላህ ታዘዝኩኝ።» አለች።
Tafsyrai arabų kalba:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَآ إِلَىٰ ثَمُودَ أَخَاهُمۡ صَٰلِحًا أَنِ ٱعۡبُدُواْ ٱللَّهَ فَإِذَا هُمۡ فَرِيقَانِ يَخۡتَصِمُونَ
45. ወደ ሰሙድም ወንድማቸውን ሷሊህን አላህን ተገዙ በማለት በእርግጥ ላክነው:: ወዲያዉም እነርሱ የሚነታረኩ ሁለት ቡድኖች ሆኑ::
Tafsyrai arabų kalba:
قَالَ يَٰقَوۡمِ لِمَ تَسۡتَعۡجِلُونَ بِٱلسَّيِّئَةِ قَبۡلَ ٱلۡحَسَنَةِۖ لَوۡلَا تَسۡتَغۡفِرُونَ ٱللَّهَ لَعَلَّكُمۡ تُرۡحَمُونَ
46. «ሕዝቦቼ ሆይ! ከመልካሙ በፊት በክፉው ቅጣትን አምጣብን በማለት ለምን ታስቸኩላላችሁ ይታዘንላችሁ ዘንድ አላህን ምህረትን አትለምኑምን?» አላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
قَالُواْ ٱطَّيَّرۡنَا بِكَ وَبِمَن مَّعَكَۚ قَالَ طَٰٓئِرُكُمۡ عِندَ ٱللَّهِۖ بَلۡ أَنتُمۡ قَوۡمٞ تُفۡتَنُونَ
47. «ባንተና ካንተም ጋር ባሉት ሰዎች ምክንያት ገደ ቢሶች ሆንን።» አሉት:: «ገደ ቢስነታችሁ አላህ ዘንድ ነው:: ይልቁንም እናንተ የምትፈተኑ ህዝቦች ናችሁ።» አላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
وَكَانَ فِي ٱلۡمَدِينَةِ تِسۡعَةُ رَهۡطٖ يُفۡسِدُونَ فِي ٱلۡأَرۡضِ وَلَا يُصۡلِحُونَ
48. በከተማይቱም ውስጥ ምድርን የሚያበላሹና የማያሳምሩ ዘጠኝ ሰዎች ነበሩ::
Tafsyrai arabų kalba:
قَالُواْ تَقَاسَمُواْ بِٱللَّهِ لَنُبَيِّتَنَّهُۥ وَأَهۡلَهُۥ ثُمَّ لَنَقُولَنَّ لِوَلِيِّهِۦ مَا شَهِدۡنَا مَهۡلِكَ أَهۡلِهِۦ وَإِنَّا لَصَٰدِقُونَ
49. ዘጠኞቹም «እርሱንና ቤተሰቦቹን ሌሊት እንግደልና ከዚያም ለዘመዱ የቤተሰቦቹን መገደል አላየንም:: እኛም እውነተኞች ነን ልንል በአላህ እንማማል።» አሉ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَكَرُواْ مَكۡرٗا وَمَكَرۡنَا مَكۡرٗا وَهُمۡ لَا يَشۡعُرُونَ
50. ተንኮልንም መከሩ:: እነርሱም የማያውቁ ሲሆኑ በተንኮላቸው ምክኒያት አጠፋናቸው::
Tafsyrai arabų kalba:
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ مَكۡرِهِمۡ أَنَّا دَمَّرۡنَٰهُمۡ وَقَوۡمَهُمۡ أَجۡمَعِينَ
51. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የተንኮላቸዉም መጨረሻ እንዴት እንደ ነበረ እኛ እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም በሙሉ እንዴት እንዳጠፋናቸው ተመልከት::
Tafsyrai arabų kalba:
فَتِلۡكَ بُيُوتُهُمۡ خَاوِيَةَۢ بِمَا ظَلَمُوٓاْۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗ لِّقَوۡمٖ يَعۡلَمُونَ
52. እንዚህም በበደላቸው ምክንያት ባዶዎች ሲሆኑ እነዚህም ቤቶቻቸው ናቸው:: በዚህም ውስጥ ለሚያውቁ ህዝቦች ሁሉ አስደናቂ ተዐምር አለበት::
Tafsyrai arabų kalba:
وَأَنجَيۡنَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَكَانُواْ يَتَّقُونَ
53. እነዚያንም ያመኑትንና ከክህደት ይጠነቀቁ የነበሩትን አዳንን::
Tafsyrai arabų kalba:
وَلُوطًا إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَتَأۡتُونَ ٱلۡفَٰحِشَةَ وَأَنتُمۡ تُبۡصِرُونَ
54. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሉጥንም ለህዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ):: «እናንተ የምታዩ ስትሆኑ መጥፎን ነገር ትሠራላችሁን?
