क़ुरआन के अर्थों का अनुवाद - الترجمة الأمهرية - زين * - अनुवादों की सूची


अर्थों का अनुवाद सूरा: सूरा अल्-मुद्दस्सिर   आयत:

ሱረቱ አል ሙደሲር

يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡمُدَّثِّرُ
1. አንተ (ልብስ) ደራቢው ሆይ!
अरबी तफ़सीरें:
قُمۡ فَأَنذِرۡ
2. ተነሳና (ህዝቦችህን) አስጠንቅቅ።
अरबी तफ़सीरें:
وَرَبَّكَ فَكَبِّرۡ
3. ጌታህንም አክብር::
अरबी तफ़सीरें:
وَثِيَابَكَ فَطَهِّرۡ
4. ልብስህንም አጥራ::
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلرُّجۡزَ فَٱهۡجُرۡ
5. ጣዖትንም ራቅ::
अरबी तफ़सीरें:
وَلَا تَمۡنُن تَسۡتَكۡثِرُ
6. ማብዛትንም የምትፈልግ ሆነህ አትለግስ::
अरबी तफ़सीरें:
وَلِرَبِّكَ فَٱصۡبِرۡ
7. (ብዙ ዒባዳን ከመስራት አትድከም):: ለጌታህም (ትዕዘዛዝ) ታገስ።
अरबी तफ़सीरें:
فَإِذَا نُقِرَ فِي ٱلنَّاقُورِ
8. በቀንዱም በተነፋ ጊዜ፤
अरबी तफ़सीरें:
فَذَٰلِكَ يَوۡمَئِذٖ يَوۡمٌ عَسِيرٌ
9. ይህን ጊዜ ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው።
अरबी तफ़सीरें:
عَلَى ٱلۡكَٰفِرِينَ غَيۡرُ يَسِيرٖ
10. (በተለይ) በከሓዲያን ላይ ገር ያልሆነ ቀን ነው።
अरबी तफ़सीरें:
ذَرۡنِي وَمَنۡ خَلَقۡتُ وَحِيدٗا
11. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) በብቸኝነት ከፈጠርኩት ጋር ተወኝ።
अरबी तफ़सीरें:
وَجَعَلۡتُ لَهُۥ مَالٗا مَّمۡدُودٗا
12. ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በዓይነቱ) አደረግኩለት።
अरबी तफ़सीरें:
وَبَنِينَ شُهُودٗا
13. በየአደባባዩ ተገኝ የሆኑ ወንዶች ልጆችንም ሰጠሁት።
अरबी तफ़सीरें:
وَمَهَّدتُّ لَهُۥ تَمۡهِيدٗا
14. ለእርሱም ኑሮውን መዘርጋትን ዘረጋሁለት፤
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ يَطۡمَعُ أَنۡ أَزِيدَ
15. ከዚያ ልጨምርለት ይከጅላል::
अरबी तफ़सीरें:
كَلَّآۖ إِنَّهُۥ كَانَ لِأٓيَٰتِنَا عَنِيدٗا
16. ሰው ይከልከል! እርሱ ለአናቅጻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበርና።
अरबी तफ़सीरें:
سَأُرۡهِقُهُۥ صَعُودًا
17. በእርግጥ (ገሀነም ውስጥ) ችግርን አስገድደዋለሁ።
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّهُۥ فَكَّرَ وَقَدَّرَ
18. እርሱ (በቁርኣን ጉዳይ) አሰበ፤ ገመተም።
अरबी तफ़सीरें:
فَقُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
19. እናም ተረገመ:: እንዴት ገመተ!
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ قُتِلَ كَيۡفَ قَدَّرَ
20. ከዚያ ተረገመ። እንዴትስ ገመተ!
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ نَظَرَ
21. ከዚያም እንደገና (በቁርኣን ጉዳይ) ተመለከተ።
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ عَبَسَ وَبَسَرَ
22. ከዚያ ፊቱን አጨፈገገ አኮማተረም::
अरबी तफ़सीरें:
ثُمَّ أَدۡبَرَ وَٱسۡتَكۡبَرَ
23. ከዚያ (በአላህ ከማመን) ዞረ:: ኮራም::
अरबी तफ़सीरें:
فَقَالَ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ يُؤۡثَرُ
24. «ይህ ከሌላ (ሰው) የሚቀዳ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም።
अरबी तफ़सीरें:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا قَوۡلُ ٱلۡبَشَرِ
