আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - الترجمة الأمهرية - زين * - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ


অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ৱাক্বিয়াহ   আয়াত:

ሱረቱ አል ዋቂዓህ

إِذَا وَقَعَتِ ٱلۡوَاقِعَةُ
1. ተጨባጪቱ (ቂያማ) እውን በሆነች ጊዜ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَيۡسَ لِوَقۡعَتِهَا كَاذِبَةٌ
2. (ቂያማ) እውን ለመሆኗ አንዲትም አስተባባይ ነፍስ የለችም።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
خَافِضَةٞ رَّافِعَةٌ
3. እርሷ (ገሚሱን) ዝቅ አድራጊና (ገሚሱን) ደግሞ ከፍ አድራጊ ናት::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِذَا رُجَّتِ ٱلۡأَرۡضُ رَجّٗا
4. ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَبُسَّتِ ٱلۡجِبَالُ بَسّٗا
5. ተራራዎች (እንደተፈጨ ዱቄት) መፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَكَانَتۡ هَبَآءٗ مُّنۢبَثّٗا
6. የተበተነ ብናኝ በሆኑም ጊዜ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكُنتُمۡ أَزۡوَٰجٗا ثَلَٰثَةٗ
7. እናንተ (ሰዎች) ሶስት ዓይነቶችም በሆናችሁ ጊዜ (ገሚሱን ዝቅ እና ገሚሱን ከፍ ታደርጋለች)::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَيۡمَنَةِ
8. እናም በዚያ ቀን የቀኝ ጓዶች ለመሆን የበቁ ሁሉ ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡمَشۡـَٔمَةِ
9. የግራ ጓዶች ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَٱلسَّٰبِقُونَ ٱلسَّٰبِقُونَ
10. እነዚያ (ለበጎ ስራ) ቀዳሚዎች የሆኑ ሁሉ (ለገነትም) ቀዳሚዎች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أُوْلَٰٓئِكَ ٱلۡمُقَرَّبُونَ
11. እነዚያ (በአላህ ዘንድም) ባለሟሎች ናቸው
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
12. በመደሰቻ ገነቶች ውስጥ ሲሆኑ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
13. (የዚህ እድል ባለ ቤቶች) ከፊተኞቹ ብዙ ቡድኖች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَقَلِيلٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ
14. ከኋለኞቹ ግን ጥቂቶች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَلَىٰ سُرُرٖ مَّوۡضُونَةٖ
15. በተሸሞኑ አልጋዎች ላይ ይሆናሉ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
مُّتَّكِـِٔينَ عَلَيۡهَا مُتَقَٰبِلِينَ
16. በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲሆኑ።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
يَطُوفُ عَلَيۡهِمۡ وِلۡدَٰنٞ مُّخَلَّدُونَ
17. እነርሱን (ለማገለገል) በእነርሱ ዙሪያ ሁልጊዜ የማያረጁ ወጣት ልጆች ይዘዋወራሉ።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بِأَكۡوَابٖ وَأَبَارِيقَ وَكَأۡسٖ مِّن مَّعِينٖ
18. ከ(ጠጅ) ምንጭ በብርጨቆዎች፣ በኩስኩስቶችና (እብሪቆች) በጽዋም በእነርሱ ዙሪያ እንዲዞሩ ይደረጋሉ።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا يُصَدَّعُونَ عَنۡهَا وَلَا يُنزِفُونَ
19. ከእርሷ የራስ ምታት እንኳን አያገኛቸዉም:: አይሰክሩምም::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفَٰكِهَةٖ مِّمَّا يَتَخَيَّرُونَ
20. ከእሸቶች ከሚመርጡት ዓይነት
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَحۡمِ طَيۡرٖ مِّمَّا يَشۡتَهُونَ
21. ከሚፈልጉት የበራሪ ስጋ ይዘው ይዞሩላቸዋል::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَحُورٌ عِينٞ
22. ዓይናማዎች የሆኑ ነጫጭ ቆንጆ ሴቶችም አሏቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
كَأَمۡثَٰلِ ٱللُّؤۡلُوِٕ ٱلۡمَكۡنُونِ
23. ልክ እንደተሸፈነ ሉል የሚመስሉ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
جَزَآءَۢ بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
24. ለዚያ ይሰሩት በነበሩት መልካም ተግባር ምክንያት ዋጋ ይሆን ዘንድ ይህንን አደረግንላቸው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَا يَسۡمَعُونَ فِيهَا لَغۡوٗا وَلَا تَأۡثِيمًا
