அல்குர்ஆன் மொழிபெயர்ப்பு - அம்ஹாரிக் மொழிபெயர்ப்பு * - மொழிபெயர்ப்பு அட்டவணை

XML CSV Excel API
Please review the Terms and Policies

மொழிபெயர்ப்பு அத்தியாயம்: ஸூரா அஷ்ஷுஅரா   வசனம்:

ሱረቱ አሽ ሹዐራእ

طسٓمٓ
ጧ ሲን ሚም
அரபு விரிவுரைகள்:
تِلۡكَ ءَايَٰتُ ٱلۡكِتَٰبِ ٱلۡمُبِينِ
ይህች ግልጽ ከኾነው መጽሐፍ አንቀጾች ናት፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
لَعَلَّكَ بَٰخِعٞ نَّفۡسَكَ أَلَّا يَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
አማኞች ባለመኾናቸው፤ (በቁጭት) ነፍስህን ገዳይ መኾን ይፈራልሃል፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِن نَّشَأۡ نُنَزِّلۡ عَلَيۡهِم مِّنَ ٱلسَّمَآءِ ءَايَةٗ فَظَلَّتۡ أَعۡنَٰقُهُمۡ لَهَا خَٰضِعِينَ
ብንሻ በእነሱ ላይ ከሰማይ ተዓምረን እናወርድና አንገቶቻቸው (መሪዎቻቸው) ለእርሷ ተዋራጆች ይኾናሉ።
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَا يَأۡتِيهِم مِّن ذِكۡرٖ مِّنَ ٱلرَّحۡمَٰنِ مُحۡدَثٍ إِلَّا كَانُواْ عَنۡهُ مُعۡرِضِينَ
ከአልረሕማንም ዘንድ ኣዲስ የተወረደ ቁርኣን አይመጣላቸውም፤ ከእርሱ የሚሸሹ ቢኾኑ እንጂ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَقَدۡ كَذَّبُواْ فَسَيَأۡتِيهِمۡ أَنۢبَٰٓؤُاْ مَا كَانُواْ بِهِۦ يَسۡتَهۡزِءُونَ
በእርግጥም አስተባበሉ፡፡ የዚያም በእርሱ ይሳለቁበት የነበሩት ወሬዎች (ፍጻሜ) ይመጣባቸዋል፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَوَلَمۡ يَرَوۡاْ إِلَى ٱلۡأَرۡضِ كَمۡ أَنۢبَتۡنَا فِيهَا مِن كُلِّ زَوۡجٖ كَرِيمٍ
ወደ ምድርም በውስጧ ከመልካም (በቃይ) ጎሳ ሁሉ ብዙን እንዳበቀልን አላዩምን?፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ አስደናቂ ምልክት አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊ አዛኝ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِذۡ نَادَىٰ رَبُّكَ مُوسَىٰٓ أَنِ ٱئۡتِ ٱلۡقَوۡمَ ٱلظَّٰلِمِينَ
ጌታህም ሙሳን «ወደ በደለኞቹ ሕዝቦች ኺድ» በማለት በጠራው ጊዜ (አስታውስ)፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَوۡمَ فِرۡعَوۡنَۚ أَلَا يَتَّقُونَ
«ወደ ፈርዖን ሕዝቦች (ኺድ) አላህን አይፈሩምን» (አለው)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ رَبِّ إِنِّيٓ أَخَافُ أَن يُكَذِّبُونِ
(ሙሳም) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ሊያስተባብሉኝ እፈራለሁ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَيَضِيقُ صَدۡرِي وَلَا يَنطَلِقُ لِسَانِي فَأَرۡسِلۡ إِلَىٰ هَٰرُونَ
«ልቤም ይጠብባል፡፡ ምላሴም አይፈታም፡፡ ስለዚህ ወደ ሃሩን ላክ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَهُمۡ عَلَيَّ ذَنۢبٞ فَأَخَافُ أَن يَقۡتُلُونِ
«ለእነርሱም በእኔ ላይ (የደም) ወንጀል አልለ፡፡ ስለዚህ እንዳይገድሉኝ እፈራለሁ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ كَلَّاۖ فَٱذۡهَبَا بِـَٔايَٰتِنَآۖ إِنَّا مَعَكُم مُّسۡتَمِعُونَ
(አላህ) አለ «ተው! (አይነኩህም)፡፡ በተዓምራቶቻችንም ኺዱ፡፡ እኛ ከእናንተ ጋር ሰሚዎች ነንና፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأۡتِيَا فِرۡعَوۡنَ فَقُولَآ إِنَّا رَسُولُ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«ወደ ፈርዖንም ኺዱ፡፡ በሉትም፡- እኛ የዓለማት ጌታ መልክተኞች ነን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَنۡ أَرۡسِلۡ مَعَنَا بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
«የእስራኤልን ልጆች ከእኛ ጋር ልቀቅ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ أَلَمۡ نُرَبِّكَ فِينَا وَلِيدٗا وَلَبِثۡتَ فِينَا مِنۡ عُمُرِكَ سِنِينَ
(ፈርዖንም) አለ «ልጅ ኾነህ በእኛ ውስጥ አላሳደግንህምን? በእኛ ውስጥም ከዕድሜህ ብዙ ዓመታትን አልተቀመጥክምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
وَفَعَلۡتَ فَعۡلَتَكَ ٱلَّتِي فَعَلۡتَ وَأَنتَ مِنَ ٱلۡكَٰفِرِينَ
