قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - الترجمة الأمهرية - زين * - ترجمے کی لسٹ


معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ نجم   آیت:

ሱረቱ አን ነጅም

وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ
1. በኮከብ እምላለሁ በገባ ጊዜ፤
عربی تفاسیر:
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ
2. (እናንተ የመካ ሰዎች ሆይ)፤ ባልደረባችሁ ሙሐመድ ከሐቅ አልተሳሳተም። አላፈነገጠም።
عربی تفاسیر:
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ
3. ከልብ ወለድ ስሜቱም አይናገርም::
عربی تفاسیر:
إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ
4. እርሱ (ንግግሩ) ከአላህ የተወረደ እንጂ ሌላ አይደለም።
عربی تفاسیر:
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ
5. ሀይለ ብርቱ የሆነው አስተማረው::
عربی تفاسیر:
ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ
6. የእውቀት ባለቤት የሆነው:: ከዚያም ላይ ሆኖ ተመቻቸ።
عربی تفاسیر:
وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
7. በላይኛው አድማስ ላይ ሆኖ፤
عربی تفاسیر:
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
8. ከዚያም (ነቢዩን) ቀረበው፤ በጣም ተጠጋውም።
عربی تفاسیر:
فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ
9. ከዚያም የሁለት ደጋን ጫፎች ያህል ወይም ከዚያም ባነሰ ርቀት ላይ ሆነም::
عربی تفاسیر:
فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ
10. እናም (አላህ) ለአገልጋዩ (ለሙሐመድ) ማውረድ የሻውን አወረደ::
عربی تفاسیر:
مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
11. ያየውን ነገር ሁሉ ልቦናው አላስተባበለዉም::
عربی تفاسیر:
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
12. ታዲያ (ከሓዲያን ሆይ!) በሚያየው ጉዳይ ላይ ትከራከሩታላችሁን?
عربی تفاسیر:
وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ
13. እርግጥ በሌላይቱም መውረድ (ነቢዩ ሙሐመድ መልዐኩ ጂብሪልን) አይቶታል::
عربی تفاسیر:
عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ
14. ይኸዉም ሲድረቱ አል-ሙንተሃ (የመጨረሻቱ ቁርቁራ) በተባለው ዓለም ላይ ነው::
عربی تفاسیر:
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ
15. እርሷ ዘንድ መኖርያ የሆነችው ገነት አለች::
عربی تفاسیر:
إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ
16. (ቁርቁራይቱን) ሸፋኝ ነገር በሸፈናት ጊዜ (አየው)።
عربی تفاسیر:
مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
17. አይኑ አልተዘነበለም:: ወሰንም አላለፈም።
عربی تفاسیر:
لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ
18. ከጌታው ታላላቅ ተዐምራት በእርግጥ ተመለከተ።
عربی تفاسیر:
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ
19. (ቁርይሾች ሆይ!) ላትንና ዑዛን አያችሁን?
عربی تفاسیر:
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ
20. ስለ ሶስተኛዋ መናትም የምታውቁትን እስቲ ንገሩኝ::
عربی تفاسیر:
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ
21. ለእናንተ ወንድ ወንድ ለእሱ ግን ሴት ሴት ታደርጋላችሁን::
عربی تفاسیر:
تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ
22. ይህ ተግባር አድሏዊ ክፍፍል ነው::
عربی تفاسیر:
إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ
23. እነዚያ ጣዖታት እናንተና አባቶቻችሁ የሰየማችኋቸው ስሞች ብቻ እንጂ ሌላ አይደሉም::አላህ በእርሷ (መገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ጣኡት አምላኪዎች ሁሉ ከጌታቸው የተላከላቸው ቅኑ መመሪያ እያለ የሚከተሉት ግን ጥርጣሬንና ስሜትን ብቻ ነው::
عربی تفاسیر:
أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
24. የሰው ልጅ የፈለገውን ሁሉ ያገኛልን?
عربی تفاسیر:
فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ
25. መጪውን ዓለምም ሆነ የመጀመሪያው ዓለም የአላህ ብቻ ነው::
عربی تفاسیر:
۞ وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ
26. በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት አላህ የሚሻውንና የሚወደውን ለሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::
عربی تفاسیر:
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ
27. እነዚያ በመጪው ዓለም የማያምኑት መላዕክትን በእንስት ስም ይሰይማሉ::
عربی تفاسیر:
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا
28. ለእነርሱም በእርሱ እውቀት የላቸውም። እነርሱ የሚከተሉት ጥርጣሬን ብቻ ነው:: ጥርጣሬ ደግሞ ሀቅን አይተካም::
عربی تفاسیر:
فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
29. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከቁርኣን አፈንግጦና የዚችን ዓለም ኑሮ እንጂ ሌላ ከማይመኝ ሰው እራስህን አሽሽ::
عربی تفاسیر:
ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
30. ይህ የእውቀታቸው ጣሪያ (መጨረሻ) ነው:: ጌታህ ግን መንገዱን የሳተውን ሁሉ አዋቂ ነው:: የተቀናውንም እንዲሁ አዋቂ ነው።