Tafsyrai arabų kalba:
أَئِنَّكُمۡ لَتَأۡتُونَ ٱلرِّجَالَ شَهۡوَةٗ مِّن دُونِ ٱلنِّسَآءِۚ بَلۡ أَنتُمۡ قَوۡمٞ تَجۡهَلُونَ
55. «እናንተ ከሴቶች አልፋችሁ ወንዶችን ለመከጀል ትመጣላችሁን? በእውነቱ እናንተ የምትሳሳቱ ህዝቦች ናችሁ።»
Tafsyrai arabų kalba:
۞ فَمَا كَانَ جَوَابَ قَوۡمِهِۦٓ إِلَّآ أَن قَالُوٓاْ أَخۡرِجُوٓاْ ءَالَ لُوطٖ مِّن قَرۡيَتِكُمۡۖ إِنَّهُمۡ أُنَاسٞ يَتَطَهَّرُونَ
56. የህዝቦቹም መልስ «የሉጥን ቤተሰቦች ከከተማችሁ አውጡ:: እነርሱ የሚጥራሩ ሰዎች ናቸውና።» ማለት እንጂ ሌላ አልነበረም።
Tafsyrai arabų kalba:
فَأَنجَيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ إِلَّا ٱمۡرَأَتَهُۥ قَدَّرۡنَٰهَا مِنَ ٱلۡغَٰبِرِينَ
57. እርሱንና ቤተሰቦቹንም አዳንን:: ሚስቱ ብቻ ስትቀር:: እርሷማ በጥፋቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ አደረግናት::
Tafsyrai arabų kalba:
وَأَمۡطَرۡنَا عَلَيۡهِم مَّطَرٗاۖ فَسَآءَ مَطَرُ ٱلۡمُنذَرِينَ
58. በእነርሱም ላይ የድንጋይ ዝናብን አዘነብንባቸው:: የተስፈራሪዎቹም የቅጣት ዝናብ ከፋ።
Tafsyrai arabų kalba:
قُلِ ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ وَسَلَٰمٌ عَلَىٰ عِبَادِهِ ٱلَّذِينَ ٱصۡطَفَىٰٓۗ ءَآللَّهُ خَيۡرٌ أَمَّا يُشۡرِكُونَ
59. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!)፡- «ምስጋና ሁሉ ለአላህ ይገባው:: በእነዚያም በመረጣቸው ባሮቹ ላይ ሁልጊዜም ሰላም ይውረድ:: አላህ በላጭ ነውን? ወይስ ያ በእርሱ የሚያጋሩት ጣዖት?» በል።
Tafsyrai arabų kalba:
أَمَّنۡ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَ وَأَنزَلَ لَكُم مِّنَ ٱلسَّمَآءِ مَآءٗ فَأَنۢبَتۡنَا بِهِۦ حَدَآئِقَ ذَاتَ بَهۡجَةٖ مَّا كَانَ لَكُمۡ أَن تُنۢبِتُواْ شَجَرَهَآۗ أَءِلَٰهٞ مَّعَ ٱللَّهِۚ بَلۡ هُمۡ قَوۡمٞ يَعۡدِلُونَ
60. ወይስ ያ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረና ከሰማይም ለእናንተ ውሃን ያወረደው ማን ሆነና? በእርሱም ባለ ውበት የሆኑትን የታጠሩ አትክልቶችን ዛፍዋን ልታበቅሉ ለእናንተ ችሎታ ሳይኖራችሁ እኛ ብቻችንን አበቀልን:: ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን? (የለም) ግን እነርሱ ከእውነት የሚያዘነብሉ ህዝቦች ናቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
أَمَّن جَعَلَ ٱلۡأَرۡضَ قَرَارٗا وَجَعَلَ خِلَٰلَهَآ أَنۡهَٰرٗا وَجَعَلَ لَهَا رَوَٰسِيَ وَجَعَلَ بَيۡنَ ٱلۡبَحۡرَيۡنِ حَاجِزًاۗ أَءِلَٰهٞ مَّعَ ٱللَّهِۚ بَلۡ أَكۡثَرُهُمۡ لَا يَعۡلَمُونَ
