Check out the new design

ترجمهٔ معانی قرآن کریم - ترجمه‌ى امهری ـ آکادمی آفریقا * - لیست ترجمه ها

PDF XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

ترجمهٔ معانی سوره: طه   آیه:

ጣሃ

طه
1. ጧሃ፤
تفسیرهای عربی:
مَآ أَنزَلۡنَا عَلَيۡكَ ٱلۡقُرۡءَانَ لِتَشۡقَىٰٓ
2.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቁርኣንን አንድትቸገር ባንተ ላይ አላወረድንም::
تفسیرهای عربی:
إِلَّا تَذۡكِرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰ
3. አላህን ለሚፈራ ሁሉ መገሠጫ ይሆን ዘንድ እንጂ
تفسیرهای عربی:
تَنزِيلٗا مِّمَّنۡ خَلَقَ ٱلۡأَرۡضَ وَٱلسَّمَٰوَٰتِ ٱلۡعُلَى
4. ቁርኣን ምድርንና የላይኛዎቹን (የተከበሩ) ሰማያትን ከፈጠረ አምላክ ተወረደ::
تفسیرهای عربی:
ٱلرَّحۡمَٰنُ عَلَى ٱلۡعَرۡشِ ٱسۡتَوَىٰ
5.እርሱ አዛኙ ጌታ (አር-ረህማን) በዐርሹ ላይ ከፍ አለ::
تفسیرهای عربی:
لَهُۥ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَمَا تَحۡتَ ٱلثَّرَىٰ
6. በሰማያት፤በምድርና በመካከላቸዉም ያለው ከአፈር በታችም ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው::
تفسیرهای عربی:
وَإِن تَجۡهَرۡ بِٱلۡقَوۡلِ فَإِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلسِّرَّ وَأَخۡفَى
7. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በንግግር ብትጮህ (አላህ ከጩኸቱ የተብቃቃ ነው።) እርሱ ምስጢርን ከዚያም በጣም የተደበቀንም ያውቃልና::
تفسیرهای عربی:
ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَۖ لَهُ ٱلۡأَسۡمَآءُ ٱلۡحُسۡنَىٰ
8.አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም:: ለእርሱ መልካሞች የሆኑ አያሌ ስሞች አሉት::
تفسیرهای عربی:
وَهَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
9.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሙሳ ወሬ (ታሪክ) መጥቶሃልን (ደርሶሃልን)?
تفسیرهای عربی:
إِذۡ رَءَا نَارٗا فَقَالَ لِأَهۡلِهِ ٱمۡكُثُوٓاْ إِنِّيٓ ءَانَسۡتُ نَارٗا لَّعَلِّيٓ ءَاتِيكُم مِّنۡهَا بِقَبَسٍ أَوۡ أَجِدُ عَلَى ٱلنَّارِ هُدٗى
10. እሳትን ባየና ለቤተሰቦቹ «(እዚህ) ቆዩ:: እኔ እሳትን አየሁ፤ ከእርሷ ችቦን ላመጣላችሁ ወይም እሳቲቱ ዘንድ መሪን ላገኝ እከጅላለሁ።» ባለ ጊዜ የሆነውን አስታውስ::
تفسیرهای عربی:
فَلَمَّآ أَتَىٰهَا نُودِيَ يَٰمُوسَىٰٓ
11. እናም ወደ እርሷ በመጣ ጊዜ (እንዲህ) በማለት ተጠራ: «ሙሳ ሆይ!
تفسیرهای عربی:
إِنِّيٓ أَنَا۠ رَبُّكَ فَٱخۡلَعۡ نَعۡلَيۡكَ إِنَّكَ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوٗى
12. «እኔ ጌታህ ነኝ። ጫማዎችህን አውልቅ፤ አንተ በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ ነህና።
تفسیرهای عربی:
وَأَنَا ٱخۡتَرۡتُكَ فَٱسۡتَمِعۡ لِمَا يُوحَىٰٓ
13. «እኔም መረጥኩህ ስለ ሆነም የሚወረድልህን ነገር በደንብ አዳምጥ።
تفسیرهای عربی:
إِنَّنِيٓ أَنَا ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعۡبُدۡنِي وَأَقِمِ ٱلصَّلَوٰةَ لِذِكۡرِيٓ
14. «እኔ አላህ ነኝ። ያለ እኔ ትክክለኛ አምላክ የለምና እኔን ብቻ ተገዛኝ:: ሶላትንም እኔን ለማውሳት በአግባቡ ስገድ።
تفسیرهای عربی:
إِنَّ ٱلسَّاعَةَ ءَاتِيَةٌ أَكَادُ أُخۡفِيهَا لِتُجۡزَىٰ كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا تَسۡعَىٰ
15. «ነፍስ ሁሉ በምትሰራው ነገር ትመነዳ ዘንድ ሰዓቲቱ በእርግጥ መጪ ናት። የትንሳኤውን ወሬ ልደብቃት እቀርባለሁ።
تفسیرهای عربی:
فَلَا يَصُدَّنَّكَ عَنۡهَا مَن لَّا يُؤۡمِنُ بِهَا وَٱتَّبَعَ هَوَىٰهُ فَتَرۡدَىٰ
16. (ሙሳ ሆይ!) «በእርሷ የማያምንና ዝንባሌውን የሚከተል ሰው ሁሉ ከእርሷ አያግድህ ትጠፋለህና።
تفسیرهای عربی:
وَمَا تِلۡكَ بِيَمِينِكَ يَٰمُوسَىٰ
17. (ሙሳ ሆይ!) «ይህችም በቀኝ እጅህ ያለችው ምንድን ናት?» (ተባለ)።
تفسیرهای عربی:
قَالَ هِيَ عَصَايَ أَتَوَكَّؤُاْ عَلَيۡهَا وَأَهُشُّ بِهَا عَلَىٰ غَنَمِي وَلِيَ فِيهَا مَـَٔارِبُ أُخۡرَىٰ
18. «እርሷ በትሬ ናት:: በእርሷም እደገፍባታለሁ:: በእርሷም ለፍየሎቼ ቅጠልን አረግፍባታለሁ:: በእርሷ ሌሎች ጉዳዮችም አሉኝ።» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ أَلۡقِهَا يَٰمُوسَىٰ
19. አላህም «ሙሳ ሆይ! እስቲ ጣላት።» አለው።
تفسیرهای عربی:
فَأَلۡقَىٰهَا فَإِذَا هِيَ حَيَّةٞ تَسۡعَىٰ
20.ሙሳም ጣላትና፤ ወዲያዉም እርሷ የምትሮጥ እባብ ሆነች::
تفسیرهای عربی:
