Check out the new design

Kilniojo Korano reikšmių vertimas - Vertimas į amharų k. - Afrikos akademija * - Vertimų turinys


Reikšmių vertimas Sūra: Al-A’raf   Aja (Korano eilutė):
وَنَادَىٰٓ أَصۡحَٰبُ ٱلۡجَنَّةِ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ أَن قَدۡ وَجَدۡنَا مَا وَعَدَنَا رَبُّنَا حَقّٗا فَهَلۡ وَجَدتُّم مَّا وَعَدَ رَبُّكُمۡ حَقّٗاۖ قَالُواْ نَعَمۡۚ فَأَذَّنَ مُؤَذِّنُۢ بَيۡنَهُمۡ أَن لَّعۡنَةُ ٱللَّهِ عَلَى ٱلظَّٰلِمِينَ
44. የገነት ሰዎች የእሳት ሰዎችን «ጌታችን ቃል የገባልንን እውነት ሆኖ አገኘን እናንተስ ጌታችሁ የዛተባችሁን እውነት ሆኖ አገኛችሁትን?» ሲሉ ይጣራሉ:: የእሳት ሰዎችም «አዎን አገኘን» ይላሉ:: በመካከላቸዉም «የአላህ እርግማን በበደለኞች ላይ ይሁን» ሲል አዋጅ ነጋሪ ያውጃል::
Tafsyrai arabų kalba:
ٱلَّذِينَ يَصُدُّونَ عَن سَبِيلِ ٱللَّهِ وَيَبۡغُونَهَا عِوَجٗا وَهُم بِٱلۡأٓخِرَةِ كَٰفِرُونَ
45. በደለኞች ማለት እነዚያ ከአላህ መንገድ ሌሎችን ክፍሎች የሚከለክሉና የአላህ መንገድ እንድትጣመም የሚፈልጉ በመጨረሻዋ ዓለም ከሓዲያን የሆኑ ሰዎች ብቻ ናቸው::
Tafsyrai arabų kalba:
وَبَيۡنَهُمَا حِجَابٞۚ وَعَلَى ٱلۡأَعۡرَافِ رِجَالٞ يَعۡرِفُونَ كُلَّۢا بِسِيمَىٰهُمۡۚ وَنَادَوۡاْ أَصۡحَٰبَ ٱلۡجَنَّةِ أَن سَلَٰمٌ عَلَيۡكُمۡۚ لَمۡ يَدۡخُلُوهَا وَهُمۡ يَطۡمَعُونَ
46. በገነት ሰዎችና በገሀነም ሰዎች መካከል አዕራፍ የሚባል ከባድ መጋረጃ አለ:: በአዕራፍ ላይ ሁሉንም በምልክታቸው የሚያውቁ ሰዎች አሉ:: የገነትን ሰዎችን «ሰላም ለእናንተ ይሁን» በማለት ይጣራሉ:: የአዕራፍ ሰዎች ገነት መግባትን የሚከጅሉ ሲሆኑ ገና እንዲገቡ አልተደረጉም::
Tafsyrai arabų kalba:
۞ وَإِذَا صُرِفَتۡ أَبۡصَٰرُهُمۡ تِلۡقَآءَ أَصۡحَٰبِ ٱلنَّارِ قَالُواْ رَبَّنَا لَا تَجۡعَلۡنَا مَعَ ٱلۡقَوۡمِ ٱلظَّٰلِمِينَ
47. ዓይኖቻቸው ወደ እሳት ሰዎች አቅጣጫ በተዞሩ ጊዜም፡- «ጌታችን ሆይ! እባክህ ከበደለኞች ጋር አታድርገን።» ይላሉ::
Tafsyrai arabų kalba:
وَنَادَىٰٓ أَصۡحَٰبُ ٱلۡأَعۡرَافِ رِجَالٗا يَعۡرِفُونَهُم بِسِيمَىٰهُمۡ قَالُواْ مَآ أَغۡنَىٰ عَنكُمۡ جَمۡعُكُمۡ وَمَا كُنتُمۡ تَسۡتَكۡبِرُونَ
48. የአዕራፍ ሰዎች በምልክታቸው የሚያውቋቸውን ታላላቅ ሰዎች ይጠራሉ:: «ክምችታችሁና (ብዛታችሁና) ኩራታችሁ ምን ጠቀማችሁ?» ይሏቸዋል::
Tafsyrai arabų kalba:
أَهَٰٓؤُلَآءِ ٱلَّذِينَ أَقۡسَمۡتُمۡ لَا يَنَالُهُمُ ٱللَّهُ بِرَحۡمَةٍۚ ٱدۡخُلُواْ ٱلۡجَنَّةَ لَا خَوۡفٌ عَلَيۡكُمۡ وَلَآ أَنتُمۡ تَحۡزَنُونَ
49. «እነዚያ የአላህ ችሮታው አይደርሳቸዉም ብላችሁ የማላችሁት ወገኖች ናቸውን? ገነትን ግቡ:: (አሁን ግን) ፍርሃት የለባችሁም:: እናንተም አታዝኑም።» (ተባሉ ይሏቸዋል::)
Tafsyrai arabų kalba:
وَنَادَىٰٓ أَصۡحَٰبُ ٱلنَّارِ أَصۡحَٰبَ ٱلۡجَنَّةِ أَنۡ أَفِيضُواْ عَلَيۡنَا مِنَ ٱلۡمَآءِ أَوۡ مِمَّا رَزَقَكُمُ ٱللَّهُۚ قَالُوٓاْ إِنَّ ٱللَّهَ حَرَّمَهُمَا عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ
50. የእሳት ሰዎች የገነት ሰዎችን «በእኛ ላይ ውሃ ወይም አላህ ከሰጣችሁ ሲሳይ እባካችሁ ጣሉልን (አፍስሱልን)።» ብለው ይጠሯቸዋል:: የገነት ሰዎችም «እነዚህ ሲሳዮች እኮ አላህ በከሓዲያን ላይ እርም አድርጓቸዋል።» ይሏቸዋል።
Tafsyrai arabų kalba:
ٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ دِينَهُمۡ لَهۡوٗا وَلَعِبٗا وَغَرَّتۡهُمُ ٱلۡحَيَوٰةُ ٱلدُّنۡيَاۚ فَٱلۡيَوۡمَ نَنسَىٰهُمۡ كَمَا نَسُواْ لِقَآءَ يَوۡمِهِمۡ هَٰذَا وَمَا كَانُواْ بِـَٔايَٰتِنَا يَجۡحَدُونَ
51. ለእነዚያ ሃይማኖታቸውን መሳለቂያና መጫወቻ አድርገው የያዙና የቅርቢቱ ህይወት ያታለለቻቸው የዚህን ቀን መገናኘታቸውን እንደ ረሱና በተአምራታችን ይክዱ እንደ ነበሩ ሁሉ ዛሬ እኛም እንረሳቸዋለን (እንተዋቸዋለን)::
Tafsyrai arabų kalba:
 
Reikšmių vertimas Sūra: Al-A’raf
Sūrų turinys Puslapio numeris
 
Kilniojo Korano reikšmių vertimas - Vertimas į amharų k. - Afrikos akademija - Vertimų turinys

Išvertė Muchamed Zain Zahr Ad-Din. Išleido Afrikos akademija.

Uždaryti