Qurani Kərimin mənaca tərcüməsi - الترجمة الأمهرية - زين * - Tərcumənin mündəricatı


Mənaların tərcüməsi Surə: əs-Saffat   Ayə:

ሱረቱ አስ ሷፋት

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا
1. መሰለፍን በሚሰለፉት፤
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
2. (ደመና) መንዳትን በሚነዱት፤
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ብቻ ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
5. እርሱ ያ በሰማያትና በምድር በመካካለቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው:: የምስራቆችም ጌታ ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት (አስዋብናት)::
Ərəbcə təfsirlər:
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
7. አመጸኛ ከሆነ ሰይጣንም ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት::
Ərəbcə təfsirlər:
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
8. ወደ ላይኛው ሰራዊት አያደምጡም፤ ከየአቅጣጫውም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፤ (ይቀጠቀጣሉ)።
Ərəbcə təfsirlər:
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፤ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አለባቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውኑም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር (እርሱ ይሰማዋል)::
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠረነው ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
12. ይልቁንም ማስተባበላቸው አስደነቀህ፤ በመደነቅህም ይሳለቃሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
13. በተገሰጹም ጊዜ አይገሰጹም::
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
14. ተዓምርንም ባዩ ጊዜ ለመሳለቅ ይጣጣራሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
15. አሉም: «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
Ərəbcə təfsirlər:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በሆን ጊዜ የምንቀስቀስ ነን?
Ərəbcə təfsirlər:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
17. «የቀድሞዎቹ አባቶቻችንም እንደዚሁ ይቀሰቀሳሉን?» (ይላሉ።)
Ərəbcə təfsirlər:
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
18. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አዎን! እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)።» በላቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት:: እነርሱም ወዲያውኑ ምን እንደሚፈጸምባቸው ያያሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው።» (ይላሉም)
Ərəbcə təfsirlər:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉት የነበራችት መለያው ቀን ነው።» ይባላሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
22. (ለመላዕክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ከአላህ ሌላ ይገዟቸው የነበሩትንም ጣዖታት በአንድ ሰብስቡ።
Ərəbcə təfsirlər:
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
23. ከአላህ ውጭ (ይገዟቸው የነበሩትን ሰብስቡ)። ከዚያም ወደ ገሀነም መንገድ ምሯቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
24. «እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና አቁሟቸዉም።» (ይባላል።)
Ərəbcə təfsirlər:
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
25. ለነርሱም «ምን ሆናችሁ ነው የማትረዳዱት?» ይባላሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
26. በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ማምለጫ የሌላቸው ወራዳዎች ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
27. እርስ በራሳቸውም የሚወቃቀሱም ሆነው ይመጣሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
28. (ተከታዮቹ ለአስከታዮቻቸው) «እናንተ በጉልበት ትመጡብን ነበር» ይላሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
29. (አስከታዮቹም) ይላሉ፡- «አይደለም ፈጽሞ አማኞች አልነበራችሁም።
Ərəbcə təfsirlər:
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
30. «ለእኛም በናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም። በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ህዝቦች ነበራችሁና ነው እንጂ።
Ərəbcə təfsirlər:
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
31. «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል የተረጋገጠብንና ሁላችንም ቅጣቱን ቀማሽ ነን።
Ərəbcə təfsirlər:
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
32. «እኛ ጠማሞች ስለ ነበርን ወደ ጥመት ጠራናችሁም።» ይላሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
33. ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
34. እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሰራለን።
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
35. እነርሱ «ከአላህ ሌላ ትክክለኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።
Ərəbcə təfsirlər:
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
36. «እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።
Ərəbcə təfsirlər:
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
37. አይደለም እውነቱን ሃይማኖት አመጣ፤ መልዕክተኞቹንም እውነተኝነታቸውን አረጋገጠ።
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
38. እናንተ አሳማሚውን ቅጣት እርግጥ ቀማሾች ናችሁ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
39. ትሰሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም::
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
40. ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ቅጣትን አይቀምሱም::
Ərəbcə təfsirlər:
أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
41. እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አለላቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
42. ፍራፋሬዎች (አሉላቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
43. በድሎት ገነቶች ውስጥ::
Ərəbcə təfsirlər:
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
44. ፊት ለፊት የሚተያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ ይንፈላሰሳሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
45. ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዙ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል::
Ərəbcə təfsirlər:
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ
46. ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከሆነች፤
Ərəbcə təfsirlər:
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
47. በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም:: እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም::
Ərəbcə təfsirlər:
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
48. እነርሱ ዘንድ ዓይናቸውን በባሎቻቸው ላይ ብቻ አሳጣሪዎች የሆኑ ዓይናማ ሴቶች አሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
49. እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) እንቁላል ይመስላሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
50. የሚጠያያቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
51. ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ (እንዲህ) ይላል: «እኔ ጓደኛ ነበረኝ።
Ərəbcə təfsirlər:
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ
52. (እንዲህ) የሚል: ‹በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን?
Ərəbcə təfsirlər:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
53. ‹በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆነ ጊዜ እኛ በእርግጥ እኛ እንመረመራለን?› የሚልም።
Ərəbcə təfsirlər:
قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
54. እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል::
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ
55. ይመለከታልም በገሀነም መካከልም ጓደኛውን ያየዋል::
Ərəbcə təfsirlər:
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ
56. ይላል «በአላህ እምላለሁ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር።
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ
57. «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር።» (ይላል)
Ərəbcə təfsirlər:
أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ
58. (የገነት ሰዎች ይላሉ)፡ «እኛ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን?»
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
59. «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር እኛም የምንቀጣ አይደለንም» ይላሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ
60.ይህ ለገነት ሰዎች የተወሳው እርሱ በእርግጥ ታላቅ እድል ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ
61. ለዚህ ብጤ ሰሪዎች ሁሉ ይስሩ::
Ərəbcə təfsirlər:
أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
62. በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ
63. እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል።
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ
64. እርሷ ከገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፤
Ərəbcə təfsirlər:
طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ
65. እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል::
Ərəbcə təfsirlər:
فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
66. እነርሱ ከእርሷ በይዎች ናቸው:: ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ
67. ከዚያ ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅልን መጠጥ አላቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ
68. ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ
69. እነርሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋል።
Ərəbcə təfsirlər:
فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ
70. እነርሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና።
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
71. ከእነርሱም በፊት የነበሩት የቀድሞዎቹ ህዝቦች አብዛሀኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል::
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
72. በውስጣቸዉም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል::
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ
73. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት!
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
74. ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ
75. ኑህም በእርግጥ ጠራን:: ምንኛ ያማርን ምላሽ ሰጪ ነን?
Ərəbcə təfsirlər:
وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
76. እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ
77. ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
78. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝና ተውን::
Ərəbcə təfsirlər:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ
79. «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑህ ላይ ይሁን።»
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
80. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
81. እርሱ ከአማኞች ባሮቻችን ነውና::
Ərəbcə təfsirlər:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
82. ከዚያም ሌሎችን አሰመጥን::
Ərəbcə təfsirlər:
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ
83. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) ኢብራሂምም በእርግጥ ከወገኖቹ አንዱ ነው።
Ərəbcə təfsirlər:
إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ
84. ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ የሆነውን (አስታውስ)::
Ərəbcə təfsirlər:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ
85. ለአባቱና ለህዝቦቹ ባለ ጊዜ: «ምንን ትገዛላችሁ?
Ərəbcə təfsirlər:
أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
86. «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Ərəbcə təfsirlər:
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
87. «በዓለማቱ ጌታስ ሀሳባችሁ ምንድ ነው?።»
Ərəbcə təfsirlər:
فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ
88. በከዋክብት መመልከትን ተመለከተ::
Ərəbcə təfsirlər:
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ
89. እኔ «በሽተኛ ነኝ» አለ።
Ərəbcə təfsirlər:
فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ
90. እነርሱም ከእርሱ የሸሹ ሆነው ሄዱ።
Ərəbcə təfsirlər:
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ
91. ከዚያ እሱ ወደ አማልዕክቶቻቸው ተዘነበለ፤ (እንዲህ) አለም፡- «አትበሉም እንዴ?
Ərəbcə təfsirlər:
مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ
92. «ምንም የማትናገሩበትስ ምን ምክኒያት አላችሁ?»
Ərəbcə təfsirlər:
فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ
93. በቀኝ (እጁ) የሚመታቸዉም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ::
Ərəbcə təfsirlər:
فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ
94. ወደ እርሱም ሰዎቹ እየሮጡ መጡ።
Ərəbcə təfsirlər:
قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ
95. አለ: «የምትጠርቡትን ትገዛላችሁን?
Ərəbcə təfsirlər:
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ
96. «አላህ እናንተንም ሆነ የምትሰሩትን ሁሉ የፈጠረ ሲሆን» አላቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ
97. «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም።» አሉ።
Ərəbcə təfsirlər:
فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ
98. ለእርሱ ተንኮልን አስቡ ወራዶችም አደረግናቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
99. አለም፡- «እኔ ወደ ጌታየ ሂያጅ ነኝ፤ በእርግጥ ይመራኛልና።
Ərəbcə təfsirlər:
رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
100. «ጌታየ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ።»
Ərəbcə təfsirlər:
فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ
101. ታጋሽም በሆነ ልጅም አበሰርነው።
Ərəbcə təfsirlər:
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ
102. ከእርሱ ጋርም (ለስራ) በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በህልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ትላለህ?» አለው። «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ስራ፤ አላህ ቢሻ ከታጋሾች ሆኜ ታገኘኛለህ።» አለ።
Ərəbcə təfsirlər:
فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ
103. ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)::
Ərəbcə təfsirlər:
وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ
104. ጠራነዉም: «ኢብራሂም ሆይ!
Ərəbcə təfsirlər:
قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
105. «ራዕዩን በርግጥ እውን አደረግክ።» እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን።
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ
106. ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ
107. በታላቅ እርድም መስዕዋት ቤዛ አደረግንለት።
Ərəbcə təfsirlər:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
108. በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት::
Ərəbcə təfsirlər:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ
109. ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን::
Ərəbcə təfsirlər:
كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
110. ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
111. እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
112. በኢስሐቅም አበሰርነው። ከመልካሞች የሆነ ነብይ ሲሆን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ
113. በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን። ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሰሪ አለ:: ነፍሱን በግልጽ በዳይም አለ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
114. በሙሳና በሀሩን ላይ በእርግጥ ለገስን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
115. እነርሱንም ሆነ ህዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
116. ረዳናቸውናም እነርሱ አሸናፊዎቹ ሆኑ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ
117. በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ
118. ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
119. በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካምን ዝናን ተውንላቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
120. ሰላም በሙሳና በሀሩን ላይ ይሁን::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
121. እኛ ልክ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
122. ሁለቱም በትክክል በአላህ ካመኑት ባሮቻችን ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
123. ኢልያስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።
Ərəbcə təfsirlər:
إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
124. ለህዝቦቹም ባለ ጊዜ (አስታውስ) «አላህን አትፈሩምን?
Ərəbcə təfsirlər:
أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ
125. «ስዕልን ትገዛላችሁ? ከስዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነዉም አምላክ ትተዋላችሁን?
Ərəbcə təfsirlər:
ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
126. «አላህ ጌታችሁና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁንም ጌታ ትተዋላችሁን?»
Ərəbcə təfsirlər:
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
127. አስተባበሉትም ስለዚህ እነርሱ ለቅጣት የሚጣዱ ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
128. ንጹህ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
129. በእነርሱ ላይም በኋለኞቹ ህዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት::
Ərəbcə təfsirlər:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ
130. ሰላም በኢልያስ ላይ ይሁን፤
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
131. እኛ ልክ እንደዚሁ መልካም ሰሪዎችን እንመነዳለን::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
132. እርሱ በእርግጥ ከምዕመናን ባሮቻችን ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
133. ሉጥም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው::
Ərəbcə təfsirlər:
إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
134. እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳናቸው ጊዜ (የሆነዉን አስታውስ)::
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
135. በቅጣቱ ውስጥ ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር::
Ərəbcə təfsirlər:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
136. ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ
137. (መኮች ሆይ)፤ እናንተም በእነርሱ መኖሪያዎች ላይ ያነጋችሁ ስትሆኑ ታልፋላችሁ።
Ərəbcə təfsirlər:
وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
138. በሌሊትም ታልፋላችሁ:: ልብ አታደርጉምን?
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
139. ዩኑስም በእርግጥ ከመልዕክተኞቹ ነው።
Ərəbcə təfsirlər:
إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
140. ወደ ተሞላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ አስታውስ::
Ərəbcə təfsirlər:
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ
141. እጣም ተጣጣለ፤ ከተሸነፉትም ሆነ::
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ
142. እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳ ነባሪው ዋጠው::
Ərəbcə təfsirlər:
فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ
143. እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነ ኖሮ
