Check out the new design

કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - એમ્હારિક ભાષામાં અનુવાદ - આફ્રિકન એકેડમી * - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા


શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: ગાફિર   આયત:
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا رُسُلٗا مِّن قَبۡلِكَ مِنۡهُم مَّن قَصَصۡنَا عَلَيۡكَ وَمِنۡهُم مَّن لَّمۡ نَقۡصُصۡ عَلَيۡكَۗ وَمَا كَانَ لِرَسُولٍ أَن يَأۡتِيَ بِـَٔايَةٍ إِلَّا بِإِذۡنِ ٱللَّهِۚ فَإِذَا جَآءَ أَمۡرُ ٱللَّهِ قُضِيَ بِٱلۡحَقِّ وَخَسِرَ هُنَالِكَ ٱلۡمُبۡطِلُونَ
78. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ካንተ በፊትም መልዕክተኞችን በእርግጥ ልከናል። ከእነርሱ ባንተ ላይ የተረክንልህ አለ:: ከእነርሱም ባንተ ላይ ያልተረክነውም አለ:: ለማንኛዉም መልዕክተኛ በአላህ ፈቃድ ካልሆነ በስተቀር ተዓምርን ሊያመጣ አይገባዉም:: የአላህም ትዕዛዝ በመጣ ጊዜ በእውነት ይፈረዳል:: እዚያ ዘንድም አጥፊዎች ይከስራሉ::
અરબી તફસીરો:
ٱللَّهُ ٱلَّذِي جَعَلَ لَكُمُ ٱلۡأَنۡعَٰمَ لِتَرۡكَبُواْ مِنۡهَا وَمِنۡهَا تَأۡكُلُونَ
79. አላህ ያ ለእናንተ ግመልን ከብትንና ፍየልን ከእርሷ ከፊሏን ልትጋልቡ የፈጠረላችሁ ነውና:: ከእርሷም ትበላላችሁ::
અરબી તફસીરો:
وَلَكُمۡ فِيهَا مَنَٰفِعُ وَلِتَبۡلُغُواْ عَلَيۡهَا حَاجَةٗ فِي صُدُورِكُمۡ وَعَلَيۡهَا وَعَلَى ٱلۡفُلۡكِ تُحۡمَلُونَ
80. ለእናተም በርሷ ውስጥ ጥቅሞች አሏችሁ:: በእርሷም ላይ ዕቃን በመጫን በልቦቻችሁ ያሰባችሁትን ጉዳይ ትደርሱ ዘንድ ፈጠረላችሁ። በእርሷም ላይ በመርከቦችም ላይ ትሳፈራላችሁ::
અરબી તફસીરો:
وَيُرِيكُمۡ ءَايَٰتِهِۦ فَأَيَّ ءَايَٰتِ ٱللَّهِ تُنكِرُونَ
81. ተዓምራትንም ያሳያችኋል:: ታዲያ ከአላህ ተዓምራት መካከል የትኛውን ትክዳላችሁ?
અરબી તફસીરો:
أَفَلَمۡ يَسِيرُواْ فِي ٱلۡأَرۡضِ فَيَنظُرُواْ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلَّذِينَ مِن قَبۡلِهِمۡۚ كَانُوٓاْ أَكۡثَرَ مِنۡهُمۡ وَأَشَدَّ قُوَّةٗ وَءَاثَارٗا فِي ٱلۡأَرۡضِ فَمَآ أَغۡنَىٰ عَنۡهُم مَّا كَانُواْ يَكۡسِبُونَ
82. የእነዚያም ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ህዝቦች ፍፃሜ እንዴት እንደነበር ይመለከቱ ዘንድ በምድር ላይ አይሄዱምን ? ከእነርሱ ይበልጥ ብዙዎች በኃይልና በምድር ላይ በተዋቸው ምልክቶችም በጣም ብርቱዎች ነበሩ:: ያም ይሰሩት የነበሩት ለእነርሱ ምንም አልጠቀማቸዉም::
અરબી તફસીરો:
فَلَمَّا جَآءَتۡهُمۡ رُسُلُهُم بِٱلۡبَيِّنَٰتِ فَرِحُواْ بِمَا عِندَهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِ وَحَاقَ بِهِم مَّا كَانُواْ بِهِۦ يَسۡتَهۡزِءُونَ
83. መልዕክተኞቻቸዉም ተዓምራትን ባመጡላችሁ ጊዜ እነርሱ ዘንድ ባለው ዕውቀት ተደሰቱ:: በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ቅጣትም በእነርሱ ላይ ሰፈረባቸው::
અરબી તફસીરો:
فَلَمَّا رَأَوۡاْ بَأۡسَنَا قَالُوٓاْ ءَامَنَّا بِٱللَّهِ وَحۡدَهُۥ وَكَفَرۡنَا بِمَا كُنَّا بِهِۦ مُشۡرِكِينَ
84. ብርቱ ቅጣታችንንም ባዩ ጊዜ «በአላህ አንድነት አምነናል በእርሱም እናጋራ በነበርነው ጣዖታት ክደናል» አሉ::
અરબી તફસીરો:
فَلَمۡ يَكُ يَنفَعُهُمۡ إِيمَٰنُهُمۡ لَمَّا رَأَوۡاْ بَأۡسَنَاۖ سُنَّتَ ٱللَّهِ ٱلَّتِي قَدۡ خَلَتۡ فِي عِبَادِهِۦۖ وَخَسِرَ هُنَالِكَ ٱلۡكَٰفِرُونَ
85. ብርቱ ቅጣታችንን ባዩ ጊዜ ማመናቸዉም የሚጠቅማቸው አልነበረም:: የአላህን ደንብ ያችን በባሮቹ ውስጥ ያለፈችውን ተጠንቀቁ:: በዚያ ጊዜም ከሓዲያን ከሰሩ::
અરબી તફસીરો:
 
શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: ગાફિર
સૂરહ માટે અનુક્રમણિકા પેજ નંબર
 
કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - એમ્હારિક ભાષામાં અનુવાદ - આફ્રિકન એકેડમી - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા

તેનું અનુવાદ મુહમ્મદ ઝૈન ઝહરુદ્ દીન દ્વારા કરવામાં આવ્યું. આફ્રિકા એકેડમી દ્વારા પ્રકાશિત.

બંધ કરો