25. «ይህ የሰው ቃል እንጂ ሌላ አይደለም» አለ::
अरबी तफ़सीरें:
سَأُصۡلِيهِ سَقَرَ
26. ሰቀር (በተባለ የገሀነም ዋሻ ውስጥ) በእርግጥ አስገባዋለሁ::
अरबी तफ़सीरें:
وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سَقَرُ
27. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ሰቀር ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?
अरबी तफ़सीरें:
لَا تُبۡقِي وَلَا تَذَرُ
28. (ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም:: አትተዉምም::
अरबी तफ़सीरें:
لَوَّاحَةٞ لِّلۡبَشَرِ
29. የሰዎችን ቆዳ በጣም አክሳይ ናት።
अरबी तफ़सीरें:
عَلَيۡهَا تِسۡعَةَ عَشَرَ
30. በእርሷም ላይ አስራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት::
अरबी तफ़सीरें:
وَمَا جَعَلۡنَآ أَصۡحَٰبَ ٱلنَّارِ إِلَّا مَلَٰٓئِكَةٗۖ وَمَا جَعَلۡنَا عِدَّتَهُمۡ إِلَّا فِتۡنَةٗ لِّلَّذِينَ كَفَرُواْ لِيَسۡتَيۡقِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَيَزۡدَادَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓاْ إِيمَٰنٗا وَلَا يَرۡتَابَ ٱلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَ وَلِيَقُولَ ٱلَّذِينَ فِي قُلُوبِهِم مَّرَضٞ وَٱلۡكَٰفِرُونَ مَاذَآ أَرَادَ ٱللَّهُ بِهَٰذَا مَثَلٗاۚ كَذَٰلِكَ يُضِلُّ ٱللَّهُ مَن يَشَآءُ وَيَهۡدِي مَن يَشَآءُۚ وَمَا يَعۡلَمُ جُنُودَ رَبِّكَ إِلَّا هُوَۚ وَمَا هِيَ إِلَّا ذِكۡرَىٰ لِلۡبَشَرِ
31. የእሳትን ዘበኞች መላዕክት እንጂ ሌላ አላደረግንም:: ቁጥራቸውንም ለእነዚያ በአላህ ለካዱት ሰዎች መፈተኛ እንጂ ለሌላ አላደረግንም:: እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች እንዲያረጋግጡ፤ እነዚያም በትክክል ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፤ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምዕመናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፤ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አስመሳዮችና ከሓዲያን «አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል?» እንዲሉ እንጂ (አላደረግንም):: ልክ እንደዚሁ አላህ የሚፈልገውን ያጠማል:: የሚፈልገውንም ያቀናል:: (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የጌታህንም ሰራዊት ልክ ከእርሱ በስተቀር ማንም አያውቅም:: የሰቀር እሳት ለሰዎች መገሰጫ እንጂ ሌላ አይደለም::
अरबी तफ़सीरें:
كَلَّا وَٱلۡقَمَرِ
32. (ከክህደት) ይከልከሉ:: በጨረቃ (እምላለሁ)፤
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلَّيۡلِ إِذۡ أَدۡبَرَ
33. በሌሊቱም በሄደ ጊዜ፤
अरबी तफ़सीरें:
وَٱلصُّبۡحِ إِذَآ أَسۡفَرَ
34. በንጋቱም ባበራ ጊዜ እምላለሁ።
अरबी तफ़सीरें:
إِنَّهَا لَإِحۡدَى ٱلۡكُبَرِ
35. (ሰቀር) ከታላላቆች አደጋዎች አንዱ፤
अरबी तफ़सीरें:
نَذِيرٗا لِّلۡبَشَرِ
36. ለሰዎች አስፈራሪ ናት።
अरबी तफ़सीरें:
لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَتَقَدَّمَ أَوۡ يَتَأَخَّرَ
37. ከናንተ መካከል ወደ በጎ ነገር መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለፈለገ (ሰው) ሁሉ፤
