Vertaling van de betekenissen Edele Qur'an - Amharic vertaling * - Index van vertaling

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

Vertaling van de betekenissen Surah: Soerat Al-Qi'jaamah (De Resurrectie)   Vers:

ሱረቱ አል ቂያማህ

لَآ أُقۡسِمُ بِيَوۡمِ ٱلۡقِيَٰمَةِ
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلنَّفۡسِ ٱللَّوَّامَةِ
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَلَّن نَّجۡمَعَ عِظَامَهُۥ
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን?
Arabische uitleg van de Qur'an:
بَلَىٰ قَٰدِرِينَ عَلَىٰٓ أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُۥ
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
بَلۡ يُرِيدُ ٱلۡإِنسَٰنُ لِيَفۡجُرَ أَمَامَهُۥ
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
يَسۡـَٔلُ أَيَّانَ يَوۡمُ ٱلۡقِيَٰمَةِ
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
فَإِذَا بَرِقَ ٱلۡبَصَرُ
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَخَسَفَ ٱلۡقَمَرُ
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَجُمِعَ ٱلشَّمۡسُ وَٱلۡقَمَرُ
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
يَقُولُ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذٍ أَيۡنَ ٱلۡمَفَرُّ
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
كَلَّا لَا وَزَرَ
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمُسۡتَقَرُّ
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
يُنَبَّؤُاْ ٱلۡإِنسَٰنُ يَوۡمَئِذِۭ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
بَلِ ٱلۡإِنسَٰنُ عَلَىٰ نَفۡسِهِۦ بَصِيرَةٞ
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَلَوۡ أَلۡقَىٰ مَعَاذِيرَهُۥ
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
لَا تُحَرِّكۡ بِهِۦ لِسَانَكَ لِتَعۡجَلَ بِهِۦٓ
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
إِنَّ عَلَيۡنَا جَمۡعَهُۥ وَقُرۡءَانَهُۥ
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
فَإِذَا قَرَأۡنَٰهُ فَٱتَّبِعۡ قُرۡءَانَهُۥ
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
ثُمَّ إِنَّ عَلَيۡنَا بَيَانَهُۥ
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
كَلَّا بَلۡ تُحِبُّونَ ٱلۡعَاجِلَةَ
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَتَذَرُونَ ٱلۡأٓخِرَةَ
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ نَّاضِرَةٌ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٞ
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذِۭ بَاسِرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
تَظُنُّ أَن يُفۡعَلَ بِهَا فَاقِرَةٞ
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
كَلَّآ إِذَا بَلَغَتِ ٱلتَّرَاقِيَ
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَقِيلَ مَنۡۜ رَاقٖ
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَظَنَّ أَنَّهُ ٱلۡفِرَاقُ
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَٱلۡتَفَّتِ ٱلسَّاقُ بِٱلسَّاقِ
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
إِلَىٰ رَبِّكَ يَوۡمَئِذٍ ٱلۡمَسَاقُ
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ ነው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّىٰ
አላመነምም አልሰገደምም፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
وَلَٰكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِۦ يَتَمَطَّىٰٓ
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰ
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
ثُمَّ أَوۡلَىٰ لَكَ فَأَوۡلَىٰٓ
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
أَيَحۡسَبُ ٱلۡإِنسَٰنُ أَن يُتۡرَكَ سُدًى
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?
Arabische uitleg van de Qur'an:
أَلَمۡ يَكُ نُطۡفَةٗ مِّن مَّنِيّٖ يُمۡنَىٰ
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?
Arabische uitleg van de Qur'an:
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةٗ فَخَلَقَ فَسَوَّىٰ
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
فَجَعَلَ مِنۡهُ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡
Arabische uitleg van de Qur'an:
أَلَيۡسَ ذَٰلِكَ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحۡـِۧيَ ٱلۡمَوۡتَىٰ
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?
Arabische uitleg van de Qur'an:
 
Vertaling van de betekenissen Surah: Soerat Al-Qi'jaamah (De Resurrectie)
Surah's Index Pagina nummer
 
Vertaling van de betekenissen Edele Qur'an - Amharic vertaling - Index van vertaling

De vertaling van de betekenissen van de Heilige Koran naar het Azerbeidzjaans, vertaald door Ali Khan Musayev. Het is gecorrigeerd onder toezicht van het Pioneers Translation Center en de originele vertaling is beschikbaar voor consultatie met als doel feedback, evaluatie en continue ontwikkeling.

Sluit