25. በውስጧ ውድቅ ንግግርንና መወንጀልንም አይሰሙም።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِلَّا قِيلٗا سَلَٰمٗا سَلَٰمٗا
26. ሰላም ሰላም መባባልን ግን ይሰማሉ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلۡيَمِينِ
27. የቀኝ ጓዶች ምንኛ የከበሩ የቀኝ ጓዶች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي سِدۡرٖ مَّخۡضُودٖ
28. በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَطَلۡحٖ مَّنضُودٖ
29. ፍሬው በተነባበረ ሙዝ ዛፍም ውስጥ ናቸው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَظِلّٖ مَّمۡدُودٖ
30. በተዘረጋ ጥላ ስርም ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَمَآءٖ مَّسۡكُوبٖ
31. በሚንቧቡ ውሃ አጠገብም ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفَٰكِهَةٖ كَثِيرَةٖ
32. በብዙ ዓይነት ፍራፍሬዎችም ውስጥ ናቸው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا مَقۡطُوعَةٖ وَلَا مَمۡنُوعَةٖ
33. ምንጊዜም የማትቋረጥ የማትከለከልም የሆነች፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَفُرُشٖ مَّرۡفُوعَةٍ
34. ከፍ በተደረጉ ምንጣፎች ላይም ናቸው።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّآ أَنشَأۡنَٰهُنَّ إِنشَآءٗ
35. እኛ (የገነት ሴቶችን) አዲስ ፍጥረት አድርገን ፈጠርናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَجَعَلۡنَٰهُنَّ أَبۡكَارًا
36. እናም ደናግሎችም አደረግናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عُرُبًا أَتۡرَابٗا
37. ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎችና እኩያዎች አደረግናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لِّأَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
38. ለቀኝ ጓዶች አዘጋጀናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
39. ከፊተኞቹ ብዙ ቡድኖች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَثُلَّةٞ مِّنَ ٱلۡأٓخِرِينَ
40. ከኋለኞቹም ብዙ ቡድኖች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ مَآ أَصۡحَٰبُ ٱلشِّمَالِ
41. የግራ ጓዶችም ምንኛ የተዋረዱ የግራ ጓዶች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي سَمُومٖ وَحَمِيمٖ
42. በመርዛም ንፋስና በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَظِلّٖ مِّن يَحۡمُومٖ
43. ከጥቁር ጭስም በሆነ ጥላ ውስጥ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا بَارِدٖ وَلَا كَرِيمٍ
44. ቀዝቃዛም መልካምም ያልሆነ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُمۡ كَانُواْ قَبۡلَ ذَٰلِكَ مُتۡرَفِينَ
45. እነርሱ ከዚህ በፊት የነብያትን አስተምህሮት ወደ ጎን የተው የዱንያ ቅምጥሎች ነበሩና::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكَانُواْ يُصِرُّونَ عَلَى ٱلۡحِنثِ ٱلۡعَظِيمِ
46. በከባድ ኃጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَكَانُواْ يَقُولُونَ أَئِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
47. (እንዲህ) ይሉ ነበርም፡ "ሞተን አፈር፣ አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
48. "የፊተኞቹ አባቶቻችንንም (ይቀሰቀሳሉን)?" (ይሉ ነበር)
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
قُلۡ إِنَّ ٱلۡأَوَّلِينَ وَٱلۡأٓخِرِينَ
49. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) "ፊተኞቹም ሆኑ ኋለኞቹ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَمَجۡمُوعُونَ إِلَىٰ مِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
50. "በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው" በላቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ثُمَّ إِنَّكُمۡ أَيُّهَا ٱلضَّآلُّونَ ٱلۡمُكَذِّبُونَ
51. ከዚያም እናንተ ጠማሞችና አስተባባዩች ሆይ!
