د قرآن کریم د معناګانو ژباړه - امهري ژباړه * - د ژباړو فهرست (لړلیک)

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

د معناګانو ژباړه سورت: الصافات   آیت:

ሱረቱ አስ ሷፋት

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
عربي تفسیرونه:
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
عربي تفسیرونه:
فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
عربي تفسیرونه:
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
عربي تفسیرونه:
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
عربي تفسیرونه:
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
عربي تفسیرونه:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
عربي تفسیرونه:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
عربي تفسیرونه:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
عربي تفسیرونه:
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
عربي تفسیرونه:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
عربي تفسیرونه:
۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
عربي تفسیرونه:
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
عربي تفسیرونه:
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
عربي تفسیرونه:
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
عربي تفسیرونه:
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
عربي تفسیرونه:
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
عربي تفسیرونه:
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
عربي تفسیرونه:
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
عربي تفسیرونه:
أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
عربي تفسیرونه:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
عربي تفسیرونه:
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
عربي تفسیرونه:
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
عربي تفسیرونه:
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
عربي تفسیرونه:
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
عربي تفسیرونه:
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
عربي تفسیرونه:
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
عربي تفسیرونه:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
عربي تفسیرونه:
قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
عربي تفسیرونه:
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
عربي تفسیرونه:
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
عربي تفسیرونه:
وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
عربي تفسیرونه:
أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
عربي تفسیرونه:
إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
عربي تفسیرونه:
أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
عربي تفسیرونه:
إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
عربي تفسیرونه:
طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
عربي تفسیرونه:
فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
عربي تفسیرونه:
فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
عربي تفسیرونه:
وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
عربي تفسیرونه:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
عربي تفسیرونه:
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
عربي تفسیرونه:
وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
عربي تفسیرونه:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
عربي تفسیرونه:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
عربي تفسیرونه:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
عربي تفسیرونه:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
عربي تفسیرونه:
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
عربي تفسیرونه:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
عربي تفسیرونه:
أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
عربي تفسیرونه:
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
عربي تفسیرونه:
مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
عربي تفسیرونه:
فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
عربي تفسیرونه:
قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
عربي تفسیرونه:
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
عربي تفسیرونه:
قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
عربي تفسیرونه:
رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
عربي تفسیرونه:
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
عربي تفسیرونه:
وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
عربي تفسیرونه:
قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
عربي تفسیرونه:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
عربي تفسیرونه:
كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
عربي تفسیرونه:
أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
عربي تفسیرونه:
ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
عربي تفسیرونه:
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
عربي تفسیرونه:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
عربي تفسیرونه:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
عربي تفسیرونه:
إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
عربي تفسیرونه:
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
عربي تفسیرونه:
فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
عربي تفسیرونه:
فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
عربي تفسیرونه:
لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
عربي تفسیرونه:
۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
عربي تفسیرونه:
وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ።
عربي تفسیرونه:
فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ
ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
عربي تفسیرونه:
أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
عربي تفسیرونه:
أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
عربي تفسیرونه:
وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
عربي تفسیرونه:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
عربي تفسیرونه:
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
አትገነዘቡምን?
عربي تفسیرونه:
أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
عربي تفسیرونه:
فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
عربي تفسیرونه:
وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
عربي تفسیرونه:
سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
عربي تفسیرونه:
فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
عربي تفسیرونه:
مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
عربي تفسیرونه:
إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
عربي تفسیرونه:
لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
عربي تفسیرونه:
لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
عربي تفسیرونه:
فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
عربي تفسیرونه:
إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
عربي تفسیرونه:
وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
عربي تفسیرونه:
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
عربي تفسیرونه:
وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
عربي تفسیرونه:
وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
عربي تفسیرونه:
سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
عربي تفسیرونه:
وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
عربي تفسیرونه:
وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
عربي تفسیرونه:
 
د معناګانو ژباړه سورت: الصافات
د سورتونو فهرست (لړلیک) د مخ نمبر
 
د قرآن کریم د معناګانو ژباړه - امهري ژباړه - د ژباړو فهرست (لړلیک)

په اماریک ژبه کې د قرآن کریم د معنی ژباړه، د شیخ محمد صادق او محمد الثاني لخوا شوې ده دا ژباړه د مرکز رواد الترجمة تر څارنې لاندې اصلاح شوې او اصلي ژباړه د نظر څرګندولو، ارزونې او دوامداره پرمختګ لپاره شتون لري.

بندول