قَالَ خُذۡهَا وَلَا تَخَفۡۖ سَنُعِيدُهَا سِيرَتَهَا ٱلۡأُولَىٰ
21.አላህም አለው: «ሙሳ ሆይ! ያዛት አትፍራም ወደ መጀመሪያ ጠባይዋ እንመልሳታለን።
تفسیرهای عربی:
وَٱضۡمُمۡ يَدَكَ إِلَىٰ جَنَاحِكَ تَخۡرُجۡ بَيۡضَآءَ مِنۡ غَيۡرِ سُوٓءٍ ءَايَةً أُخۡرَىٰ
22. «እጅህንም ወደ ብብትህ አስገባ:: ሌላ ተዓምር ስትሆን ያለ ምንም ችግር ነጭ ሆና ትወጣለችና::
تفسیرهای عربی:
لِنُرِيَكَ مِنۡ ءَايَٰتِنَا ٱلۡكُبۡرَى
23. (ሙሳ ሆይ!) «ከተዓምራቶቻችን ታላቋን እናሳይህ ዘንድ ይህን ፈጸምን::
تفسیرهای عربی:
ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
24. (ሙሳ ሆይ!) «ወደ ፈርዖን ሂድ:: እርሱ ወሰን (ድንበር) አልፏልና።»
تفسیرهای عربی:
قَالَ رَبِّ ٱشۡرَحۡ لِي صَدۡرِي
25. ሙሳም አለ: «ጌታዬ ሆይ! ልቤን አስፋልኝ።
تفسیرهای عربی:
وَيَسِّرۡ لِيٓ أَمۡرِي
26. «ጉዳዬንም አግራልኝ።
تفسیرهای عربی:
وَٱحۡلُلۡ عُقۡدَةٗ مِّن لِّسَانِي
27. «የምላሴን መኮላተፍም አስወግድልኝ።
تفسیرهای عربی:
يَفۡقَهُواْ قَوۡلِي
28. «ንግግሬን ይረዱ ዘንድ።
تفسیرهای عربی:
وَٱجۡعَل لِّي وَزِيرٗا مِّنۡ أَهۡلِي
29. «ከቤተሰቦቼም ለእኔ ረዳትን አድርግልኝ።
تفسیرهای عربی:
هَٰرُونَ أَخِي
30. «ወንድሜን ሃሩንን
تفسیرهای عربی:
ٱشۡدُدۡ بِهِۦٓ أَزۡرِي
31. «ኃይሌንም በእርሱ አበርታልኝ::
تفسیرهای عربی:
وَأَشۡرِكۡهُ فِيٓ أَمۡرِي
32. «በነገሬም አጋራው።
تفسیرهای عربی:
كَيۡ نُسَبِّحَكَ كَثِيرٗا
33. «በብዛት እንድናጠራህና
تفسیرهای عربی:
وَنَذۡكُرَكَ كَثِيرًا
34. «በብዛት እንድናወሳህ
تفسیرهای عربی:
إِنَّكَ كُنتَ بِنَا بَصِيرٗا
35. «አንተ በእኛ ነገር አዋቂ ነህና።»
تفسیرهای عربی:
قَالَ قَدۡ أُوتِيتَ سُؤۡلَكَ يَٰمُوسَىٰ
36. አላህም አለ: «ሙሳ ሆይ! ልመናህ በእርግጥ ተቀባይነትን አገኝቷል።
تفسیرهای عربی:
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَيۡكَ مَرَّةً أُخۡرَىٰٓ
37. «ሙሳ ሆይ! በሌላም ጊዜ ባንተ ላይ በእርግጥ ውለታን ውለናል::
تفسیرهای عربی:
إِذۡ أَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰٓ أُمِّكَ مَا يُوحَىٰٓ
38. «ለእናትህ በራእይ ባሳወቅን ጊዜ ነው።
تفسیرهای عربی:
أَنِ ٱقۡذِفِيهِ فِي ٱلتَّابُوتِ فَٱقۡذِفِيهِ فِي ٱلۡيَمِّ فَلۡيُلۡقِهِ ٱلۡيَمُّ بِٱلسَّاحِلِ يَأۡخُذۡهُ عَدُوّٞ لِّي وَعَدُوّٞ لَّهُۥۚ وَأَلۡقَيۡتُ عَلَيۡكَ مَحَبَّةٗ مِّنِّي وَلِتُصۡنَعَ عَلَىٰ عَيۡنِيٓ
39. «‹ሕፃኑን በሳጥኑ ውስጥ አስገቢው እርሱንም (ሳጥኑን) በባህር ላይ ጣይው፤ ባህሩም በዳርቻው ይጥለዋል (ይተፋዋል):: ለእኔም ለእርሱም ጠላት የሆነ ሰው ይይዘዋልና› በማለት (ባሳወቅን ጊዜ ለገስንልህ)። ልትወደድና በዐይኔ እይታ (በእኔም ጥበቃ) ታድግ ዘንድ ባንተ ላይም ከእኔ የሆነ መወደድን ጣልኩብህ::
تفسیرهای عربی:
إِذۡ تَمۡشِيٓ أُخۡتُكَ فَتَقُولُ هَلۡ أَدُلُّكُمۡ عَلَىٰ مَن يَكۡفُلُهُۥۖ فَرَجَعۡنَٰكَ إِلَىٰٓ أُمِّكَ كَيۡ تَقَرَّ عَيۡنُهَا وَلَا تَحۡزَنَۚ وَقَتَلۡتَ نَفۡسٗا فَنَجَّيۡنَٰكَ مِنَ ٱلۡغَمِّ وَفَتَنَّٰكَ فُتُونٗاۚ فَلَبِثۡتَ سِنِينَ فِيٓ أَهۡلِ مَدۡيَنَ ثُمَّ جِئۡتَ عَلَىٰ قَدَرٖ يَٰمُوسَىٰ
40. «እህትህ በምትሄድና ‹የሚያሳድገውን ሰው ላመላክታችሁን?› ባለች ጊዜ (መወደድን ጣልኩብህ):: ወደ እናትህም ዓይኗ እንዲረጋና እርሷ እንዳታዝንም መለስንህ:: ነፍስንም ገደልክ ከጭንቅም አዳንንህ:: ፈተናዎችንም ፈተንህ:: በመድየን ቤተሰቦችም ውስጥ ብዙ ዓመታትን ተቀመጥክ:: ከዚያ ሙሳ ሆይ! በተወሰነ ጊዜ ላይ መጣህ::
تفسیرهای عربی:
وَٱصۡطَنَعۡتُكَ لِنَفۡسِي
41. «ለራሴም ለመልዕክተኝነት መረጥኩህ::
تفسیرهای عربی:
ٱذۡهَبۡ أَنتَ وَأَخُوكَ بِـَٔايَٰتِي وَلَا تَنِيَا فِي ذِكۡرِي
42. «አንተና ወንድምህ በተዓምራቴ ሆናችሁ ሂዱ:: እኔንም ከማውሳትም አትቦዝኑ::
تفسیرهای عربی:
ٱذۡهَبَآ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
43. «ወደ ፈርዖን ሂዱ:: እርሱ ወሰን አልፏልና::
تفسیرهای عربی:
فَقُولَا لَهُۥ قَوۡلٗا لَّيِّنٗا لَّعَلَّهُۥ يَتَذَكَّرُ أَوۡ يَخۡشَىٰ
44. «እርሱ ምን አልባትም ይገሰጥ ወይም ይፈራ ዘንድ:: ለእርሱ ለስላሳን ቃል ተናገሩት።»
تفسیرهای عربی:
قَالَا رَبَّنَآ إِنَّنَا نَخَافُ أَن يَفۡرُطَ عَلَيۡنَآ أَوۡ أَن يَطۡغَىٰ
45. «ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ክፋት በመስራት መቸኮሉን ወይም ኩራትን መጨመሩን እንፈራለን።» አሉ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ لَا تَخَافَآۖ إِنَّنِي مَعَكُمَآ أَسۡمَعُ وَأَرَىٰ