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَأٓكِلُونَ مِن شَجَرٖ مِّن زَقُّومٖ
52. ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
53. ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَشَٰرِبُونَ عَلَيۡهِ مِنَ ٱلۡحَمِيمِ
54. በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَشَٰرِبُونَ شُرۡبَ ٱلۡهِيمِ
55. የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናቸው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
هَٰذَا نُزُلُهُمۡ يَوۡمَ ٱلدِّينِ
56. ይህ የፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَحۡنُ خَلَقۡنَٰكُمۡ فَلَوۡلَا تُصَدِّقُونَ
57. (ሰዎች ሆይ!) እኛ ፈጠርናችሁ አታምኑምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُم مَّا تُمۡنُونَ
58. በሴቶች ማህጸኖች የምታፈሱትን (የምትረጩትን ፍትወት) አያችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ تَخۡلُقُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡخَٰلِقُونَ
59. እናንተ ትፈጥሩታላችሁን! ወይስ እኛ ነን ፈጣሪዎቹ?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَحۡنُ قَدَّرۡنَا بَيۡنَكُمُ ٱلۡمَوۡتَ وَمَا نَحۡنُ بِمَسۡبُوقِينَ
60. እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
عَلَىٰٓ أَن نُّبَدِّلَ أَمۡثَٰلَكُمۡ وَنُنشِئَكُمۡ فِي مَا لَا تَعۡلَمُونَ
61. ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም ቅርጽ እናንተኑ በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَلَقَدۡ عَلِمۡتُمُ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُولَىٰ فَلَوۡلَا تَذَكَّرُونَ
62. የፊተኛይቱን አፈጣጠር በእርግጥ አውቃችኋል አትገነዘቡምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُم مَّا تَحۡرُثُونَ
63. የምትዘሩትን (አዝርአት) አያችሁን
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ تَزۡرَعُونَهُۥٓ أَمۡ نَحۡنُ ٱلزَّٰرِعُونَ
64. እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَوۡ نَشَآءُ لَجَعَلۡنَٰهُ حُطَٰمٗا فَظَلۡتُمۡ تَفَكَّهُونَ
65. ብንሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባረደግነው እና የምትደነቁም በሆናችሁ ነበር::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّا لَمُغۡرَمُونَ
66. "እኛ በእዳ ተያዥዎች ነን::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
بَلۡ نَحۡنُ مَحۡرُومُونَ
67. "በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለክልን ነን" ትሉ ነበር።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلۡمَآءَ ٱلَّذِي تَشۡرَبُونَ
68. ያንን ምትጠጡትን ውሃ አያችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ أَنزَلۡتُمُوهُ مِنَ ٱلۡمُزۡنِ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنزِلُونَ
69. እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَوۡ نَشَآءُ جَعَلۡنَٰهُ أُجَاجٗا فَلَوۡلَا تَشۡكُرُونَ
70. ብንፈልግ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር:: አታመሰግኑምን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱلنَّارَ ٱلَّتِي تُورُونَ
71. ያችንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
ءَأَنتُمۡ أَنشَأۡتُمۡ شَجَرَتَهَآ أَمۡ نَحۡنُ ٱلۡمُنشِـُٔونَ
72. እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹ ነን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
نَحۡنُ جَعَلۡنَٰهَا تَذۡكِرَةٗ وَمَتَٰعٗا لِّلۡمُقۡوِينَ
73. እኛ ለገሀነም ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
74. የታላቁን ጌታህንም ስም አጥራው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