61. ወይስ ምድርን መርጊያ ያደረገና በመካከሏም ወንዞችን ያደረገ ለእርሷም ጋራዎችን ያደረገ በጣፋጩና በጨዋማው በሁለቱ ባህሮችም መካከል ግርዶን ያደረገ ማን ሆነና? ከአላህ ጋር ሌላ አምላክ አለን? ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም።
Tafsyrai arabų kalba:
أَمَّن يُجِيبُ ٱلۡمُضۡطَرَّ إِذَا دَعَاهُ وَيَكۡشِفُ ٱلسُّوٓءَ وَيَجۡعَلُكُمۡ خُلَفَآءَ ٱلۡأَرۡضِۗ أَءِلَٰهٞ مَّعَ ٱللَّهِۚ قَلِيلٗا مَّا تَذَكَّرُونَ
62. ወይስ ችግረኛን በለመነው ጊዜ የሚቀበል መከራንም የሚያስወግድ በምድርም ላይ ምትኮች የሚደርጋችሁ ማን ሆነና? ከአላህ ጋር ሌላ ትክክለኛ አምላክ አለን? ጥቂትንም አትገሰጹም።
Tafsyrai arabų kalba:
أَمَّن يَهۡدِيكُمۡ فِي ظُلُمَٰتِ ٱلۡبَرِّ وَٱلۡبَحۡرِ وَمَن يُرۡسِلُ ٱلرِّيَٰحَ بُشۡرَۢا بَيۡنَ يَدَيۡ رَحۡمَتِهِۦٓۗ أَءِلَٰهٞ مَّعَ ٱللَّهِۚ تَعَٰلَى ٱللَّهُ عَمَّا يُشۡرِكُونَ
63. ወይስ በየብስና በባህር ጨለማዎች ውስጥ የሚመራችሁ ንፋሶችንም ከዝናቡ በፊት አብሳሪ ሆነው የሚልክ ማን ሆነና? ከአላህ ጋር ሌላ ትክክለኛ አምላክ አለን? አላህ በእርሱ ከሚያጋሯቸው ነገሮች ሁሉ ላቀ።
Tafsyrai arabų kalba:
أَمَّن يَبۡدَؤُاْ ٱلۡخَلۡقَ ثُمَّ يُعِيدُهُۥ وَمَن يَرۡزُقُكُم مِّنَ ٱلسَّمَآءِ وَٱلۡأَرۡضِۗ أَءِلَٰهٞ مَّعَ ٱللَّهِۚ قُلۡ هَاتُواْ بُرۡهَٰنَكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
64. ወይስ መፍጠርን የሚጀምር ከዚያም የሚመልሰው፤ ከሰማይና ከምድርም ሲሳይን የሚሰጣቸሁ አምላክ ማን ሆነና? ከአላህ ጋር ሌላ ትክክለኛ አምላክ አለን? እውነተኞች እንደሆናችሁ አስረጃችሁን አምጡ በላቸው::
Tafsyrai arabų kalba:
قُل لَّا يَعۡلَمُ مَن فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ ٱلۡغَيۡبَ إِلَّا ٱللَّهُۚ وَمَا يَشۡعُرُونَ أَيَّانَ يُبۡعَثُونَ
65. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ ሩቅን ምስጢር አያውቅም:: አላህ ግን ያውቀዋል:: መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም።» በላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
بَلِ ٱدَّٰرَكَ عِلۡمُهُمۡ فِي ٱلۡأٓخِرَةِۚ بَلۡ هُمۡ فِي شَكّٖ مِّنۡهَاۖ بَلۡ هُم مِّنۡهَا عَمُونَ
66. በእውነት የመጨረሻይቱን ዓለም ሁኔታ ማወቃቸው ተሟላን? አይደለም። እነርሱ ከእርሷ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው:: በእውነትም እነርሱ ከእርሷ እውሮች ናቸው::
Tafsyrai arabų kalba:
وَقَالَ ٱلَّذِينَ كَفَرُوٓاْ أَءِذَا كُنَّا تُرَٰبٗا وَءَابَآؤُنَآ أَئِنَّا لَمُخۡرَجُونَ
67. እነዚያም በአላህ የካዱት አሉ፡- «እኛም አባቶቻችንም ዐፈር በሆንን ጊዜ እንደ ገና ከመቃብር የምንወጣ ነን?
