Check out the new design

Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Africa Academy * - Translations’ Index


Translation of the meanings Surah: As-Sāffāt   Ayah:

አስ ሷፋት

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا
1. መሰለፍን በሚሰለፉት፤
Arabic explanations of the Qur’an:
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
2. (ደመና) መንዳትን በሚነዱት፤
Arabic explanations of the Qur’an:
فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
3. ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ::
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
4. አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ብቻ ነው::
Arabic explanations of the Qur’an:
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
5. እርሱ ያ በሰማያትና በምድር በመካካለቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው:: የምስራቆችም ጌታ ነው::
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
6. እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት (አስዋብናት)::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
7. አመጸኛ ከሆነ ሰይጣንም ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት::
Arabic explanations of the Qur’an:
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
8. ወደ ላይኛው ሰራዊት አያደምጡም፤ ከየአቅጣጫውም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፤ (ይቀጠቀጣሉ)።
Arabic explanations of the Qur’an:
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
9. የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፤ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አለባቸው::
Arabic explanations of the Qur’an:
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
10. ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውኑም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር (እርሱ ይሰማዋል)::
Arabic explanations of the Qur’an:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ ከእነርሱ በፊት የፈጠረነው ፍጡር? እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው::
Arabic explanations of the Qur’an:
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
12. ይልቁንም ማስተባበላቸው አስደነቀህ፤ በመደነቅህም ይሳለቃሉ::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
13. በተገሰጹም ጊዜ አይገሰጹም::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
14. ተዓምርንም ባዩ ጊዜ ለመሳለቅ ይጣጣራሉ።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
15. አሉም: «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
Arabic explanations of the Qur’an:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
16. «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በሆን ጊዜ የምንቀስቀስ ነን?
Arabic explanations of the Qur’an:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
17. «የቀድሞዎቹ አባቶቻችንም እንደዚሁ ይቀሰቀሳሉን?» (ይላሉ።)
Arabic explanations of the Qur’an:
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
18. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «አዎን! እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)።» በላቸው።
Arabic explanations of the Qur’an:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
19. እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት:: እነርሱም ወዲያውኑ ምን እንደሚፈጸምባቸው ያያሉ::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
20. «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው።» (ይላሉም)
Arabic explanations of the Qur’an:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
21. «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉት የነበራችት መለያው ቀን ነው።» ይባላሉ።
Arabic explanations of the Qur’an:
۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
22. (ለመላዕክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ከአላህ ሌላ ይገዟቸው የነበሩትንም ጣዖታት በአንድ ሰብስቡ።
Arabic explanations of the Qur’an:
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
23. ከአላህ ውጭ (ይገዟቸው የነበሩትን ሰብስቡ)። ከዚያም ወደ ገሀነም መንገድ ምሯቸው።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
24. «እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና አቁሟቸዉም።» (ይባላል።)
Arabic explanations of the Qur’an:
 
Translation of the meanings Surah: As-Sāffāt
Surahs’ Index Page Number
 
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Africa Academy - Translations’ Index

Translated by Muhammad Zain Zahruddin. Published by Africa Academy

close