Check out the new design

કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - એમ્હારિક ભાષામાં અનુવાદ - આફ્રિકન એકેડમી * - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા


શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: મુહમ્મદ   આયત:
وَلَوۡ نَشَآءُ لَأَرَيۡنَٰكَهُمۡ فَلَعَرَفۡتَهُم بِسِيمَٰهُمۡۚ وَلَتَعۡرِفَنَّهُمۡ فِي لَحۡنِ ٱلۡقَوۡلِۚ وَٱللَّهُ يَعۡلَمُ أَعۡمَٰلَكُمۡ
30. (ሙሐመድ ሆይ!) ብንፈልግ ኖሮ እነርሱን ባሳየንህና በምልክታቸዉም በእርግጥ ባወቅካቸው ነበር:: ንግግርንም በማሸሞራቸው በእርግጥ ታውቃቸዋለህ:: አላህም ስራዎቻችሁን ሁሉ ያውቃልና::
અરબી તફસીરો:
وَلَنَبۡلُوَنَّكُمۡ حَتَّىٰ نَعۡلَمَ ٱلۡمُجَٰهِدِينَ مِنكُمۡ وَٱلصَّٰبِرِينَ وَنَبۡلُوَاْ أَخۡبَارَكُمۡ
31. (አማኞች ሆይ!) ከናንተ መካከል ተዋጊዎችንና ታጋሾቹን እስከምንገልጽ ድረስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን:: ወሬዎቻችሁንም (እስከምንገልጽ ድረስ) እንሞክራችኋለን::
અરબી તફસીરો:
إِنَّ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ وَصَدُّواْ عَن سَبِيلِ ٱللَّهِ وَشَآقُّواْ ٱلرَّسُولَ مِنۢ بَعۡدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُمُ ٱلۡهُدَىٰ لَن يَضُرُّواْ ٱللَّهَ شَيۡـٔٗا وَسَيُحۡبِطُ أَعۡمَٰلَهُمۡ
32. እነዚያ የካዱና ከአላህም መንገድ ሰዎችን ያገዱ ለእነርሱም ቅኑ መንገድ ከተገለጸላቸው በኋላ መልዕክተኛውን የተከራከሩ ሁሉ አላህን በምንም አይጎዱትም:: ስራዎቻቸውንም በእርግጥ ያበላሻል::
અરબી તફસીરો:
۞ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ أَطِيعُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُواْ ٱلرَّسُولَ وَلَا تُبۡطِلُوٓاْ أَعۡمَٰلَكُمۡ
33. እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገዙ:: መልዕክተኛውንም ታዘዙ:: ስራዎቻችሁንም አታበላሹ::
અરબી તફસીરો:
إِنَّ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ وَصَدُّواْ عَن سَبِيلِ ٱللَّهِ ثُمَّ مَاتُواْ وَهُمۡ كُفَّارٞ فَلَن يَغۡفِرَ ٱللَّهُ لَهُمۡ
34. እነዚያ የካዱ ከአላህ መንገድ ሌሎችን ያገዱና ከዚያም እነርሱ ከሓዲያን ሆነው የሞቱ አላህ ለእነርሱ በፍጹም አይምርም::
અરબી તફસીરો:
فَلَا تَهِنُواْ وَتَدۡعُوٓاْ إِلَى ٱلسَّلۡمِ وَأَنتُمُ ٱلۡأَعۡلَوۡنَ وَٱللَّهُ مَعَكُمۡ وَلَن يَتِرَكُمۡ أَعۡمَٰلَكُمۡ
35. እናንተ አሸናፊዎች ስትሆኑና አላህም ከናንተ ጋር ሲሆን አትድከሙ:: ወደ እርቅም አትጥሩ:: ስራዎቻችሁን ፈጽሞ አያጎድልባችሁም::
અરબી તફસીરો:
إِنَّمَا ٱلۡحَيَوٰةُ ٱلدُّنۡيَا لَعِبٞ وَلَهۡوٞۚ وَإِن تُؤۡمِنُواْ وَتَتَّقُواْ يُؤۡتِكُمۡ أُجُورَكُمۡ وَلَا يَسۡـَٔلۡكُمۡ أَمۡوَٰلَكُمۡ
36. ቅርቢቱ ሕይወት ጫወታና ዛዛታ ብቻ ናት:: ብታምኑና ቅጣቱንም ብትጠነቀቁ ምንዳዎቻችሁን ይሰጣችኋል:: ገንዘቦቻችሁንም ሁሉ አይጠይቃችሁም::
અરબી તફસીરો:
إِن يَسۡـَٔلۡكُمُوهَا فَيُحۡفِكُمۡ تَبۡخَلُواْ وَيُخۡرِجۡ أَضۡغَٰنَكُمۡ
37. እርሷን ቢጠይቃችሁና ችክ ቢልባችሁ ትሰስታላችሁ:: ቂሞቻችሁንም ያወጣል::
અરબી તફસીરો:
هَٰٓأَنتُمۡ هَٰٓؤُلَآءِ تُدۡعَوۡنَ لِتُنفِقُواْ فِي سَبِيلِ ٱللَّهِ فَمِنكُم مَّن يَبۡخَلُۖ وَمَن يَبۡخَلۡ فَإِنَّمَا يَبۡخَلُ عَن نَّفۡسِهِۦۚ وَٱللَّهُ ٱلۡغَنِيُّ وَأَنتُمُ ٱلۡفُقَرَآءُۚ وَإِن تَتَوَلَّوۡاْ يَسۡتَبۡدِلۡ قَوۡمًا غَيۡرَكُمۡ ثُمَّ لَا يَكُونُوٓاْ أَمۡثَٰلَكُم
38. (አማኞች ሆይ!) አስተውሉ:: እናንተ እነዚያ በአላህ መንገድ ትለግሱ ዘንድ የምትጠሩ ናችሁ:: ከናንተም መካከልም የሚሰስት ሰው አለ:: የሚሰስት ሰው ሁሉ የሚሰስተው በራሱ ላይ ብቻ ነው:: አላህ በራሱ ተብቃቂ ነውና:: እናንተ ግን ድሆች ናችሁ:: ብትሸሹም ሌሎችን ሀዝቦች በቦታችሁ ይለውጣል:: ከዚያም ባለመታዘዝ እንደናንተ ብጤዎቻችሁ አይሆኑም::
અરબી તફસીરો:
 
શબ્દોનું ભાષાંતર સૂરહ: મુહમ્મદ
સૂરહ માટે અનુક્રમણિકા પેજ નંબર
 
કુરઆન મજીદના શબ્દોનું ભાષાંતર - એમ્હારિક ભાષામાં અનુવાદ - આફ્રિકન એકેડમી - ભાષાંતરોની અનુક્રમણિકા

તેનું અનુવાદ મુહમ્મદ ઝૈન ઝહરુદ્ દીન દ્વારા કરવામાં આવ્યું. આફ્રિકા એકેડમી દ્વારા પ્રકાશિત.

બંધ કરો