۞ فَلَآ أُقۡسِمُ بِمَوَٰقِعِ ٱلنُّجُومِ
75. በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَإِنَّهُۥ لَقَسَمٞ لَّوۡ تَعۡلَمُونَ عَظِيمٌ
76. እርሱም ብታውቁ ታላቅ መሀላ ነው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّهُۥ لَقُرۡءَانٞ كَرِيمٞ
77. እርሱ የተከበረ ቁርኣን ነው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فِي كِتَٰبٖ مَّكۡنُونٖ
78. በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥም ነው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
لَّا يَمَسُّهُۥٓ إِلَّا ٱلۡمُطَهَّرُونَ
79. የተጥራሩት እንጂ ሌላ አይነካዉም::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
تَنزِيلٞ مِّن رَّبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
80. ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
أَفَبِهَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ أَنتُم مُّدۡهِنُونَ
81. በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَتَجۡعَلُونَ رِزۡقَكُمۡ أَنَّكُمۡ تُكَذِّبُونَ
82. ሲሳያችሁንም (ዝናብን) እናንተ የምታስተባበሉት ታደርጋላችሁን?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَلَوۡلَآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلۡحُلۡقُومَ
83. ነፍስ ጉሮሮንም በደረሰች ጊዜ::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَنتُمۡ حِينَئِذٖ تَنظُرُونَ
84. እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትሆኑ፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَنَحۡنُ أَقۡرَبُ إِلَيۡهِ مِنكُمۡ وَلَٰكِن لَّا تُبۡصِرُونَ
85. እኛም ግን እናንተ አታዩም እንጂ ከናንተ ይልቅ ወደ እርሱ የቀረብን ነን::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَلَوۡلَآ إِن كُنتُمۡ غَيۡرَ مَدِينِينَ
86. የማትዳኙም ከሆናችሁ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
تَرۡجِعُونَهَآ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
87. እውነተኞች እንደሆናችሁ ነፍሲቱን ወደ አካል ለምን አትመልሷትም?
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ
88. እናም ሟቹ ከባለሟሎቹ ከሆነም፤
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَرَوۡحٞ وَرَيۡحَانٞ وَجَنَّتُ نَعِيمٖ
89. ለእርሱ እረፍት መልካም ሲሳይና የመጠቀሚያ ገነት አለው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
90. ሟቹ ከቀኝ ጓዶችም ከሆነ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَلَٰمٞ لَّكَ مِنۡ أَصۡحَٰبِ ٱلۡيَمِينِ
91."ከቀኝ ጓዶች ስለሆንክ ላንተ ሰላም ነው የሚገባህ" ይባላል።
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَأَمَّآ إِن كَانَ مِنَ ٱلۡمُكَذِّبِينَ ٱلضَّآلِّينَ
92. ሟች ከእነዚያ ከሚያስተባብሉት ጠማማዎች ከሆነ ደግሞ
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَنُزُلٞ مِّنۡ حَمِيمٖ
93. ከፈላ ውሃ የሆነ መስተንግዶ አለለት::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
وَتَصۡلِيَةُ جَحِيمٍ
94. በገሀነም መቃጠልም አለለት::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ حَقُّ ٱلۡيَقِينِ
95. ይህ እርሱ እርግጠኛው እውነት ነው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
فَسَبِّحۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلۡعَظِيمِ
96. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የታላቁ ጌታህን ስም አጥራው::
আৰবী তাফছীৰসমূহ:
 
অৰ্থানুবাদ ছুৰা: ছুৰা আল-ৱাক্বিয়াহ
ছুৰাৰ তালিকা পৃষ্ঠা নং
 
আল-কোৰআনুল কাৰীমৰ অৰ্থানুবাদ - الترجمة الأمهرية - زين - অনুবাদসমূহৰ সূচীপত্ৰ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

বন্ধ