Tafsyrai arabų kalba:
لَقَدۡ وُعِدۡنَا هَٰذَا نَحۡنُ وَءَابَآؤُنَا مِن قَبۡلُ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّآ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
68. «ይህንን እኛም ሆነ ከእኛ በፊትም የነበሩት አባቶቻችን በእርግጥ ተቀጥረንበታል:: ይህ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች እንጂ ሌላ አይደለም።» አሉ።
Tafsyrai arabų kalba:
قُلۡ سِيرُواْ فِي ٱلۡأَرۡضِ فَٱنظُرُواْ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
69. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «በምድር ላይ ሂዱ የአመጸኞችም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልክቱ።» በላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
وَلَا تَحۡزَنۡ عَلَيۡهِمۡ وَلَا تَكُن فِي ضَيۡقٖ مِّمَّا يَمۡكُرُونَ
70. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በእነርሱም ላይ አትዘን:: ከሚመክሩብህም ነገር በጭንቀት ውስጥ አትሁን::
Tafsyrai arabų kalba:
وَيَقُولُونَ مَتَىٰ هَٰذَا ٱلۡوَعۡدُ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
71. «እውነተኞችም እንደሆናችሁ ይህ ቀጠሮ መቼ ነው?» ይላሉ።
Tafsyrai arabų kalba:
قُلۡ عَسَىٰٓ أَن يَكُونَ رَدِفَ لَكُم بَعۡضُ ٱلَّذِي تَسۡتَعۡجِلُونَ
72. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «የዚያ የምትቻኮሉበት ከፊሉ ለእናንተ የቀረበ መሆኑ ተረጋግጧል።» በላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَذُو فَضۡلٍ عَلَى ٱلنَّاسِ وَلَٰكِنَّ أَكۡثَرَهُمۡ لَا يَشۡكُرُونَ
73. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጌታህም በሰዎች ላይ በእርግጥ የችሮታ ባለቤት ነው:: ግን አብዛኛዎቻቸው አያመሰግኑም::
Tafsyrai arabų kalba:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَيَعۡلَمُ مَا تُكِنُّ صُدُورُهُمۡ وَمَا يُعۡلِنُونَ
74. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጌታህም ልቦቻቸው የሚደብቁትንና የሚገልጹትን ያውቃል::
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَا مِنۡ غَآئِبَةٖ فِي ٱلسَّمَآءِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّا فِي كِتَٰبٖ مُّبِينٍ
75. በሰማይም ሆነ በምድር ውስጥ ምንም የተደበቀ ነገር የለም:: ገላጭ በሆነው መጽሐፍ ውስጥ ያለ ቢሆን እንጂ::
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّ هَٰذَا ٱلۡقُرۡءَانَ يَقُصُّ عَلَىٰ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ أَكۡثَرَ ٱلَّذِي هُمۡ فِيهِ يَخۡتَلِفُونَ
76. ይህ ቁርኣን እነዚያ የኢስራኢል ልጆች እነርሱ በእርሱ ላይ የሚለያዩበትን ጉዳይ አብዛኛውን ይነግራል::
Tafsyrai arabų kalba:
وَإِنَّهُۥ لَهُدٗى وَرَحۡمَةٞ لِّلۡمُؤۡمِنِينَ
77. እርሱም ለአማኞች ብቸኛ መምሪያና እዝነት ነው::
