وه‌رگێڕانی ماناكانی قورئانی پیرۆز - وەرگێڕاوی ئەمهەری - زەین * - پێڕستی وه‌رگێڕاوه‌كان


وه‌رگێڕانی ماناكان سوره‌تی: سورەتی النجم   ئایه‌تی:

ሱረቱ አን ነጅም

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ
1. በኮከብ እምላለሁ በገባ ጊዜ፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ
2. (እናንተ የመካ ሰዎች ሆይ)፤ ባልደረባችሁ ሙሐመድ ከሐቅ አልተሳሳተም። አላፈነገጠም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ
3. ከልብ ወለድ ስሜቱም አይናገርም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ
4. እርሱ (ንግግሩ) ከአላህ የተወረደ እንጂ ሌላ አይደለም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ
5. ሀይለ ብርቱ የሆነው አስተማረው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ
6. የእውቀት ባለቤት የሆነው:: ከዚያም ላይ ሆኖ ተመቻቸ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
7. በላይኛው አድማስ ላይ ሆኖ፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
8. ከዚያም (ነቢዩን) ቀረበው፤ በጣም ተጠጋውም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ
9. ከዚያም የሁለት ደጋን ጫፎች ያህል ወይም ከዚያም ባነሰ ርቀት ላይ ሆነም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ
10. እናም (አላህ) ለአገልጋዩ (ለሙሐመድ) ማውረድ የሻውን አወረደ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
11. ያየውን ነገር ሁሉ ልቦናው አላስተባበለዉም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
12. ታዲያ (ከሓዲያን ሆይ!) በሚያየው ጉዳይ ላይ ትከራከሩታላችሁን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ
13. እርግጥ በሌላይቱም መውረድ (ነቢዩ ሙሐመድ መልዐኩ ጂብሪልን) አይቶታል::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ
14. ይኸዉም ሲድረቱ አል-ሙንተሃ (የመጨረሻቱ ቁርቁራ) በተባለው ዓለም ላይ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ
15. እርሷ ዘንድ መኖርያ የሆነችው ገነት አለች::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ
16. (ቁርቁራይቱን) ሸፋኝ ነገር በሸፈናት ጊዜ (አየው)።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
17. አይኑ አልተዘነበለም:: ወሰንም አላለፈም።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ
18. ከጌታው ታላላቅ ተዐምራት በእርግጥ ተመለከተ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ
19. (ቁርይሾች ሆይ!) ላትንና ዑዛን አያችሁን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ
20. ስለ ሶስተኛዋ መናትም የምታውቁትን እስቲ ንገሩኝ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ
21. ለእናንተ ወንድ ወንድ ለእሱ ግን ሴት ሴት ታደርጋላችሁን::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ
22. ይህ ተግባር አድሏዊ ክፍፍል ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ
23. እነዚያ ጣዖታት እናንተና አባቶቻችሁ የሰየማችኋቸው ስሞች ብቻ እንጂ ሌላ አይደሉም::አላህ በእርሷ (መገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ጣኡት አምላኪዎች ሁሉ ከጌታቸው የተላከላቸው ቅኑ መመሪያ እያለ የሚከተሉት ግን ጥርጣሬንና ስሜትን ብቻ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
24. የሰው ልጅ የፈለገውን ሁሉ ያገኛልን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ
25. መጪውን ዓለምም ሆነ የመጀመሪያው ዓለም የአላህ ብቻ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ
26. በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት አላህ የሚሻውንና የሚወደውን ለሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ
27. እነዚያ በመጪው ዓለም የማያምኑት መላዕክትን በእንስት ስም ይሰይማሉ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا
28. ለእነርሱም በእርሱ እውቀት የላቸውም። እነርሱ የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው:: ጥርጣሬ ደግሞ ሀቅን አይተካም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
29. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከቁርኣን አፈንግጦና የዚችን ዓለም ኑሮ እንጂ ሌላ ከማይመኝ ሰው እራስህን አሽሽ::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
30. ይህ የእውቀታቸው ጣሪያ (መጨረሻ) ነው:: ጌታህ ግን መንገዱን የሳተውን ሁሉ አዋቂ ነው:: የተቀናውንም እንዲሁ አዋቂ ነው።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى
31. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያን ያጠፉትን በተግባራቸው ለመመንዳትና እነዚያን መልካም የሰሩትንም በመልካሟ (በገነት) ሊመነዳ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
32. እነርሱም ከጥቃቅን ጥፋቶች በቀር ከባባድ ወንጀሎችንና አጸያፊ ተግባሮችን የራቁ ናቸው:: ጌታህ ምህረተ ሰፊ ነው:: እርሱ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜም ሆነ በእናቶቻችሁ ማሕጸን ውስጥ ጽንሶች በሁናችሁበት ጊዜ ያውቃችኋል:: ስለዚህ እራሳችሁን አታሞግሱ:: እርሱ በትክክል የሚፈራውን ሰው ከሁሉም ይበልጥ አዋቂ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ
33. ያን ከእምነት የሸሸውን አየህን (እስቲ ንገረኝ)?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ
34. ጥቂትን ብቻ ሰጥቶ ያቋረጠውን፤
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
35, ለመሆኑ የሚያውቀው የሩቅ ሚስጢር አለውና እርሱንም ያያልን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ
36. ወይስ በሙሳ ፅሁፍ ያለው አልተነገረውም?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ
37. በኢብራሂም (ትእዛዛቱን) በፈፀመው ያለውስ አልተነገረዉምን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ
38. ይኸዉም ወንጀለኛ ነፍስ የሌላውን ነፍስ ወንጀል በፍጹም አትሸከምም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
39. የሰው ልጅም የለፋበትን ብቻ እንጂ ሌላ የለዉም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ
40. የሰራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ
41. ከዚያም ጌታው ሙሉ ምንዳውን ይመነዳዋል::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ
42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሁሉም መጨረሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ
43. እርሱ ያ ያሳቀና ያስለቀሰ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا
44. እርሱ ያ የገደለና ሕያው ያደረገም ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ
45. እርሱ ያ ጥንድን፤ ወንድንና ሴትን የፈጠረ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ
46. ይኸዉም ከፍትወት ጠብታ በማሕጸን ውስጥ በምትፈሰስ ጊዜ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ
47. ሌላውን ማስገኘትም በእርሱ ላይ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ
48. እርሱ ያ ሀብትን የሰጠና ያብቃቃ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ
49. እርሱ የሺዕራ ጌታ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ
50. እርሱ የቀድሞ ሰዎችን የአድ ሕዝቦችንም አጠፋ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ
51. ሰሙድንም አጠፋ:: አንድንም አላስቀረም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ
52. በፊትም የኑህን ህዝቦች አጥፍቷል:: እነርሱ እጅግ በዳዮችና በጣም አመጸኞች ነበሩና ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ
53.የተገለበጡትንም ደፋ።
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
54. ባሸፈናት ሸፈናት::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
55. (የሰው ልጅ ሆይ)፤ ከጌታህ ጸጋዎች በየትኛው ነው የምትጠራጠረው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ
56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህ ከቀድሞዎቹ አስጠንቃቂዎች አንዱ ነው::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ
57. ቀራቢቱም ቀረበች::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
58. ከአላህ በስተቀር ገላጭ የላትም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ
59. በዚህ ዘገባ ትደነቃላችሁን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ
60 ትስቃላችሁን? አታለቅሱምን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ
61. እናንተ ዘወትር ዘንጊዎች ናችሁን?
تەفسیرە عەرەبیەکان:
فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩
62. ለአላህ ስገዱ በብቸኝነትም አምልኩትም::
تەفسیرە عەرەبیەکان:
 
وه‌رگێڕانی ماناكان سوره‌تی: سورەتی النجم
پێڕستی سوره‌ته‌كان ژمارەی پەڕە
 
وه‌رگێڕانی ماناكانی قورئانی پیرۆز - وەرگێڕاوی ئەمهەری - زەین - پێڕستی وه‌رگێڕاوه‌كان

وەرگێڕاوی ئەمهەری

داخستن