«ያችንም የሠራሃትን ሥራህን አልሠራህምን? አንተም ከውለታ ቢሶቹ ነህ» (አለ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ فَعَلۡتُهَآ إِذٗا وَأَنَا۠ مِنَ ٱلضَّآلِّينَ
(ሙሳም) አለ «ያን ጊዜ እኔም ከተሳሳቱት ኾኜ ሠራኋት፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَفَرَرۡتُ مِنكُمۡ لَمَّا خِفۡتُكُمۡ فَوَهَبَ لِي رَبِّي حُكۡمٗا وَجَعَلَنِي مِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
«በፈራኋችሁም ጊዜ ከእንናተ ሸሸሁ፡፡ ጌታየም ለእኔ ጥበብን ሰጠኝ፡፡ ከመልክተኞቹም አደረገኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَتِلۡكَ نِعۡمَةٞ تَمُنُّهَا عَلَيَّ أَنۡ عَبَّدتَّ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
«ይህችም የእስራኤልን ልጆች ባሪያ በማድረግህ በእኔ ላይ የምትመጻደቅባት ጸጋ ነት፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ فِرۡعَوۡنُ وَمَا رَبُّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ፈርዖን አለ «(ላከኝ የምትለው) የዓለማትም ጌታ ምንድነው?»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ رَبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَآۖ إِن كُنتُم مُّوقِنِينَ
(ሙሳ) «የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምታረጋግጡ ብትኾኑ (ነገሩ ይህ ነው)፤» አለው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ لِمَنۡ حَوۡلَهُۥٓ أَلَا تَسۡتَمِعُونَ
(ፈርዖንም) በዙሪያው ላሉት ሰዎች «አትሰሙምን?» አለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ رَبُّكُمۡ وَرَبُّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
(ሙሳ) «ጌታችሁና የመጀመሪያዎቹ አባቶቻችሁም ጌታ ነው» አለው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ إِنَّ رَسُولَكُمُ ٱلَّذِيٓ أُرۡسِلَ إِلَيۡكُمۡ لَمَجۡنُونٞ
(ፈርዖን) "ያ ወደናንተ የተላከው መልእክተኛችሁ በእርግጥ እብድ ነው" አለ።
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ رَبُّ ٱلۡمَشۡرِقِ وَٱلۡمَغۡرِبِ وَمَا بَيۡنَهُمَآۖ إِن كُنتُمۡ تَعۡقِلُونَ
(ሙሳ) «የምሥራቅና የምዕራብ በመካከላቸውም ያለው ነገር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ ታውቁ እንደኾናችሁ (እመኑበት)» አለው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ لَئِنِ ٱتَّخَذۡتَ إِلَٰهًا غَيۡرِي لَأَجۡعَلَنَّكَ مِنَ ٱلۡمَسۡجُونِينَ
(ፈርዖን) «ከእኔ ሌላ አምላክን ብትይዝ በውነቱ ከእስረኞቹ አደርግሃለሁ» አለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ أَوَلَوۡ جِئۡتُكَ بِشَيۡءٖ مُّبِينٖ
(ሙሳ) «በግልጽ አስረጅ ብመጣህም እንኳ?» አለው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ فَأۡتِ بِهِۦٓ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
«እንግዲያውስ ከእውነተኞች እንደኾንክ (አስረጁን) አምጣው» አለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَلۡقَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ ثُعۡبَانٞ مُّبِينٞ
በትሩንም ጣለ፡፡ እርሷም ወዲያውኑ ግልጽ እባብ ኾነች፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَنَزَعَ يَدَهُۥ فَإِذَا هِيَ بَيۡضَآءُ لِلنَّٰظِرِينَ
እጁንም አወጣ፡፡ ወዲያውም እርሷ ለተመልካቾች (የምታበራ) ነጭ ኾነች፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ لِلۡمَلَإِ حَوۡلَهُۥٓ إِنَّ هَٰذَا لَسَٰحِرٌ عَلِيمٞ
(ፈርዖን) በዙሪያው ላሉት መማክርት «ይህ በእርግጥ ዐዋቂ ድግምተኛ ነው» አለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
يُرِيدُ أَن يُخۡرِجَكُم مِّنۡ أَرۡضِكُم بِسِحۡرِهِۦ فَمَاذَا تَأۡمُرُونَ
«ከምድራችሁ በድግምቱ ሊያወጣችሁ ይፈልጋልና ምንን ታዛላችሁ?» (አላቸው)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُوٓاْ أَرۡجِهۡ وَأَخَاهُ وَٱبۡعَثۡ فِي ٱلۡمَدَآئِنِ حَٰشِرِينَ
አሉት «እርሱን ወንድሙንም አቆይና በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን ላክ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