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّ رَبَّكَ يَقۡضِي بَيۡنَهُم بِحُكۡمِهِۦۚ وَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلۡعَلِيمُ
78. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጌታህ በመካከላቸው በትክክል ፍርዱ ይፈርዳል፤ እርሱም ሁሉን አሸናፊዉና አዋቂው ነው።
Tafsyrai arabų kalba:
فَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱللَّهِۖ إِنَّكَ عَلَى ٱلۡحَقِّ ٱلۡمُبِينِ
79. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በአላህም ላይ ተጠጋ:: አንተ ግልጽ በሆነው እውነት ላይ ነህና።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّكَ لَا تُسۡمِعُ ٱلۡمَوۡتَىٰ وَلَا تُسۡمِعُ ٱلصُّمَّ ٱلدُّعَآءَ إِذَا وَلَّوۡاْ مُدۡبِرِينَ
80. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንተ ሙታንን አታሰማም። ደንቆሮዎችንም የሚተው ሆነው በዞሩ ጊዜ ጥሪን አታሰማም።
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَآ أَنتَ بِهَٰدِي ٱلۡعُمۡيِ عَن ضَلَٰلَتِهِمۡۖ إِن تُسۡمِعُ إِلَّا مَن يُؤۡمِنُ بِـَٔايَٰتِنَا فَهُم مُّسۡلِمُونَ
81.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) አንተም ልበ ዕውሮችን ከጥመታቸው አቅኚ አይደለህም:: እነዚያን በአናቅጻችን በትክክል የሚያምኑትን እንጂ አታሰማም:: እነርሱ ፍጹም ታዛዦች (ሙስሊሞች) ናቸውና።
Tafsyrai arabų kalba:
۞ وَإِذَا وَقَعَ ٱلۡقَوۡلُ عَلَيۡهِمۡ أَخۡرَجۡنَا لَهُمۡ دَآبَّةٗ مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ تُكَلِّمُهُمۡ أَنَّ ٱلنَّاسَ كَانُواْ بِـَٔايَٰتِنَا لَا يُوقِنُونَ
82. በእነርሱም ላይ የቅጣት ቃሉ በተረጋገጠ ጊዜ ሰዎቹ በአናቅጻችን የማያረጋግጡ እንደነበሩ የምትነግራቸውን እንስሳ ለእነርሱ ከምድር እናወጣላቸዋለን::
Tafsyrai arabų kalba:
وَيَوۡمَ نَحۡشُرُ مِن كُلِّ أُمَّةٖ فَوۡجٗا مِّمَّن يُكَذِّبُ بِـَٔايَٰتِنَا فَهُمۡ يُوزَعُونَ
83. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሕዝቦቹም ሁሉ በአናቅጽ የሚያስተባብሉትን ቡድኖች የምንሰበስብበትን ቀን አስታውስ:: እነርሱም ይከመከማሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
حَتَّىٰٓ إِذَا جَآءُو قَالَ أَكَذَّبۡتُم بِـَٔايَٰتِي وَلَمۡ تُحِيطُواْ بِهَا عِلۡمًا أَمَّاذَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
84. በመጡም ጊዜ (አላህ) ይላቸዋል፡ «በአንቀጾቼ እርሷን በማወቅ ያላዳረሳችሁ ስትሆኑ አስተባበላችሁን? ወይስ ምንን ትሰሩ ነበራችሁ?»
Tafsyrai arabų kalba:
وَوَقَعَ ٱلۡقَوۡلُ عَلَيۡهِم بِمَا ظَلَمُواْ فَهُمۡ لَا يَنطِقُونَ
85. በመበደላቸዉም ምክኒያት በእነርሱ ላይ ቃሉ ይፈጸምባቸዋል:: እነርሱም አይናገሩም::
Tafsyrai arabų kalba:
أَلَمۡ يَرَوۡاْ أَنَّا جَعَلۡنَا ٱلَّيۡلَ لِيَسۡكُنُواْ فِيهِ وَٱلنَّهَارَ مُبۡصِرًاۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَٰتٖ لِّقَوۡمٖ يُؤۡمِنُونَ
86. እኛ ሌሊትን በእርሱ ውስጥ እንደሚያርፉበት ቀንንም የሚያሳይ እንዳደረግን አያዩምን? ለሚያምኑ ሕዝቦች በዚህ ውስጥ አያሌ ተዓምራት አሉበት::