46. አላህም አለ: «እኔ በእርግጥ ከናንተ ጋር ነኝና አትፍሩ:: የሚለውንም ሁሉ እሰማለሁ። የሚፈጸመዉንም አያለሁም።
تفسیرهای عربی:
فَأۡتِيَاهُ فَقُولَآ إِنَّا رَسُولَا رَبِّكَ فَأَرۡسِلۡ مَعَنَا بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ وَلَا تُعَذِّبۡهُمۡۖ قَدۡ جِئۡنَٰكَ بِـَٔايَةٖ مِّن رَّبِّكَۖ وَٱلسَّلَٰمُ عَلَىٰ مَنِ ٱتَّبَعَ ٱلۡهُدَىٰٓ
47. እናም ወደ እርሱም ሂዱና (እንዲህ) በሉት: ‹እኛ የጌታህ መልዕክተኞች ነንና የኢስራኢልን ልጆች ሁሉ ከእኛ ጋር ልቀቅ። አታሰቃያቸዉም:: ከጌታህ በሆነው ተዓምር በእርግጥ መጥተንሃልና:: ሰላምም ቀጥታን በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን።
تفسیرهای عربی:
إِنَّا قَدۡ أُوحِيَ إِلَيۡنَآ أَنَّ ٱلۡعَذَابَ عَلَىٰ مَن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
48. «‹እነሆ የአላህ ቅጣት እውነትን ባስተባበለና እምቢ ባለ ሰው ላይ እንደሆነ በእርግጥ አያሌ መልዕክት ተወረደልን።› በሉት።»
تفسیرهای عربی:
قَالَ فَمَن رَّبُّكُمَا يَٰمُوسَىٰ
49. ፈርዖንም «ሙሳ ሆይ! ጌታችሁ ማነው?» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ رَبُّنَا ٱلَّذِيٓ أَعۡطَىٰ كُلَّ شَيۡءٍ خَلۡقَهُۥ ثُمَّ هَدَىٰ
50. «ጌታችን ያ ለፍጥረቱ ሁሉ የሚያስፈልገውን ቅርጹንና ባህሪውን የሰጠው ከዚያም ሁሉንም ለተፈጠረለት የመራው ነው።» አለው።
تفسیرهای عربی:
قَالَ فَمَا بَالُ ٱلۡقُرُونِ ٱلۡأُولَىٰ
51. ፈርዖንም «የመጀመሪያይቱ ዘመናት ህዝቦች ሁኔታስ ምንድን ነው?» አለ::
تفسیرهای عربی:
قَالَ عِلۡمُهَا عِندَ رَبِّي فِي كِتَٰبٖۖ لَّا يَضِلُّ رَبِّي وَلَا يَنسَى
52. ሙሳም «የዚህ ዕውቀት እጌታዬ ዘንድ በመጽሐፍ የተመዘገበ ነው:: ጌታዬ አይሳሳትም አይረሳምም።» አለው።
تفسیرهای عربی:
ٱلَّذِي جَعَلَ لَكُمُ ٱلۡأَرۡضَ مَهۡدٗا وَسَلَكَ لَكُمۡ فِيهَا سُبُلٗا وَأَنزَلَ مِنَ ٱلسَّمَآءِ مَآءٗ فَأَخۡرَجۡنَا بِهِۦٓ أَزۡوَٰجٗا مِّن نَّبَاتٖ شَتَّىٰ
53. ያ ምድርን ለእናንተ ምንጣፍ ያደረገላችሁ በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መንገድን ያገራላችሁ ውሃንም ከሰማይ ያወረደላችሁ ነው። በእርሱም ከተለያየ በቃይ ዓይነቶችን አወጣንላችሁ።
تفسیرهای عربی:
كُلُواْ وَٱرۡعَوۡاْ أَنۡعَٰمَكُمۡۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَٰتٖ لِّأُوْلِي ٱلنُّهَىٰ
54. ለራሳችሁ ብሉ:: እንስሳዎቻችሁንም አግጡ:: (ባዮች ሆነን አወጣንላችሁ።) በዚህ ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች ሁሉ በእርግጥ ተዐምራት አለበት።
تفسیرهای عربی:
۞ مِنۡهَا خَلَقۡنَٰكُمۡ وَفِيهَا نُعِيدُكُمۡ وَمِنۡهَا نُخۡرِجُكُمۡ تَارَةً أُخۡرَىٰ
55. (ሰዎች ሆይ!) ከእርሷ (ከምድር) ፈጠርናችሁ:: ወደ እርሷም ውስጥ እንመልሳችኋለን:: ከእርሷም በሌላ ጊዜ እናወጣችኋለን::
تفسیرهای عربی:
وَلَقَدۡ أَرَيۡنَٰهُ ءَايَٰتِنَا كُلَّهَا فَكَذَّبَ وَأَبَىٰ
56.ተዓምራቶቻችንንም ሁሏንም ለፈርዖን በእርግጥ አሳየነው:: አስተባበለም:: እምቢም አለ::
تفسیرهای عربی:
قَالَ أَجِئۡتَنَا لِتُخۡرِجَنَا مِنۡ أَرۡضِنَا بِسِحۡرِكَ يَٰمُوسَىٰ
57. አለም: «ሙሳ ሆይ! ከምድራችን በድግምትህ ልታወጣን መጣህብን?
تفسیرهای عربی:
فَلَنَأۡتِيَنَّكَ بِسِحۡرٖ مِّثۡلِهِۦ فَٱجۡعَلۡ بَيۡنَنَا وَبَيۡنَكَ مَوۡعِدٗا لَّا نُخۡلِفُهُۥ نَحۡنُ وَلَآ أَنتَ مَكَانٗا سُوٗى
58. «መሰሉንም ድግምት እናመጣብሃለን:: በእኛና ባንተም መካከል እኛም አንተም የማንጥሰው የሆነ ቀጠሮን በመካከለኛ ስፍራ አድርግልን።» አለ::
تفسیرهای عربی:
قَالَ مَوۡعِدُكُمۡ يَوۡمُ ٱلزِّينَةِ وَأَن يُحۡشَرَ ٱلنَّاسُ ضُحٗى
59.ሙሳም: «ቀጠሯችሁ ያ የማጌጫው የበአሉ ቀን ነው። ሰዎችም ረፋድ ላይ እንዲሰበሰቡ ይሁን።» አለ።
تفسیرهای عربی:
فَتَوَلَّىٰ فِرۡعَوۡنُ فَجَمَعَ كَيۡدَهُۥ ثُمَّ أَتَىٰ
60. ፈርዖንም ዞረ:: ተንኮሉን ሰበሰበ:: ከዚያ መጣ::
تفسیرهای عربی:
قَالَ لَهُم مُّوسَىٰ وَيۡلَكُمۡ لَا تَفۡتَرُواْ عَلَى ٱللَّهِ كَذِبٗا فَيُسۡحِتَكُم بِعَذَابٖۖ وَقَدۡ خَابَ مَنِ ٱفۡتَرَىٰ
61.ሙሳም ለእነርሱ: «ወዮላችሁ በአላህ ላይ ውሸትን አትቅጠፉ:: በቅጣት ያጠፋችኋልና:: የቀጠፈም ሰው በእርግጥ አፈረ።» አላቸው።
تفسیرهای عربی:
فَتَنَٰزَعُوٓاْ أَمۡرَهُم بَيۡنَهُمۡ وَأَسَرُّواْ ٱلنَّجۡوَىٰ
62. (ድግምተኞቹ) በመካከላቸውም ነገራቸውን ተጨቃጨቁ፡፡ ውይይትንም ደበቁ፡፡
تفسیرهای عربی:
قَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَٰنِ لَسَٰحِرَٰنِ يُرِيدَانِ أَن يُخۡرِجَاكُم مِّنۡ أَرۡضِكُم بِسِحۡرِهِمَا وَيَذۡهَبَا بِطَرِيقَتِكُمُ ٱلۡمُثۡلَىٰ
