Übersetzung der Bedeutungen von dem heiligen Quran - Amherische Übersetzung * - Übersetzungen

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Übersetzung der Bedeutungen Surah / Kapitel: As-Sâffât   Vers:

ሱረቱ አስ ሷፋት

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ።
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ
ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
አትገነዘቡምን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
Arabische Interpretationen von dem heiligen Quran:
 
Übersetzung der Bedeutungen Surah / Kapitel: As-Sâffât
Suren/ Kapiteln Liste Nummer der Seite
 
Übersetzung der Bedeutungen von dem heiligen Quran - Amherische Übersetzung - Übersetzungen

Übersetzung der Quran-Bedeutung in Amhari Sprache von Muhammed Sadeq und Muhammed Ath.thany Habib in 2011 Hinweis: Einige übersetzte Verse, korrigiert von Ruwwad Translation Center. Die Originalübersetzung steht für Anregungen, kontinuierliche Auswertung und Entwicklung zur Verfügung

Schließen