আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ * - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ইনশ্বিক্বাক্ব   আয়াত:

ሱረቱ አል ኢንሺቃቅ

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنشَقَّتۡ
ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ
ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَإِذَا ٱلۡأَرۡضُ مُدَّتۡ
ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَلۡقَتۡ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتۡ
በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَذِنَتۡ لِرَبِّهَا وَحُقَّتۡ
ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَىٰ رَبِّكَ كَدۡحٗا فَمُلَٰقِيهِ
አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ بِيَمِينِهِۦ
መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَوۡفَ يُحَاسَبُ حِسَابٗا يَسِيرٗا
በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَيَنقَلِبُ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورٗا
ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَمَّا مَنۡ أُوتِيَ كِتَٰبَهُۥ وَرَآءَ ظَهۡرِهِۦ
መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَوۡفَ يَدۡعُواْ ثُبُورٗا
(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَيَصۡلَىٰ سَعِيرًا
የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُۥ كَانَ فِيٓ أَهۡلِهِۦ مَسۡرُورًا
እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُۥ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ
እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بَلَىٰٓۚ إِنَّ رَبَّهُۥ كَانَ بِهِۦ بَصِيرٗا
አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلشَّفَقِ
(አትካዱ)፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلَّيۡلِ وَمَا وَسَقَ
በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلۡقَمَرِ إِذَا ٱتَّسَقَ
በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَتَرۡكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٖ
ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَمَا لَهُمۡ لَا يُؤۡمِنُونَ
የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَإِذَا قُرِئَ عَلَيۡهِمُ ٱلۡقُرۡءَانُ لَا يَسۡجُدُونَۤ۩
በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?) {1}
{1} እዚህ አንድ የትላዋ ሱጁድ ይደረጋል።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بَلِ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ يُكَذِّبُونَ
በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱللَّهُ أَعۡلَمُ بِمَا يُوعُونَ
አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَبَشِّرۡهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ
በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَهُمۡ أَجۡرٌ غَيۡرُ مَمۡنُونِۭ
ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
 
অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ইনশ্বিক্বাক্ব
ছুৰাৰ তালিকা পৃষ্ঠা নং
 
আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - আমহাৰী অনুবাদ - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الامهرية، ترجمها الشيخ محمد صادق ومحمد الثاني حبيب. تم تصويبها بإشراف مركز رواد الترجمة، ويتاح الإطلاع على الترجمة الأصلية لغرض إبداء الرأي والتقييم والتطوير المستمر.

বন্ধ