63. አሉም: «እነዚህ በእርግጥ ደጋሚዎች ናቸው:: ከምድራችሁ በድግምታቸው ሊያወጧችሁ በላጪቱንም መንገዳችሁን ሊያስወግዱባችሁ ይሻሉ።
تفسیرهای عربی:
فَأَجۡمِعُواْ كَيۡدَكُمۡ ثُمَّ ٱئۡتُواْ صَفّٗاۚ وَقَدۡ أَفۡلَحَ ٱلۡيَوۡمَ مَنِ ٱسۡتَعۡلَىٰ
64. «ተንኮላችሁንም አጠንክሩ:: ከዚያም ተሰልፋችሁ ኑ:: ዛሬ ያሸነፈም ሰው ምኞቱን አገኘ።» ተባባሉ።
تفسیرهای عربی:
قَالُواْ يَٰمُوسَىٰٓ إِمَّآ أَن تُلۡقِيَ وَإِمَّآ أَن نَّكُونَ أَوَّلَ مَنۡ أَلۡقَىٰ
65. «ሙሳ ሆይ! በመጀመሪያ ትጥላለህ ወይስ እኛ እንጣል? (ምረጥ)» አሉ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ بَلۡ أَلۡقُواْۖ فَإِذَا حِبَالُهُمۡ وَعِصِيُّهُمۡ يُخَيَّلُ إِلَيۡهِ مِن سِحۡرِهِمۡ أَنَّهَا تَسۡعَىٰ
66. ሙሳም «እናንተ በመጀመሪያ ጣሉ።» አላቸው። ጣሉም:: ወዲያዉም ገመዶቻቸውና ዘንጎቻቸው ከድግምታቸው የተነሳ የሚሮጡ እባቦች ሆነው (መስለው) ወደ እርሱ ተመሰሉበት።
تفسیرهای عربی:
فَأَوۡجَسَ فِي نَفۡسِهِۦ خِيفَةٗ مُّوسَىٰ
67.ሙሳም በውስጡ ፍርሃት አደረበት::
تفسیرهای عربی:
قُلۡنَا لَا تَخَفۡ إِنَّكَ أَنتَ ٱلۡأَعۡلَىٰ
68. አልነውም: «አትፍራ። የበላዩ አንተ ነህና።
تفسیرهای عربی:
وَأَلۡقِ مَا فِي يَمِينِكَ تَلۡقَفۡ مَا صَنَعُوٓاْۖ إِنَّمَا صَنَعُواْ كَيۡدُ سَٰحِرٖۖ وَلَا يُفۡلِحُ ٱلسَّاحِرُ حَيۡثُ أَتَىٰ
69. «በቀኝ እጅህ ያለችውን ብትር ጣል:: ያንን የሰሩትን ሁሉ ትውጣለችና። ያ የሰሩት ሁሉ የድግምተኛ ተንኮል ብቻ ነውና:: ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናዉም::»
تفسیرهای عربی:
فَأُلۡقِيَ ٱلسَّحَرَةُ سُجَّدٗا قَالُوٓاْ ءَامَنَّا بِرَبِّ هَٰرُونَ وَمُوسَىٰ
70. ድግምተኞቹም ሱጁድ ወረዱ: «በሃሩንና በሙሳ ጌታ አመንን።» አሉ::
تفسیرهای عربی:
قَالَ ءَامَنتُمۡ لَهُۥ قَبۡلَ أَنۡ ءَاذَنَ لَكُمۡۖ إِنَّهُۥ لَكَبِيرُكُمُ ٱلَّذِي عَلَّمَكُمُ ٱلسِّحۡرَۖ فَلَأُقَطِّعَنَّ أَيۡدِيَكُمۡ وَأَرۡجُلَكُم مِّنۡ خِلَٰفٖ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمۡ فِي جُذُوعِ ٱلنَّخۡلِ وَلَتَعۡلَمُنَّ أَيُّنَآ أَشَدُّ عَذَابٗا وَأَبۡقَىٰ
71. (ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁለትን! እርሱ በእርግጥ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ መሪያችሁ ነው:: እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (በማናጋት) ግራንና ቀኝን በማፈራረቅ እቆራርጣችኋለሁ:: በዘምባባም ግንዶች ላይ እሰቅላችኋለሁ:: የማንኛችን ቅጣት በጣም ብርቱና የሚቆይ መሆኑን በዚያ ጊዜ ታውቃላችሁ።» አላቸው።
تفسیرهای عربی:
قَالُواْ لَن نُّؤۡثِرَكَ عَلَىٰ مَا جَآءَنَا مِنَ ٱلۡبَيِّنَٰتِ وَٱلَّذِي فَطَرَنَاۖ فَٱقۡضِ مَآ أَنتَ قَاضٍۖ إِنَّمَا تَقۡضِي هَٰذِهِ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَآ
72. አሉትም: «ከመጡልን ተዓምራትና ከዚያ ከፈጠረን አምላክ ፈጽሞ አናስበልጥህም:: እናም የምትፈርደውን ፍረድ:: የምትፈርደው በዚህች በአነስተኛይቱ ህይወት ብቻ ላይ ነውና።
تفسیرهای عربی:
إِنَّآ ءَامَنَّا بِرَبِّنَا لِيَغۡفِرَ لَنَا خَطَٰيَٰنَا وَمَآ أَكۡرَهۡتَنَا عَلَيۡهِ مِنَ ٱلسِّحۡرِۗ وَٱللَّهُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
73. «ኃጢአቶቻችንንና ከድግምትም እንድንፈጽመው ያስገደድከንን ይምረን ዘንድ እኛ በጌታችን አምነናል:: አላህ በጣም በላጭ ነው:: ቅጣቱም ሆነ ምንዳው በጣም የሚዘወትር ነው።» አሉ።
تفسیرهای عربی:
إِنَّهُۥ مَن يَأۡتِ رَبَّهُۥ مُجۡرِمٗا فَإِنَّ لَهُۥ جَهَنَّمَ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
74. ከሃዲ ሆኖ ወደ ጌታው የሚመጣ (የሚሞት) ሰው ሁሉ ለእርሱ ገሀነም አለችለት:: በውስጧም አይሞትም ህያዉም አይሆንም::
تفسیرهای عربی:
وَمَن يَأۡتِهِۦ مُؤۡمِنٗا قَدۡ عَمِلَ ٱلصَّٰلِحَٰتِ فَأُوْلَٰٓئِكَ لَهُمُ ٱلدَّرَجَٰتُ ٱلۡعُلَىٰ
75.እነዚያ በጎ ስራዎችን የሰሩና አማኝ ሆነው ወደ ጌታቸው የመጡ ሰዎች ደግሞ እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አሏቸው::
تفسیرهای عربی:
جَنَّٰتُ عَدۡنٖ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَاۚ وَذَٰلِكَ جَزَآءُ مَن تَزَكَّىٰ
76.ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው የመኖሪያ ገነቶች በውስጣቸው ዘውታሪዎች ሲሆኑ አሏቸው:: ይህም አይነቱ ክፍያ ለተጥራራ ሁሉ ምንዳው ነው::
تفسیرهای عربی:
وَلَقَدۡ أَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰ مُوسَىٰٓ أَنۡ أَسۡرِ بِعِبَادِي فَٱضۡرِبۡ لَهُمۡ طَرِيقٗا فِي ٱلۡبَحۡرِ يَبَسٗا لَّا تَخَٰفُ دَرَكٗا وَلَا تَخۡشَىٰ
77. ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ በሌሊት ሂድ:: ለእነርሱም በባህር ውስጥ ደረቅ መንገድን አድርግላቸው:: ፈርዖን ያገኘኛል ብለህ አትፍራ:: ከመስመጥም አትጨነቅ።» ስንል በእርግጥ ላክንበት።
تفسیرهای عربی:
فَأَتۡبَعَهُمۡ فِرۡعَوۡنُ بِجُنُودِهِۦ فَغَشِيَهُم مِّنَ ٱلۡيَمِّ مَا غَشِيَهُمۡ
78. ፈርዖን ከሰራዊቱ ጋር ሆኖ ተከተላቸው:: ከባህሩም የሚሸፍን ነገር ሸፈናቸው።
تفسیرهای عربی:
وَأَضَلَّ فِرۡعَوۡنُ قَوۡمَهُۥ وَمَا هَدَىٰ
79.ፈርዖንም ህዝቦቹን አሳሳታቸው:: ቅኑንም መንገድ አልመራቸዉም::
تفسیرهای عربی:
يَٰبَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ قَدۡ أَنجَيۡنَٰكُم مِّنۡ عَدُوِّكُمۡ وَوَٰعَدۡنَٰكُمۡ جَانِبَ ٱلطُّورِ ٱلۡأَيۡمَنَ وَنَزَّلۡنَا عَلَيۡكُمُ ٱلۡمَنَّ وَٱلسَّلۡوَىٰ
80. የኢስራኢል ልጆች ሆይ! ከጠላታችሁ በእርግጥ አዳንናችሁ:: በጡር ተራራም ቀኝ ጎን ላይ ቀጠሮ አደረግንላችሁ። በእናንተም ላይ መናንና ሰልዋን (ድርጭት) አወረድንላችሁ።
تفسیرهای عربی:
كُلُواْ مِن طَيِّبَٰتِ مَا رَزَقۡنَٰكُمۡ وَلَا تَطۡغَوۡاْ فِيهِ فَيَحِلَّ عَلَيۡكُمۡ غَضَبِيۖ وَمَن يَحۡلِلۡ عَلَيۡهِ غَضَبِي فَقَدۡ هَوَىٰ
81. ከሰጠናችሁ ሲሳይ ከመልካሙ ብሉ:: በእርሱም ወሰንን አትለፉ:: ቁጣዬ በእናንተ ላይ ይወርድባችኋልና:: ቁጣዬ የሚወርድበት ሁሉ በእርግጥ ይጠፋል::
تفسیرهای عربی:
وَإِنِّي لَغَفَّارٞ لِّمَن تَابَ وَءَامَنَ وَعَمِلَ صَٰلِحٗا ثُمَّ ٱهۡتَدَىٰ
82.እኔም ለተጸጸተ ላመነም መልካምንም ለሰራ ከዚያ ለተመራ ሁሉ በእርግጥ መሓሪ ነኝ::
تفسیرهای عربی:
۞ وَمَآ أَعۡجَلَكَ عَن قَوۡمِكَ يَٰمُوسَىٰ
83. «ሙሳ ሆይ! ከህዝቦችህ ምን አስቸኮለህ?» ተባለ::
تفسیرهای عربی:
قَالَ هُمۡ أُوْلَآءِ عَلَىٰٓ أَثَرِي وَعَجِلۡتُ إِلَيۡكَ رَبِّ لِتَرۡضَىٰ
84. «እነርሱ እነዚህ በዱካዬ ላይ ያሉ ናቸው:: ጌታዬ ሆይ! ትወድልኝ ዘንድ ወደ አንተ ቸኮልኩ።» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ فَإِنَّا قَدۡ فَتَنَّا قَوۡمَكَ مِنۢ بَعۡدِكَ وَأَضَلَّهُمُ ٱلسَّامِرِيُّ
85.(አላህም) «እኛም ካንተ በኋላ ሰዎችህን በእርግጥ ፈተንን:: ሳምራዊዉም አሳሳታቸው።» አለው::
تفسیرهای عربی:
فَرَجَعَ مُوسَىٰٓ إِلَىٰ قَوۡمِهِۦ غَضۡبَٰنَ أَسِفٗاۚ قَالَ يَٰقَوۡمِ أَلَمۡ يَعِدۡكُمۡ رَبُّكُمۡ وَعۡدًا حَسَنًاۚ أَفَطَالَ عَلَيۡكُمُ ٱلۡعَهۡدُ أَمۡ أَرَدتُّمۡ أَن يَحِلَّ عَلَيۡكُمۡ غَضَبٞ مِّن رَّبِّكُمۡ فَأَخۡلَفۡتُم مَّوۡعِدِي
86. ሙሳም ወደ ሰዎች የተቆጣና ያዘነ ሆኖ ተመለሰ:: «ህዝቦቼ ሆይ! ጌታችሁ መልካም ተስፋን አልቀጠራችሁምን? ቀጠሮው በእናንተ ላይ ረዘመባችሁን? ወይስ በእናንተ ላይ ከጌታችሁ ቅጣት ሊወርድባችሁ ፈለጋችሁና ቃል ኪዳኔን አፈረሳችሁ?» አላቸው::
تفسیرهای عربی:
قَالُواْ مَآ أَخۡلَفۡنَا مَوۡعِدَكَ بِمَلۡكِنَا وَلَٰكِنَّا حُمِّلۡنَآ أَوۡزَارٗا مِّن زِينَةِ ٱلۡقَوۡمِ فَقَذَفۡنَٰهَا فَكَذَٰلِكَ أَلۡقَى ٱلسَّامِرِيُّ
87. «ቀጠሮህን በፈቃዳችን አልጣስንም:: ግን እኛ ከህዝቦች ጌጥ ሸክሞችን ተጫን:: በእሳት ላይ ጣልናትም:: ሳምራዊዉም እንደዚሁ አብሮን ጣለ።» አሉት።
تفسیرهای عربی:
فَأَخۡرَجَ لَهُمۡ عِجۡلٗا جَسَدٗا لَّهُۥ خُوَارٞ فَقَالُواْ هَٰذَآ إِلَٰهُكُمۡ وَإِلَٰهُ مُوسَىٰ فَنَسِيَ
88. ለእነርሱም የመጓጎር ባህሪ ያለውን ጥጃን (መሰል) አካልን አወጣላቸው። «ተከታዮቹ ሆይ! ይህ የእናንተም ሆነ የሙሳ አምላክ ነው:: ግን ረሳው እንጂ።» አሉ።
تفسیرهای عربی:
أَفَلَا يَرَوۡنَ أَلَّا يَرۡجِعُ إِلَيۡهِمۡ قَوۡلٗا وَلَا يَمۡلِكُ لَهُمۡ ضَرّٗا وَلَا نَفۡعٗا
89.ወደ እነርሱ ንግግርን የማይመልስ ለእነርሱም ጉዳትንና ጥቅምን የማይችል መሆኑን አያዩምን?
تفسیرهای عربی:
وَلَقَدۡ قَالَ لَهُمۡ هَٰرُونُ مِن قَبۡلُ يَٰقَوۡمِ إِنَّمَا فُتِنتُم بِهِۦۖ وَإِنَّ رَبَّكُمُ ٱلرَّحۡمَٰنُ فَٱتَّبِعُونِي وَأَطِيعُوٓاْ أَمۡرِي
90-.ከዚያ በፊት ሀሩንም በእርግጥ አላቸው: «ህዝቦቼ ሆይ! ይህ በእርሱ የተሞከራችሁበት ብቻ ነው:: ጌታችሁም አር-ረህማን ነው:: ተከተሉኝም፤ ትእዛዜንም ስሙ።»
تفسیرهای عربی:
قَالُواْ لَن نَّبۡرَحَ عَلَيۡهِ عَٰكِفِينَ حَتَّىٰ يَرۡجِعَ إِلَيۡنَا مُوسَىٰ
91. «ሙሳ ወደ እኛ እስከሚመለስ በእርሱ መገዛት ላይ ከመቆየት ፈጽሞ አንወገድም።» አሉ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ يَٰهَٰرُونُ مَا مَنَعَكَ إِذۡ رَأَيۡتَهُمۡ ضَلُّوٓاْ
92- ሙሳም አለ፡- «ሃሩን ሆይ! ተሳስተው ባየሃቸው ጊዜ ምን ከለከለህ?
