Kur'an-ı Kerim meal tercümesi - Emheri Dilinde Kur'an-ı Kerim Meali * - Mealler fihristi

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Anlam tercümesi Sure: Sûratu's-Saffât   Ayet:

ሱረቱ አስ ሷፋት

وَٱلصَّٰٓفَّٰتِ صَفّٗا
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
Arapça tefsirler:
فَٱلزَّٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
Arapça tefsirler:
فَٱلتَّٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
Arapça tefsirler:
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
Arapça tefsirler:
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
Arapça tefsirler:
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
Arapça tefsirler:
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
Arapça tefsirler:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
Arapça tefsirler:
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
Arapça tefsirler:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
Arapça tefsirler:
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
Arapça tefsirler:
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
Arapça tefsirler:
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
Arapça tefsirler:
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
Arapça tefsirler:
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
Arapça tefsirler:
۞ ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
Arapça tefsirler:
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
Arapça tefsirler:
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
Arapça tefsirler:
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
Arapça tefsirler:
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
Arapça tefsirler:
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
Arapça tefsirler:
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
Arapça tefsirler:
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
Arapça tefsirler:
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
Arapça tefsirler:
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
Arapça tefsirler:
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
Arapça tefsirler:
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
Arapça tefsirler:
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
Arapça tefsirler:
أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
Arapça tefsirler:
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
Arapça tefsirler:
فِي جَنَّٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
Arapça tefsirler:
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
Arapça tefsirler:
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
Arapça tefsirler:
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّٰرِبِينَ
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
Arapça tefsirler:
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
Arapça tefsirler:
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
Arapça tefsirler:
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
Arapça tefsirler:
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
Arapça tefsirler:
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
Arapça tefsirler:
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
Arapça tefsirler:
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
Arapça tefsirler:
قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
Arapça tefsirler:
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
Arapça tefsirler:
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
Arapça tefsirler:
وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
Arapça tefsirler:
أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
Arapça tefsirler:
إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
Arapça tefsirler:
لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
Arapça tefsirler:
أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
Arapça tefsirler:
إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّٰلِمِينَ
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
Arapça tefsirler:
طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
Arapça tefsirler:
فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
Arapça tefsirler:
ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
Arapça tefsirler:
فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
Arapça tefsirler:
وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
Arapça tefsirler:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
Arapça tefsirler:
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Arapça tefsirler:
وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
Arapça tefsirler:
وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
Arapça tefsirler:
وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
Arapça tefsirler:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
Arapça tefsirler:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
Arapça tefsirler:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
Arapça tefsirler:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
Arapça tefsirler:
۞ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
Arapça tefsirler:
إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
Arapça tefsirler:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
Arapça tefsirler:
أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
Arapça tefsirler:
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
Arapça tefsirler:
فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
Arapça tefsirler:
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
Arapça tefsirler:
فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
Arapça tefsirler:
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
Arapça tefsirler:
مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
Arapça tefsirler:
فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
Arapça tefsirler:
فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
Arapça tefsirler:
قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
Arapça tefsirler:
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
Arapça tefsirler:
قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
Arapça tefsirler:
فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
Arapça tefsirler:
رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
Arapça tefsirler:
فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
Arapça tefsirler:
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّٰبِرِينَ
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