عربی تفاسیر:
وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى
31. በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የአላህ ነው:: እነዚያን ያጠፉትን በተግባራቸው ለመመንዳትና እነዚያን መልካም የሰሩትንም በመልካሟ (በገነት) ሊመነዳ ነው::
عربی تفاسیر:
ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
32. እነርሱም ከጥቃቅን ጥፋቶች በቀር ከባባድ ወንጀሎችንና አጸያፊ ተግባሮችን የራቁ ናቸው:: ጌታህ ምህረተ ሰፊ ነው:: እርሱ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜም ሆነ በእናቶቻችሁ ማሕጸን ውስጥ ጽንሶች በሁናችሁበት ጊዜ ያውቃችኋል:: ስለዚህ እራሳችሁን አታሞግሱ:: እርሱ በትክክል የሚፈራውን ሰው ከሁሉም ይበልጥ አዋቂ ነው::
عربی تفاسیر:
أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ
33. ያን ከእምነት የሸሸውን አየህን (እስቲ ንገረኝ)?
عربی تفاسیر:
وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ
34. ጥቂትን ብቻ ሰጥቶ ያቋረጠውን፤
عربی تفاسیر:
أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
35, ለመሆኑ የሚያውቀው የሩቅ ሚስጢር አለውና እርሱንም ያያልን?
عربی تفاسیر:
أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ
36. ወይስ በሙሳ ፅሁፍ ያለው አልተነገረውም?
عربی تفاسیر:
وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ
37. በኢብራሂም (ትእዛዛቱን) በፈፀመው ያለውስ አልተነገረዉምን?
عربی تفاسیر:
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ
38. ይኸዉም ወንጀለኛ ነፍስ የሌላውን ነፍስ ወንጀል በፍጹም አትሸከምም::
عربی تفاسیر:
وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
39. የሰው ልጅም የለፋበትን ብቻ እንጂ ሌላ የለዉም::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ
40. የሰራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል::
عربی تفاسیر:
ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ
41. ከዚያም ጌታው ሙሉ ምንዳውን ይመነዳዋል::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ
42. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሁሉም መጨረሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ
43. እርሱ ያ ያሳቀና ያስለቀሰ ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا
44. እርሱ ያ የገደለና ሕያው ያደረገም ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ
45. እርሱ ያ ጥንድን፤ ወንድንና ሴትን የፈጠረ ነው::
عربی تفاسیر:
مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ
46. ይኸዉም ከፍትወት ጠብታ በማሕጸን ውስጥ በምትፈሰስ ጊዜ ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ
47. ሌላውን ማስገኘትም በእርሱ ላይ ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ
48. እርሱ ያ ሀብትን የሰጠና ያብቃቃ ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ
49. እርሱ የሺዕራ ጌታ ነው::
عربی تفاسیر:
وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ
50. እርሱ የቀድሞ ሰዎችን የአድ ሕዝቦችንም አጠፋ።
عربی تفاسیر:
وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ
51. ሰሙድንም አጠፋ:: አንድንም አላስቀረም::
عربی تفاسیر:
وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ
52. በፊትም የኑህን ህዝቦች አጥፍቷል:: እነርሱ እጅግ በዳዮችና በጣም አመጸኞች ነበሩና ነው::
عربی تفاسیر:
وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ
53.የተገለበጡትንም ደፋ።
عربی تفاسیر:
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
54. ባሸፈናት ሸፈናት::
عربی تفاسیر:
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
55. (የሰው ልጅ ሆይ)፤ ከጌታህ ጸጋዎች በየትኛው ነው የምትጠራጠረው::
عربی تفاسیر:
هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ
56. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ይህ ከቀድሞዎቹ አስጠንቃቂዎች አንዱ ነው::
عربی تفاسیر:
أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ
57. ቀራቢቱም ቀረበች::
عربی تفاسیر:
لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
58. ከአላህ በስተቀር ገላጭ የላትም::
عربی تفاسیر:
أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ
59. በዚህ ዘገባ ትደነቃላችሁን?
عربی تفاسیر:
وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ
60 ትስቃላችሁን? አታለቅሱምን?
عربی تفاسیر:
وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ
61. እናንተ ዘወትር ዘንጊዎች ናችሁን?
عربی تفاسیر:
فَٱسۡجُدُواْۤ لِلَّهِۤ وَٱعۡبُدُواْ۩
62. ለአላህ ስገዱ በብቸኝነትም አምልኩትም::
عربی تفاسیر:
 
معانی کا ترجمہ سورت: سورۂ نجم
سورتوں کی لسٹ صفحہ نمبر
 
قرآن کریم کے معانی کا ترجمہ - الترجمة الأمهرية - زين - ترجمے کی لسٹ

ترجمة معاني القرآن الكريم إلى اللغة الأمهرية ترجمها محمد زين نهر الدين صادرة عن أكاديمية أفريقيا.

بند کریں