تفسیرهای عربی:
أَلَّا تَتَّبِعَنِۖ أَفَعَصَيۡتَ أَمۡرِي
93. «እኔን ከመከተል? ትእዛዜን ጣስክን?» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ يَبۡنَؤُمَّ لَا تَأۡخُذۡ بِلِحۡيَتِي وَلَا بِرَأۡسِيٓۖ إِنِّي خَشِيتُ أَن تَقُولَ فَرَّقۡتَ بَيۡنَ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ وَلَمۡ تَرۡقُبۡ قَوۡلِي
94. «ሃሩን የእናቴ ልጅ ሆይ! ፂሜንም ሆነ ራሴን አትያዝ:: እኔ ‹በኢስራኢል ልጆች መካከል ለያየህ ቃሌንም አልጠበክም› ማለትህን ፈራሁና ነው።» አለው።
تفسیرهای عربی:
قَالَ فَمَا خَطۡبُكَ يَٰسَٰمِرِيُّ
95. ሙሳም «ሳምራዊው ሆይ! ነገርህ ምንድን ነው?» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ بَصُرۡتُ بِمَا لَمۡ يَبۡصُرُواْ بِهِۦ فَقَبَضۡتُ قَبۡضَةٗ مِّنۡ أَثَرِ ٱلرَّسُولِ فَنَبَذۡتُهَا وَكَذَٰلِكَ سَوَّلَتۡ لِي نَفۡسِي
96. ሳምራዊውም: «እነርሱ ያላዩትን ነገር አየሁ:: ከመልዕክተኛው ፈረስ ኮቴ ዱካም ጭብጥ አፈርን ዘገንኩ:: በቅርጹ ላይ ጣልኳትም:: ልክ እንደዚሁ ነፍሴ ሸለመችልኝ።» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ فَٱذۡهَبۡ فَإِنَّ لَكَ فِي ٱلۡحَيَوٰةِ أَن تَقُولَ لَا مِسَاسَۖ وَإِنَّ لَكَ مَوۡعِدٗا لَّن تُخۡلَفَهُۥۖ وَٱنظُرۡ إِلَىٰٓ إِلَٰهِكَ ٱلَّذِي ظَلۡتَ عَلَيۡهِ عَاكِفٗاۖ لَّنُحَرِّقَنَّهُۥ ثُمَّ لَنَنسِفَنَّهُۥ فِي ٱلۡيَمِّ نَسۡفًا
97. ሙሳም ለሳምራዊው አለው: «ሂድ። በህይወትህ ላየኸው ሰው ሁሉ ‹መነካካት የለም› እያልክ ኑር:: ላንተም ፈጽሞ የማትቀር ቀጠሮ አለህ:: ወደ እዚያዉም በእርሱ ላይ ተገዢው ሆነህ ወደ ቆየህበት አምላክህ ተመልከት:: በእርግጥ እናቃጥለዋለን:: ከዚያም በባህሩ ውስጥ እንበትነዋለን::»
تفسیرهای عربی:
إِنَّمَآ إِلَٰهُكُمُ ٱللَّهُ ٱلَّذِي لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَۚ وَسِعَ كُلَّ شَيۡءٍ عِلۡمٗا
98.(ሰዎች ሆይ!) ጌታችሁም ያ ከእርሱ በስተቀር ሌላ አምላክ የሌለ የሆነው አላህ ብቻ ነው:: እውቀቱ ሁሉን ነገር አዳረሰ::
تفسیرهای عربی:
كَذَٰلِكَ نَقُصُّ عَلَيۡكَ مِنۡ أَنۢبَآءِ مَا قَدۡ سَبَقَۚ وَقَدۡ ءَاتَيۡنَٰكَ مِن لَّدُنَّا ذِكۡرٗا
99. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ልክ እንደዚሁ በእርግጥ ካለፉት ወሬዎች ባንተ ላይ እንተርካለን፤ ከእኛም ዘንድ ቁርኣንን በእርግጥ ሰጠንህ::
تفسیرهای عربی:
مَّنۡ أَعۡرَضَ عَنۡهُ فَإِنَّهُۥ يَحۡمِلُ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ وِزۡرًا
100.ከእርሱ ያፈገፈገ ሰው እርሱ በትንሳኤ ቀን ከባድን ቅጣት ይሸከማል::
تفسیرهای عربی:
خَٰلِدِينَ فِيهِۖ وَسَآءَ لَهُمۡ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ حِمۡلٗا
101.በእርሱ ውስጥ ዘውታሪዎች ሆነው ይሸከማሉ:: በትንሳኤ ቀን ለእነርሱ እጣ ፈንታ የሆነው ሸክም ከፋ!
تفسیرهای عربی:
يَوۡمَ يُنفَخُ فِي ٱلصُّورِۚ وَنَحۡشُرُ ٱلۡمُجۡرِمِينَ يَوۡمَئِذٖ زُرۡقٗا
102. በቀንዱ በሚነፋ ቀን ሸክማቸው ከፋ:: ከሓዲያን በዚያ ቀን ዓይኖቻቸው ሰማያዊዎች ሆነው እንሰበስባቸዋለን::
تفسیرهای عربی:
يَتَخَٰفَتُونَ بَيۡنَهُمۡ إِن لَّبِثۡتُمۡ إِلَّا عَشۡرٗا
103. «አስርን (ቀን) እንጂ አልቆያችሁም።» በመባባል በመካከላቸው ይንሾካሾካሉ::
تفسیرهای عربی:
نَّحۡنُ أَعۡلَمُ بِمَا يَقُولُونَ إِذۡ يَقُولُ أَمۡثَلُهُمۡ طَرِيقَةً إِن لَّبِثۡتُمۡ إِلَّا يَوۡمٗا
104. በሃሳብ ቀጥተኛቸው «አንድን ቀን እንጂ አልቆያችሁም።» በሚል ጊዜ የሚሉትን ነገር እኛ አዋቂዎች ነን።
تفسیرهای عربی:
وَيَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلۡجِبَالِ فَقُلۡ يَنسِفُهَا رَبِّي نَسۡفٗا
105. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከጋራዎች ይጠይቁሃልና (እንዲህ) በላቸው: «ጌታዬ መበተንን ይበትናቸዋል።
تفسیرهای عربی:
فَيَذَرُهَا قَاعٗا صَفۡصَفٗا
106. «ትክክል ሜዳም ሆና ይተዋታል።
تفسیرهای عربی:
لَّا تَرَىٰ فِيهَا عِوَجٗا وَلَآ أَمۡتٗا
107. «በእርሷ ዝቅታና ከፍታን ፈጽሞ አታይም።»
تفسیرهای عربی:
يَوۡمَئِذٖ يَتَّبِعُونَ ٱلدَّاعِيَ لَا عِوَجَ لَهُۥۖ وَخَشَعَتِ ٱلۡأَصۡوَاتُ لِلرَّحۡمَٰنِ فَلَا تَسۡمَعُ إِلَّا هَمۡسٗا
108. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በዚያ ቀን ለመሰብሰብ ጠሪውን ምንም እንከን የሌለውን ተጣሪ ይከተላሉ:: ድምፆችም ሁሉ ለአር-ረህማን ጸጥ ይላሉ:: ስለዚህ (የኮቴ) ሹክሹክታን እንጂ አትሰማም።
تفسیرهای عربی:
