Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Firo amhariiwo * - Tippudi firooji ɗii

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Firo maanaaji Simoore: Simoore hoodere   Aaya:

ሱረቱ አን ነጅም

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ
ባልደረባችሁ (ነቢያችን ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ
ኀይሎቹ ብርቱው አስተማረው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
Faccirooji aarabeeji:
وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
Faccirooji aarabeeji:
عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
Faccirooji aarabeeji:
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
Faccirooji aarabeeji:
إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
Faccirooji aarabeeji:
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?) (የላቸውም)።
Faccirooji aarabeeji:
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
Faccirooji aarabeeji:
تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍፍል ናት፡፡
Faccirooji aarabeeji:
إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?
Faccirooji aarabeeji:
فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ
በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا
ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊመነዳ (ሊቀጣ) እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (ነው)፡፡
Faccirooji aarabeeji:
ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ (የሚማሩ) ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
Faccirooji aarabeeji:
وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
Faccirooji aarabeeji:
أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
Faccirooji aarabeeji:
أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
Faccirooji aarabeeji:
وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
Faccirooji aarabeeji:
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ
ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
Faccirooji aarabeeji:
ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ
መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا
እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ
እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
Faccirooji aarabeeji:
وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
Faccirooji aarabeeji:
هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
Faccirooji aarabeeji:
لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡
Faccirooji aarabeeji:
أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ
ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?
Faccirooji aarabeeji:
وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
Faccirooji aarabeeji:
وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
Faccirooji aarabeeji:
فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡ {1}
{1} ኢዝህ አንድ የንባብ ሱጁድ (ሱጁዱትላዋ) ይደረጋል።
Faccirooji aarabeeji:
 
Firo maanaaji Simoore: Simoore hoodere
Tippudi cimooje Tonngoode hello ngoo
 
Firo maanaaji al-quraan tedduɗo oo - Firo amhariiwo - Tippudi firooji ɗii

Firo maaniiwo al-quraan tedduɗo oo fayde e ɗemngal amhari, firi ɗum ko Mawɗo Muhammad Saadiq e Muhammad ɗiɗaɓo Habiib. Ngo feewnitaama e njiimaandi hentorde kanngameeji firo, inanewnaa ƴellitaade e firo asliiwo ngoo mgam feññinde yiyannde e horo kam e ƴellito duumiingo.

Uddude