Ərəbcə təfsirlər:
لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ
144. እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር::
Ərəbcə təfsirlər:
۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ
145. እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው ባህር ዳርቻ ላይ ጣልነዉም::
Ərəbcə təfsirlər:
وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ
146. በእርሱም ላይ በአጠገቡ ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ
147. ወደ መቶ ሺህ ሰዎችም ላክነው፤ ከቶውንም ይጨምራሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ
148. አመኑም። እስከ ጊዜው ድረስም አጣቀምናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ
149. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የመካን ሰዎች ጠይቃቸዉም: «ለጌታህ ሴት ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራሉን?
Ərəbcə təfsirlər:
أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ
150. «ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላዕክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?»
Ərəbcə təfsirlər:
أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ
151. አስተውሉ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው የተነሳ ይላሉ:
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ
152.፡- «አላህ መላዕክትን ወለደ።» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ
153. በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጠን?
Ərəbcə təfsirlər:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
154. ለእናንተ ምን አስረጂ አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Ərəbcə təfsirlər:
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
155. አትገነዘቡምን?
Ərəbcə təfsirlər:
أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ
156. ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጂ አላችሁን?
Ərəbcə təfsirlər:
فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
157. «እውነተኞች እንደሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» በላቸው።
Ərəbcə təfsirlər:
وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
158. በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ:: አጋንንትም ሆኑ ይህን ባዩች በእሳት የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ አውቀዋል::
Ərəbcə təfsirlər:
سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
159. አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ::
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
160. ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች በአላህ ላይ አይዋሹም::
Ərəbcə təfsirlər:
فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ
161. (ካሐዲያን ሆይ!) እናንተም የምትገዟቸዉም ሁሉ፤
Ərəbcə təfsirlər:
مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ
162. በእርሱ በአላህ ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም
Ərəbcə təfsirlər:
إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ
163. ያንን እርሱ ገሀነም ገቢ የሆነውን ቢሆን እንጂ (አጥማሚዎች አይደላችሁም)።
Ərəbcə təfsirlər:
وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ
164. (መላእክቶችም አሉ)? «ከእኛ አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ።
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ
165. «እኛም ጌታን ለመገዛት ተሰላፊዎቹ እኛ ነን።
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ
166. «እኛም አላህን አጥሪዎቹ እኛው ነን።»
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ
167. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱ (ከሓዲያን) በእርግጥ ይሉ ነበር:
Ərəbcə təfsirlər:
لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
168. «ከቀድሞዎቹ መጽሐፍ ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረ ኖሮ
Ərəbcə təfsirlər:
لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
169. «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር።»
Ərəbcə təfsirlər:
فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ
170. ግን ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ በእርሱ ላይ ካዱ። ወደ ፊትም በእርግጥ ያውቃሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ
171. የእርዳታ ቃላችንም መልዕክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች::
Ərəbcə təfsirlər:
إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ
172. እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ብቻ ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
173. ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
174. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከእነርሱም ከመካ ከሓዲያን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር ተዋቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
175. ተመልከታቸዉም ወደፊትም የሚደርስባቸውን ያያሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
176. በቅጣታችንም ያቻኩሉናልን?
Ərəbcə təfsirlər:
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ
177. በቀያቸዉም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Ərəbcə təfsirlər:
وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
178. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እነርሱን እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ተዋቸው::
Ərəbcə təfsirlər:
وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
179. ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ::
Ərəbcə təfsirlər:
سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
180. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ::
Ərəbcə təfsirlər:
وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ
181. በመልዕክተኞቹም ላይ ሰላም ይሁን::
Ərəbcə təfsirlər:
وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
182. ምስጋና ሁሉም ለዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ ብቻ ይገባው::
Ərəbcə təfsirlər:
 
Mənaların tərcüməsi Surə: əs-Saffat
Surələrin mündəricatı Səhifənin rəqəmi
 
Qurani Kərimin mənaca tərcüməsi - الترجمة الأمهرية - زين - Tərcumənin mündəricatı

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

Bağlamaq