يَوۡمَئِذٖ لَّا تَنفَعُ ٱلشَّفَٰعَةُ إِلَّا مَنۡ أَذِنَ لَهُ ٱلرَّحۡمَٰنُ وَرَضِيَ لَهُۥ قَوۡلٗا
109.በዚያ ቀን ለእርሱ አር-ረህማን የፈቀደለትንና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ብቻ ቢሆን እንጂ ምልጃ አንድንም አትጠቅምም::
تفسیرهای عربی:
يَعۡلَمُ مَا بَيۡنَ أَيۡدِيهِمۡ وَمَا خَلۡفَهُمۡ وَلَا يُحِيطُونَ بِهِۦ عِلۡمٗا
110. በስተፊታቸው ያለውንም ሆነ በስተኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል:: በእርሱ ላይ ግን ማንም በእውቀቱ አያካብብም::
تفسیرهای عربی:
۞ وَعَنَتِ ٱلۡوُجُوهُ لِلۡحَيِّ ٱلۡقَيُّومِۖ وَقَدۡ خَابَ مَنۡ حَمَلَ ظُلۡمٗا
111. ፊቶችም ሁሉ ህያውና የሁሉ አስተናባሪ ለሆነው አላህ ተዋረዱ:: በደልንም የተሸከመ በእርግጥ ከሰረ::
تفسیرهای عربی:
وَمَن يَعۡمَلۡ مِنَ ٱلصَّٰلِحَٰتِ وَهُوَ مُؤۡمِنٞ فَلَا يَخَافُ ظُلۡمٗا وَلَا هَضۡمٗا
112. አማኝ ሆኖ መልካም ስራዎችን የሰራ በደልንም ሆነ መጉደልን አይፈራም::
تفسیرهای عربی:
وَكَذَٰلِكَ أَنزَلۡنَٰهُ قُرۡءَانًا عَرَبِيّٗا وَصَرَّفۡنَا فِيهِ مِنَ ٱلۡوَعِيدِ لَعَلَّهُمۡ يَتَّقُونَ أَوۡ يُحۡدِثُ لَهُمۡ ذِكۡرٗا
113.ልክ እንደዚሁም ዐረብኛ ቁርኣን ሆኖ አወረድነው:: አላህን ይፈሩ ዘንድ ወይም ለእነርሱ ግሣጼን ያድስላቸው ዘንድ ከዛቻ ደጋግመን በውስጡ ገለጽን::
تفسیرهای عربی:
فَتَعَٰلَى ٱللَّهُ ٱلۡمَلِكُ ٱلۡحَقُّۗ وَلَا تَعۡجَلۡ بِٱلۡقُرۡءَانِ مِن قَبۡلِ أَن يُقۡضَىٰٓ إِلَيۡكَ وَحۡيُهُۥۖ وَقُل رَّبِّ زِدۡنِي عِلۡمٗا
114. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) እውነተኛው ንጉስ አላህ ከሓዲያን ከሚሉት ነገር ሁሉ ላቀ:: ወደ አንተ መወረዱም ከመፈጸሙ በፊት ቁርኣንን በማንበብ አትቸኩል:: «ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ጨምርልኝ።» በልም።
تفسیرهای عربی:
وَلَقَدۡ عَهِدۡنَآ إِلَىٰٓ ءَادَمَ مِن قَبۡلُ فَنَسِيَ وَلَمۡ نَجِدۡ لَهُۥ عَزۡمٗا
115. ወደ አደምም ከዚህ በፊት ቃል ኪዳንን በእርግጥ አወረድንና ረሳ:: ለእርሱም ቆራጥነትን አላገኘንለትም::
تفسیرهای عربی:
وَإِذۡ قُلۡنَا لِلۡمَلَٰٓئِكَةِ ٱسۡجُدُواْ لِأٓدَمَ فَسَجَدُوٓاْ إِلَّآ إِبۡلِيسَ أَبَىٰ
116.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ለመላእክትም «ለአደም ስገዱ።» ባልን ጊዜ (የሆነውን አስታውስ):: እነርሱም ዲያብሎስ ብቻ ሲቀር ሰገዱ:: እሱማ እምቢ አለ::
تفسیرهای عربی:
فَقُلۡنَا يَٰٓـَٔادَمُ إِنَّ هَٰذَا عَدُوّٞ لَّكَ وَلِزَوۡجِكَ فَلَا يُخۡرِجَنَّكُمَا مِنَ ٱلۡجَنَّةِ فَتَشۡقَىٰٓ
117.ከዚያም አልን: «አደም ሆይ! ይህ ላንተም ለሚስትህም በእርግጥ ጠላት ነው:: ስለዚህ ከገነት አያውጣችሁ፤ ትለፋለህና::
تفسیرهای عربی:
إِنَّ لَكَ أَلَّا تَجُوعَ فِيهَا وَلَا تَعۡرَىٰ
118.(አደም ሆይ!) «ላንተ በእርሷ ውስጥ አለመራብና አለመታረዝ አለህ::
تفسیرهای عربی:
وَأَنَّكَ لَا تَظۡمَؤُاْ فِيهَا وَلَا تَضۡحَىٰ
119. «አንተም ከእርሷ ውስጥ አትጠማም:: በጸሐይም አትተኮስም።»
تفسیرهای عربی:
فَوَسۡوَسَ إِلَيۡهِ ٱلشَّيۡطَٰنُ قَالَ يَٰٓـَٔادَمُ هَلۡ أَدُلُّكَ عَلَىٰ شَجَرَةِ ٱلۡخُلۡدِ وَمُلۡكٖ لَّا يَبۡلَىٰ
120. ሰይጣን ወደ እርሱ (አደም) « አደም ሆይ! በመዘውተሪያ ዛፍ በማይጠፋ ንግስናም ላይ ላመላክትህን?» በማለት ጎተጎተ።
تفسیرهای عربی:
فَأَكَلَا مِنۡهَا فَبَدَتۡ لَهُمَا سَوۡءَٰتُهُمَا وَطَفِقَا يَخۡصِفَانِ عَلَيۡهِمَا مِن وَرَقِ ٱلۡجَنَّةِۚ وَعَصَىٰٓ ءَادَمُ رَبَّهُۥ فَغَوَىٰ
121.ከእርሷም በሉ:: ለእነርሱም ሀፍረተ ገላቸው ተገለጸች:: ከገነትም ቅጠል በላያቸው ላይ ይለጥፉ ጀመር:: አደምም የጌታውን ትእዛዝ ረስቶ ጣሰ:: ተሳሳተም::
تفسیرهای عربی:
ثُمَّ ٱجۡتَبَٰهُ رَبُّهُۥ فَتَابَ عَلَيۡهِ وَهَدَىٰ
122. ከዚያም ጌታው መረጠው:: ከእርሱም ጸጸቱን ተቀበለው:: መራዉም::
تفسیرهای عربی:
قَالَ ٱهۡبِطَا مِنۡهَا جَمِيعَۢاۖ بَعۡضُكُمۡ لِبَعۡضٍ عَدُوّٞۖ فَإِمَّا يَأۡتِيَنَّكُم مِّنِّي هُدٗى فَمَنِ ٱتَّبَعَ هُدَايَ فَلَا يَضِلُّ وَلَا يَشۡقَىٰ
123.አላህም አላቸው፡- «ከፊላችሁ ለከፊሉ ጠላት ሲሆን (አደምና ሐዋ) ሁላችሁም ከእርሷ ውረዱ:: ከእኔ የሆነ መመሪያ ቢመጣላችሁ መመሪያየን የተከተለ ሁሉ አይሳሳትም:: አይቸገርምም::
تفسیرهای عربی:
وَمَنۡ أَعۡرَضَ عَن ذِكۡرِي فَإِنَّ لَهُۥ مَعِيشَةٗ ضَنكٗا وَنَحۡشُرُهُۥ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ أَعۡمَىٰ
124. «ከግሳጼዬ የዞረ ግን በዚህች ዓለም ጠባብ ኑሮ አለው:: በትንሳኤ ቀንም ዕውር ሆኖ እንቀሰቅሰዋለን::»