Arapça tefsirler:
فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
Arapça tefsirler:
وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَٰٓإِبۡرَٰهِيمُ
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
Arapça tefsirler:
قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
Arapça tefsirler:
وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
Arapça tefsirler:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
Arapça tefsirler:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
Arapça tefsirler:
كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
Arapça tefsirler:
وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
Arapça tefsirler:
وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
Arapça tefsirler:
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
Arapça tefsirler:
وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
Arapça tefsirler:
وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
Arapça tefsirler:
وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
Arapça tefsirler:
سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Arapça tefsirler:
إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
Arapça tefsirler:
أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
Arapça tefsirler:
ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
Arapça tefsirler:
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
Arapça tefsirler:
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
Arapça tefsirler:
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Arapça tefsirler:
إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
Arapça tefsirler:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
Arapça tefsirler:
وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
Arapça tefsirler:
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
Arapça tefsirler:
إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
Arapça tefsirler:
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
Arapça tefsirler:
فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
Arapça tefsirler:
فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
Arapça tefsirler:
لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
Arapça tefsirler:
۞ فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
Arapça tefsirler:
وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
Arapça tefsirler:
وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ።
Arapça tefsirler:
فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَلِرَبِّكَ ٱلۡبَنَاتُ وَلَهُمُ ٱلۡبَنُونَ
ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?»
Arapça tefsirler:
أَمۡ خَلَقۡنَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ إِنَٰثٗا وَهُمۡ شَٰهِدُونَ
ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?
Arapça tefsirler:
أَلَآ إِنَّهُم مِّنۡ إِفۡكِهِمۡ لَيَقُولُونَ
ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-
Arapça tefsirler:
وَلَدَ ٱللَّهُ وَإِنَّهُمۡ لَكَٰذِبُونَ
«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
أَصۡطَفَى ٱلۡبَنَاتِ عَلَى ٱلۡبَنِينَ
በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?
Arapça tefsirler:
مَا لَكُمۡ كَيۡفَ تَحۡكُمُونَ
ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!
Arapça tefsirler:
أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
አትገነዘቡምን?
Arapça tefsirler:
أَمۡ لَكُمۡ سُلۡطَٰنٞ مُّبِينٞ
ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?
Arapça tefsirler:
فَأۡتُواْ بِكِتَٰبِكُمۡ إِن كُنتُمۡ صَٰدِقِينَ
«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡
Arapça tefsirler:
وَجَعَلُواْ بَيۡنَهُۥ وَبَيۡنَ ٱلۡجِنَّةِ نَسَبٗاۚ وَلَقَدۡ عَلِمَتِ ٱلۡجِنَّةُ إِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡
Arapça tefsirler:
سُبۡحَٰنَ ٱللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡
Arapça tefsirler:
فَإِنَّكُمۡ وَمَا تَعۡبُدُونَ
እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤
Arapça tefsirler:
مَآ أَنتُمۡ عَلَيۡهِ بِفَٰتِنِينَ
በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡
Arapça tefsirler:
إِلَّا مَنۡ هُوَ صَالِ ٱلۡجَحِيمِ
ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡
Arapça tefsirler:
وَمَا مِنَّآ إِلَّا لَهُۥ مَقَامٞ مَّعۡلُومٞ
(ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلصَّآفُّونَ
እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡمُسَبِّحُونَ
እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِن كَانُواْ لَيَقُولُونَ
እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡-
Arapça tefsirler:
لَوۡ أَنَّ عِندَنَا ذِكۡرٗا مِّنَ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤
Arapça tefsirler:
لَكُنَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
«የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡»
Arapça tefsirler:
فَكَفَرُواْ بِهِۦۖ فَسَوۡفَ يَعۡلَمُونَ
ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
Arapça tefsirler:
وَلَقَدۡ سَبَقَتۡ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا ٱلۡمُرۡسَلِينَ
(የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡
Arapça tefsirler:
إِنَّهُمۡ لَهُمُ ٱلۡمَنصُورُونَ
እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡
Arapça tefsirler:
فَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡
Arapça tefsirler:
وَأَبۡصِرۡهُمۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡
Arapça tefsirler:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
በቅጣታችንም ያቻኩላሉን?
Arapça tefsirler:
فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمۡ فَسَآءَ صَبَاحُ ٱلۡمُنذَرِينَ
በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ!
Arapça tefsirler:
وَتَوَلَّ عَنۡهُمۡ حَتَّىٰ حِينٖ
እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡
Arapça tefsirler:
وَأَبۡصِرۡ فَسَوۡفَ يُبۡصِرُونَ
ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡
Arapça tefsirler:
سُبۡحَٰنَ رَبِّكَ رَبِّ ٱلۡعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡
Arapça tefsirler:
وَسَلَٰمٌ عَلَى ٱلۡمُرۡسَلِينَ
በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤
Arapça tefsirler:
وَٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡
Arapça tefsirler:
 
Anlam tercümesi Sure: Sûratu's-Saffât
Surelerin fihristi Sayfa numarası
 
Kur'an-ı Kerim meal tercümesi - Emheri Dilinde Kur'an-ı Kerim Meali - Mealler fihristi

Emheri Dilinde Kur'an-ı Kerim Meali- Tercüme Şeyh Muhammed Sadık ve Muhammed Es-Sani Habib. Basım Yılı 2011. Belirtilen bazı ayetlerin tercümesi Ravad Tercüme Merkezi tarafından düzeltilmiştir. Değerlendirme, görüş belirtme ve gelişimin devamlı olabilmesi için orijinal tercümeye erişim sağlanmaktadır.

Kapat