Check out the new design

Kur'an-ı Kerim meal tercümesi - Amharca Tercüme - Afrika Akademisi * - Mealler fihristi


Anlam tercümesi Sure: Sûratu's-Saffât   Ayet:
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
25. ለነርሱም «ምን ሆናችሁ ነው የማትረዳዱት?» ይባላሉ።
Arapça tefsirler:
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ማምለጫ የሌላቸው ወራዳዎች ናቸው::
Arapça tefsirler:
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
27. እርስ በራሳቸውም የሚወቃቀሱም ሆነው ይመጣሉ።
Arapça tefsirler:
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
28. (ተከታዮቹ ለአስከታዮቻቸው) «እናንተ በጉልበት ትመጡብን ነበር» ይላሉ።
Arapça tefsirler:
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
29. (አስከታዮቹም) ይላሉ፡- «አይደለም ፈጽሞ አማኞች አልነበራችሁም።
Arapça tefsirler:
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
30. «ለእኛም በናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም። በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ህዝቦች ነበራችሁና ነው እንጂ።
Arapça tefsirler:
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል የተረጋገጠብንና ሁላችንም ቅጣቱን ቀማሽ ነን።
Arapça tefsirler:
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
32. «እኛ ጠማሞች ስለ ነበርን ወደ ጥመት ጠራናችሁም።» ይላሉ።
Arapça tefsirler:
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው::
Arapça tefsirler:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሰራለን።
Arapça tefsirler:
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
35. እነርሱ «ከአላህ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።
Arapça tefsirler:
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
36. «እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።
Arapça tefsirler:
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
37. አይደለም እውነቱን ሃይማኖት አመጣ፤ መልዕክተኞቹንም እውነተኝነታቸውን አረጋገጠ።
Arapça tefsirler:
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት እርግጥ ቀማሾች ናችሁ::
Arapça tefsirler:
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
39. ትሰሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም::
Arapça tefsirler:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ቅጣትን አይቀምሱም::
Arapça tefsirler:
أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አለላቸው::
Arapça tefsirler:
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
42. ፍራፋሬዎች (አሉላቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው::
Arapça tefsirler:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
43. በድሎት ገነቶች ውስጥ::
Arapça tefsirler:
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
44. ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ ይንፈላሰሳሉ::
Arapça tefsirler:
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዙ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል::
Arapça tefsirler:
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ
46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከሆነች፤
Arapça tefsirler:
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
47. በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም:: እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም::
Arapça tefsirler:
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
48. እነርሱ ዘንድ ዓይናቸውን በባሎቻቸው ላይ ብቻ አሳጣሪዎች የሆኑ ዓይናማ ሴቶች አሉ::
Arapça tefsirler:
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) እንቁላል ይመስላሉ::
Arapça tefsirler:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
50. የሚጠያያቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ::
Arapça tefsirler:
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ (እንዲህ) ይላል: «እኔ ጓደኛ ነበረኝ።
Arapça tefsirler:
 
Anlam tercümesi Sure: Sûratu's-Saffât
Surelerin fihristi Sayfa numarası
 
Kur'an-ı Kerim meal tercümesi - Amharca Tercüme - Afrika Akademisi - Mealler fihristi

Muhammed Zeyn Zehruddin Tercümesi. Afrika Akademisi Tarafından Yayınlandı.

Kapat