Tafsyrai arabų kalba:
وَيَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِ فَفَزِعَ مَن فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَن فِي ٱلۡأَرۡضِ إِلَّا مَن شَآءَ ٱللَّهُۚ وَكُلٌّ أَتَوۡهُ دَٰخِرِينَ
87. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በቀንዱም በሚነፋ ቀን በሰማያት ውስጥ ያሉትና በምድርም ውስጥ ያሉት ሁሉ አላህ የሻው ነገር ብቻ ሲቀር በሚደነግጡ ጊዜ የሚሆነውን አስታውስ። ሁሉም የተናነሱ ሆነዉም ወደ እርሱ ይመጣሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
وَتَرَى ٱلۡجِبَالَ تَحۡسَبُهَا جَامِدَةٗ وَهِيَ تَمُرُّ مَرَّ ٱلسَّحَابِۚ صُنۡعَ ٱللَّهِ ٱلَّذِيٓ أَتۡقَنَ كُلَّ شَيۡءٍۚ إِنَّهُۥ خَبِيرُۢ بِمَا تَفۡعَلُونَ
88. ጋራዎችንም እርሷ እንደ ደመና አስተላለፍ የምታልፍ ስትሆን የቆመች ናት ብለህ የምታስባት ሆና ታያለህ፤ የዚያን ነገሩን ሁሉ ያጠነከረውን የአላህን ጥበብ ተመልከት:: እርሱ በምትሠሩት ሁሉ ውስጥ አዋቂ ነው::
Tafsyrai arabų kalba:
مَن جَآءَ بِٱلۡحَسَنَةِ فَلَهُۥ خَيۡرٞ مِّنۡهَا وَهُم مِّن فَزَعٖ يَوۡمَئِذٍ ءَامِنُونَ
89. መልካም ሥራን የሰራ ለእርሱ ከእርሷ የበለጠ ምንዳ አለው:: እነርሱም በዚያ ቀን ከድንጋጤ ነፃ ናቸው::
Tafsyrai arabų kalba:
وَمَن جَآءَ بِٱلسَّيِّئَةِ فَكُبَّتۡ وُجُوهُهُمۡ فِي ٱلنَّارِ هَلۡ تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
90. መጥፎንም የሰሩ ፊቶቻቸው በእሳት ውስጥ ይደፋሉ። «ትሠሩት የነበራችሁትን እንጂ አትመነዱም» ይበላሉ።
Tafsyrai arabų kalba:
إِنَّمَآ أُمِرۡتُ أَنۡ أَعۡبُدَ رَبَّ هَٰذِهِ ٱلۡبَلۡدَةِ ٱلَّذِي حَرَّمَهَا وَلَهُۥ كُلُّ شَيۡءٖۖ وَأُمِرۡتُ أَنۡ أَكُونَ مِنَ ٱلۡمُسۡلِمِينَ
91. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! በላቸው:) «የታዘዝኩት የዚህችን አገር የመካን ጌታ ያንን ክልክል ያደረጋትንም አላህን እንድገዛ ብቻ ነው:: ነገሩም ሁሉ የእርሱ ነው:: ከሙስሊሞችም እንድሆን ታዝዣለሁ።
Tafsyrai arabų kalba:
وَأَنۡ أَتۡلُوَاْ ٱلۡقُرۡءَانَۖ فَمَنِ ٱهۡتَدَىٰ فَإِنَّمَا يَهۡتَدِي لِنَفۡسِهِۦۖ وَمَن ضَلَّ فَقُلۡ إِنَّمَآ أَنَا۠ مِنَ ٱلۡمُنذِرِينَ
92. «ቁርኣንንም እንዳነብ ታዝዣለሁ:: በቀጥተኛው መንገድ የተመራ ሁሉ የሚመራው ለራሱ ብቻ ነው:: የተሳሳተም እኔ ከአስፈራሪዎች ነኝ እንጂ ሌላ አይደለሁም።» በላቸው።
Tafsyrai arabų kalba:
وَقُلِ ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ سَيُرِيكُمۡ ءَايَٰتِهِۦ فَتَعۡرِفُونَهَاۚ وَمَا رَبُّكَ بِغَٰفِلٍ عَمَّا تَعۡمَلُونَ
93. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «ምስጋናም ሁሉ ለአላህ ብቻ ነው:: ተአምራቱን ወደ ፊት ያሳያችኋል:: ታውቋታላችሁም።» በላቸው:: ጌታህ ከምትሠሩት ነገር ሁሉ ዘንጊ አይደለም።
Tafsyrai arabų kalba:
 
Reikšmių vertimas Sūra: Sūra An-Naml
Sūrų turinys Puslapio numeris
 
Kilniojo Korano reikšmių vertimas - Amharų k. vertimas - Zain - Vertimų turinys

Amharų k. vertimas

Uždaryti