تفسیرهای عربی:
قَالَ رَبِّ لِمَ حَشَرۡتَنِيٓ أَعۡمَىٰ وَقَدۡ كُنتُ بَصِيرٗا
125. «ጌታዬ ሆይ! ለምን ዕውር አድርገህ አስነሳኸኝ:: በእርግጥ የማይ የነበርኩ ስሆን» አለ።
تفسیرهای عربی:
قَالَ كَذَٰلِكَ أَتَتۡكَ ءَايَٰتُنَا فَنَسِيتَهَاۖ وَكَذَٰلِكَ ٱلۡيَوۡمَ تُنسَىٰ
126. «ነገሩ ልክ እንደዚሁ ነው:: ተዓምራቶቻችን መጡልህና ተውካቸውም:: ልክ እንደዚሁም ዛሬ ትተዋለህ።» ይለዋል።
تفسیرهای عربی:
وَكَذَٰلِكَ نَجۡزِي مَنۡ أَسۡرَفَ وَلَمۡ يُؤۡمِنۢ بِـَٔايَٰتِ رَبِّهِۦۚ وَلَعَذَابُ ٱلۡأٓخِرَةِ أَشَدُّ وَأَبۡقَىٰٓ
127.እንደዚሁም ያጋራንና በጌታው አናቅጽ ያላመነን እንቀጣዋለን:: የመጨረሻይቱ ዓለም ቅጣት በጣም ብርቱና ለሁልጊዜም ዘውታሪ ነው::
تفسیرهای عربی:
أَفَلَمۡ يَهۡدِ لَهُمۡ كَمۡ أَهۡلَكۡنَا قَبۡلَهُم مِّنَ ٱلۡقُرُونِ يَمۡشُونَ فِي مَسَٰكِنِهِمۡۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَٰتٖ لِّأُوْلِي ٱلنُّهَىٰ
128. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ቁረይሾች) ከእነርሱ በፊት ከክፍለ ዘመናት ህዝቦች ብዙዎችን ያጠፋን መሆናችን በመኖሪያዎቻቸው የሚሄዱ ሆነው ሳሉ ለእነርሱ አልተገለጸላቸዉምን? በዚህ ውስጥ ለአእምሮ ባለቤቶች በእርግጥ መልዕክቶች አሉበት::
تفسیرهای عربی:
وَلَوۡلَا كَلِمَةٞ سَبَقَتۡ مِن رَّبِّكَ لَكَانَ لِزَامٗا وَأَجَلٞ مُّسَمّٗى
129.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከጌታህ ያለፈች ቃልና የተወሰነ ጊዜ ባልነበረ ኖሮ ቅጣቱ አሁኑኑ የሚይዛቸው ይሆን ነበር::
تفسیرهای عربی:
فَٱصۡبِرۡ عَلَىٰ مَا يَقُولُونَ وَسَبِّحۡ بِحَمۡدِ رَبِّكَ قَبۡلَ طُلُوعِ ٱلشَّمۡسِ وَقَبۡلَ غُرُوبِهَاۖ وَمِنۡ ءَانَآيِٕ ٱلَّيۡلِ فَسَبِّحۡ وَأَطۡرَافَ ٱلنَّهَارِ لَعَلَّكَ تَرۡضَىٰ
130. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! ) በሚሉትም ሁሉ ላይ ታገሥ፤ ጌታህንም ጸሐይ ከመውጣቷ በፊትና ከመግባቷም በፊት የምታመሰግን ሆነህ አጥራው:: ከሌሊት ሰዓቶችም በቀን ጫፎችም አጥራው:: በሚሰጥህ ምንዳ ልትወድ ይከጀላልና::
تفسیرهای عربی:
وَلَا تَمُدَّنَّ عَيۡنَيۡكَ إِلَىٰ مَا مَتَّعۡنَا بِهِۦٓ أَزۡوَٰجٗا مِّنۡهُمۡ زَهۡرَةَ ٱلۡحَيَوٰةِ ٱلدُّنۡيَا لِنَفۡتِنَهُمۡ فِيهِۚ وَرِزۡقُ رَبِّكَ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰ
131.ዐይኖችህን ከሰዎች የተወሰኑ ክፍሎችን ልንፈትናቸው ወደ አጣቀምንበት ወደ ቅርቢቱ ህይወት ጌጦች አትዘርጋ:: የጌታህ ሲሳይ በጣም በላጭና ዘውታሪ ነው።
تفسیرهای عربی:
وَأۡمُرۡ أَهۡلَكَ بِٱلصَّلَوٰةِ وَٱصۡطَبِرۡ عَلَيۡهَاۖ لَا نَسۡـَٔلُكَ رِزۡقٗاۖ نَّحۡنُ نَرۡزُقُكَۗ وَٱلۡعَٰقِبَةُ لِلتَّقۡوَىٰ
132.(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ቤተሰብህንም በሶላት ላይ እዘዝ:: አንተም በእርሷ ላይ ዘውትር:: ሲሳይን አንጠይቅህም:: እኛ እንሰጥሃለን:: መልካሚቱ መጨረሻ ለጥንቁቆቹ ናት::
تفسیرهای عربی:
وَقَالُواْ لَوۡلَا يَأۡتِينَا بِـَٔايَةٖ مِّن رَّبِّهِۦٓۚ أَوَلَمۡ تَأۡتِهِم بَيِّنَةُ مَا فِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
133. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ተከራካሪዎችህ «ከጌታው በሆነ ተዓምር አይመጣምን?» አሉ:: በመጀመሪያዎቹ ጹሁፎች ውስጥ ያለችው ማስረጃ አልመጣቻቸዉምን?
تفسیرهای عربی:
وَلَوۡ أَنَّآ أَهۡلَكۡنَٰهُم بِعَذَابٖ مِّن قَبۡلِهِۦ لَقَالُواْ رَبَّنَا لَوۡلَآ أَرۡسَلۡتَ إِلَيۡنَا رَسُولٗا فَنَتَّبِعَ ءَايَٰتِكَ مِن قَبۡلِ أَن نَّذِلَّ وَنَخۡزَىٰ
134. እኛም (ከሙሐመድ መላክ) በፊት በቅጣት ባጠፋናቸው ኖሮ «ጌታችን ሆይ! ከመዋረዳችንና ከማፈራችን በፊት አናቅጽህን እንከተል ዘንድ ወደኛ መልዕክተኛን አትልክልንም ነበርን?» ባሉ ነበር::
تفسیرهای عربی:
قُلۡ كُلّٞ مُّتَرَبِّصٞ فَتَرَبَّصُواْۖ فَسَتَعۡلَمُونَ مَنۡ أَصۡحَٰبُ ٱلصِّرَٰطِ ٱلسَّوِيِّ وَمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
135. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «ሁሉም ተጠባባቂ ነው:: ተጠባበቁም የቀጥታዉም መንገድ ባለቤቶች እነማን እንደ ሆኑ እነማንም እንደ ተመሩ ወደፊት ታውቃላችሁ።» በላቸው::
تفسیرهای عربی:
 
ترجمهٔ معانی سوره: طه
فهرست سوره ها شماره صفحه
 
ترجمهٔ معانی قرآن کریم - ترجمه‌ى امهری ـ آکادمی آفریقا - لیست ترجمه ها

مترجم: محمد زین زهرالدین. آکادمی آفریقا آن را منتشر كرده است.

بستن