Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic Translation - Zain * - Translations’ Index


Translation of the meanings Surah: Al-Muddaththir   Ayah:

ሱረቱ አል ሙደሲር

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
1. አንተ (ልብስ) ደራቢው ሆይ!
Arabic explanations of the Qur’an:
قُمۡ فَأَنذِرۡ
2. ተነሳና (ህዝቦችህን) አስጠንቅቅ።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
3. ጌታህንም አክብር::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
4. ልብስህንም አጥራ::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
5. ጣዖትንም ራቅ::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
6. ማብዛትንም የምትፈልግ ሆነህ አትለግስ::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
7. (ብዙ ዒባዳን ከመስራት አትድከም):: ለጌታህም (ትዕዘዛዝ) ታገስ።
Arabic explanations of the Qur’an:
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
8. በቀንዱም በተነፋ ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
9. ይህን ጊዜ ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው።
Arabic explanations of the Qur’an:
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
10. (በተለይ) በከሓዲያን ላይ ገር ያልሆነ ቀን ነው።
Arabic explanations of the Qur’an:
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በብቸኝነት ከፈጠርኩት ጋር ተወኝ።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
12. ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በዓይነቱ) አደረግኩለት።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَبَنِينَ شُهُودٗا
13. በየአደባባዩ ተገኝ የሆኑ ወንዶች ልጆችንም ሰጠሁት።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
14. ለእርሱም ኑሮውን መዘርጋትን ዘረጋሁለት፤
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
15. ከዚያ ልጨምርለት ይከጅላል::
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
16. ሰው ይከልከል! እርሱ ለአናቅጻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበርና።
Arabic explanations of the Qur’an:
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
17. በእርግጥ (ገሀነም ውስጥ) ችግርን አስገድደዋለሁ።
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
18. እርሱ (በቁርኣን ጉዳይ) አሰበ፤ ገመተም።
Arabic explanations of the Qur’an:
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
19. እናም ተረገመ:: እንዴት ገመተ!
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
20. ከዚያ ተረገመ። እንዴትስ ገመተ!
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ نَظَرَ
21. ከዚያም እንደገና (በቁርኣን ጉዳይ) ተመለከተ።
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
22. ከዚያ ፊቱን አጨፈገገ አኮማተረም::
Arabic explanations of the Qur’an:
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
23. ከዚያ (በአላህ ከማመን) ዞረ:: ኮራም::
Arabic explanations of the Qur’an:
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
24. «ይህ ከሌላ (ሰው) የሚቀዳ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
25. «ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም» አለ::
Arabic explanations of the Qur’an:
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
26. ሰቀር (በተባለ የገሀነም ዋሻ ውስጥ) በእርግጥ አስገባዋለሁ::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰቀር ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
Arabic explanations of the Qur’an:
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
28. (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም:: አትተዉምም::
Arabic explanations of the Qur’an:
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
29. የሰዎችን ቆዳ በጣም አክሳይ ናት።
Arabic explanations of the Qur’an:
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
30. በእርሷም ላይ አስራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
31. የእሳትን ዘበኞች መላዕክት እንጂ ሌላ አላደረግንም:: ቁጥራቸውንም ለእነዚያ በአላህ ለካዱት ሰዎች መፈተኛ እንጂ ለሌላ አላደረግንም:: እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች እንዲያረጋግጡ፤ እነዚያም በትክክል ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፤ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምዕመናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፤ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አስመሳዮችና ከሓዲያን «አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል?» እንዲሉ እንጂ (አላደረግንም):: ልክ እንደዚሁ አላህ የሚፈልገውን ያጠማል:: የሚፈልገውንም ያቀናል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህንም ሰራዊት ልክ ከእርሱ በስተቀር ማንም አያውቅም:: የሰቀር እሳት ለሰዎች መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
32. (ከክህደት) ይከልከሉ:: በጨረቃ (እምላለሁ)፤
Arabic explanations of the Qur’an:
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
33. በሌሊቱም በሄደ ጊዜ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
34. በንጋቱም ባበራ ጊዜ እምላለሁ።
Arabic explanations of the Qur’an:
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
35. (ሰቀር) ከታላላቆች አደጋዎች አንዱ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
36. ለሰዎች አስፈራሪ ናት።
Arabic explanations of the Qur’an:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
37. ከናንተ መካከል ወደ በጎ ነገር መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለፈለገ (ሰው) ሁሉ፤
Arabic explanations of the Qur’an:
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
38. ነፍስ ሁሉ በሰራችው ስራ ተያዥ ናት::
Arabic explanations of the Qur’an:
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
39. እነዚያ መዝገባቸውን በቀኝ እጃቸው የሚሰጡት ብቻ ሲቀሩ::
Arabic explanations of the Qur’an:
فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
40. (እነርሱማ) በገነቶች ውስጥ ሁነው እርስ በራሳቸው ይጠያየቃሉ::
Arabic explanations of the Qur’an:
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
41. ከአመጸኞች ሁኔታ (ይጠያየቃሉ)
Arabic explanations of the Qur’an:
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
42. (ከዚያ ለእነርሱ እንዲህ ይሏቸዋል።) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
Arabic explanations of the Qur’an:
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
43. «ከሰጋጆች አልነበርንም።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
44. «ለድሆችም የምናበላም አልነበርንም።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
45. «ከዘባራቂዎችም ጋር እንዘባርቅ ነበር።
Arabic explanations of the Qur’an:
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
46. «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበር፤
Arabic explanations of the Qur’an:
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
47. «እርግጠኛው ነገር ሞት እስከመጣብን ድረስ።» ይላሉ
Arabic explanations of the Qur’an:
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ
48. እናም በዚያ ቀን የአማላጆች (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።
Arabic explanations of the Qur’an:
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
49. ከ(ቁርኣን) ከግሳጼም የሚያፈገፍጉበት ምን ምክኒያት አላቸው?
Arabic explanations of the Qur’an:
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
50. እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዩች ይመስላሉ::
Arabic explanations of the Qur’an:
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
51. ከአንበሳ የሸሹ
Arabic explanations of the Qur’an:
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
52. ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለእያንዳንዱ ሰው የተዘረጉ ጹሑፎችን በእጁ እንዲሰጥ ይፈልጋል::
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
53. ከዚህ መሰል ተግባራቸው ይከልከሉ:: ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም ቅጣት አይፈሩም::
Arabic explanations of the Qur’an:
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
54. ይከልከሉ፤እርሱ(ቁርአን) መገሰጫ ነው።
Arabic explanations of the Qur’an:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
55. ስለዚህ የፈለገ ሰው ቁርኣንን ይገሰጽበታል::
Arabic explanations of the Qur’an:
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
56. ሆኖም (ሰዎች) አላህ ካልፈለገ በስተቀር አይገሰጹም:: አላህ የመፈራት ባለቤት ነው:: (ለፈሩትም) የምህረት ባለቤት ነው::
Arabic explanations of the Qur’an:
 
Translation of the meanings Surah: Al-Muddaththir
Surahs’ Index Page Number
 
Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic Translation - Zain - Translations’ Index

Amharic Translation

close