अरबी तफ़सीरें:
كُلُّ نَفۡسِۭ بِمَا كَسَبَتۡ رَهِينَةٌ
38. ነፍስ ሁሉ በሰራችው ስራ ተያዥ ናት::
अरबी तफ़सीरें:
إِلَّآ أَصۡحَٰبَ ٱلۡيَمِينِ
39. እነዚያ መዝገባቸውን በቀኝ እጃቸው የሚሰጡት ብቻ ሲቀሩ::
अरबी तफ़सीरें:
فِي جَنَّٰتٖ يَتَسَآءَلُونَ
40. (እነርሱማ) በገነቶች ውስጥ ሁነው እርስ በራሳቸው ይጠያየቃሉ::
अरबी तफ़सीरें:
عَنِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
41. ከአመጸኞች ሁኔታ (ይጠያየቃሉ)
अरबी तफ़सीरें:
مَا سَلَكَكُمۡ فِي سَقَرَ
42. (ከዚያ ለእነርሱ እንዲህ ይሏቸዋል።) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
अरबी तफ़सीरें:
قَالُواْ لَمۡ نَكُ مِنَ ٱلۡمُصَلِّينَ
43. «ከሰጋጆች አልነበርንም።
अरबी तफ़सीरें:
وَلَمۡ نَكُ نُطۡعِمُ ٱلۡمِسۡكِينَ
44. «ለድሆችም የምናበላም አልነበርንም።
अरबी तफ़सीरें:
وَكُنَّا نَخُوضُ مَعَ ٱلۡخَآئِضِينَ
45. «ከዘባራቂዎችም ጋር እንዘባርቅ ነበር።
अरबी तफ़सीरें:
وَكُنَّا نُكَذِّبُ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
46. «በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበር፤
अरबी तफ़सीरें:
حَتَّىٰٓ أَتَىٰنَا ٱلۡيَقِينُ
47. «እርግጠኛው ነገር ሞት እስከመጣብን ድረስ።» ይላሉ
अरबी तफ़सीरें:
فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ
48. እናም በዚያ ቀን የአማላጆች (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።
अरबी तफ़सीरें:
فَمَا لَهُمۡ عَنِ ٱلتَّذۡكِرَةِ مُعۡرِضِينَ
49. ከ(ቁርኣን) ከግሳጼም የሚያፈገፍጉበት ምን ምክኒያት አላቸው?
अरबी तफ़सीरें:
كَأَنَّهُمۡ حُمُرٞ مُّسۡتَنفِرَةٞ
50. እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዩች ይመስላሉ::
अरबी तफ़सीरें:
فَرَّتۡ مِن قَسۡوَرَةِۭ
51. ከአንበሳ የሸሹ
अरबी तफ़सीरें:
بَلۡ يُرِيدُ كُلُّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ أَن يُؤۡتَىٰ صُحُفٗا مُّنَشَّرَةٗ
52. ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለእያንዳንዱ ሰው የተዘረጉ ጹሑፎችን በእጁ እንዲሰጥ ይፈልጋል::
अरबी तफ़सीरें:
كَلَّاۖ بَل لَّا يَخَافُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
53. ከዚህ መሰል ተግባራቸው ይከልከሉ:: ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም ቅጣት አይፈሩም::
अरबी तफ़सीरें:
كَلَّآ إِنَّهُۥ تَذۡكِرَةٞ
54. ይከልከሉ፤እርሱ(ቁርአን) መገሰጫ ነው።
अरबी तफ़सीरें:
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
55. ስለዚህ የፈለገ ሰው ቁርኣንን ይገሰጽበታል::
अरबी तफ़सीरें:
وَمَا يَذۡكُرُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُۚ هُوَ أَهۡلُ ٱلتَّقۡوَىٰ وَأَهۡلُ ٱلۡمَغۡفِرَةِ
56. ሆኖም (ሰዎች) አላህ ካልፈለገ በስተቀር አይገሰጹም:: አላህ የመፈራት ባለቤት ነው:: (ለፈሩትም) የምህረት ባለቤት ነው::
अरबी तफ़सीरें:
 
अर्थों का अनुवाद सूरा: सूरा अल्-मुद्दस्सिर
सूरों की सूची पृष्ठ संख्या
 
क़ुरआन के अर्थों का अनुवाद - الترجمة الأمهرية - زين - अनुवादों की सूची

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

बंद करें