يَأۡتُوكَ بِكُلِّ سَحَّارٍ عَلِيمٖ
«በጣም ዐዋቂ ድግምተኞችን ሁሉ ያመጡልሃልና፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
فَجُمِعَ ٱلسَّحَرَةُ لِمِيقَٰتِ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
ድግምተኞቹም በታወቀ ቀን ቀጠሮ ተሰበሰቡ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَقِيلَ لِلنَّاسِ هَلۡ أَنتُم مُّجۡتَمِعُونَ
ለሰዎቹም «እናንተ ተሰብስባችኋልን?» ተባለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
لَعَلَّنَا نَتَّبِعُ ٱلسَّحَرَةَ إِن كَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
«ድግምተኞቹን እነሱ አሸናፊዎች ቢኾኑ እንከተል ዘንድ» (ተባለ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَلَمَّا جَآءَ ٱلسَّحَرَةُ قَالُواْ لِفِرۡعَوۡنَ أَئِنَّ لَنَا لَأَجۡرًا إِن كُنَّا نَحۡنُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
«ድግምተኞቹም በመጡ ጊዜ ለፈርዖን እኛ አሸናፊዎች ብንሆን ለእኛ በእርግጥ ዋጋ አለን?» አሉት፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ نَعَمۡ وَإِنَّكُمۡ إِذٗا لَّمِنَ ٱلۡمُقَرَّبِينَ
«አዎን፤ እናንተም ያን ጊዜ ከባለሟሎቹ ትኾናላችሁ» አላቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ لَهُم مُّوسَىٰٓ أَلۡقُواْ مَآ أَنتُم مُّلۡقُونَ
ሙሳ «ለእነርሱ እናንተ የምትጥሉትን ጣሉ» አላቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَلۡقَوۡاْ حِبَالَهُمۡ وَعِصِيَّهُمۡ وَقَالُواْ بِعِزَّةِ فِرۡعَوۡنَ إِنَّا لَنَحۡنُ ٱلۡغَٰلِبُونَ
ገመዶቻቸውንና በትሮቻቸውንም ጣሉ፡፡ «በፈርዖንም ክብር ይኹንብን፡፡ እኛ በእርግጥ አሸናፊዎቹ እኛ ነን» አሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَلۡقَىٰ مُوسَىٰ عَصَاهُ فَإِذَا هِيَ تَلۡقَفُ مَا يَأۡفِكُونَ
ሙሳም በትሩን ጣለ፡፡ ወዲያውም እርሷ የሚያስመስሉትን ሁሉ ትውጣለች፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأُلۡقِيَ ٱلسَّحَرَةُ سَٰجِدِينَ
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُوٓاْ ءَامَنَّا بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
(እነሱም) አሉ «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
رَبِّ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ ءَامَنتُمۡ لَهُۥ قَبۡلَ أَنۡ ءَاذَنَ لَكُمۡۖ إِنَّهُۥ لَكَبِيرُكُمُ ٱلَّذِي عَلَّمَكُمُ ٱلسِّحۡرَ فَلَسَوۡفَ تَعۡلَمُونَۚ لَأُقَطِّعَنَّ أَيۡدِيَكُمۡ وَأَرۡجُلَكُم مِّنۡ خِلَٰفٖ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمۡ أَجۡمَعِينَ
(ፈርዖንም) «ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት ለእርሱ አመናችሁን? እርሱ ያ ድግምትን ያስተማራችሁ ታላቃችሁ ነው፡፡ ወደፊትም (የሚያገኛችሁን) በእርግጥ ታውቃላችሁ፡፡ እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን (ቀኝና ግራን) በማናጋት እቆረርጣለሁ፡፡ ሁላችሁንም እሰቅላችኋለሁም» አለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ لَا ضَيۡرَۖ إِنَّآ إِلَىٰ رَبِّنَا مُنقَلِبُونَ
(እነርሱም) አሉ «ጉዳት የለብንም፡፡ እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّا نَطۡمَعُ أَن يَغۡفِرَ لَنَا رَبُّنَا خَطَٰيَٰنَآ أَن كُنَّآ أَوَّلَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
«እኛ የምእምናን መጀመሪያ በመኾናችን ጌታችን ኀጢአቶቻችንን ለእኛ ሊምር እንከጅላለን፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
۞ وَأَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰ مُوسَىٰٓ أَنۡ أَسۡرِ بِعِبَادِيٓ إِنَّكُم مُّتَّبَعُونَ
ወደ ሙሳም «ባሮቼን ይዘህ ሌሊት ኺድ፡፡ እናንተ የሚከተሉዋችሁ ናችሁና» ስንል ላክን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَرۡسَلَ فِرۡعَوۡنُ فِي ٱلۡمَدَآئِنِ حَٰشِرِينَ
ፈርዖንም በየከተሞቹ ሰብሳቢዎችን (እንዲህ ሲል) ላከ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ هَٰٓؤُلَآءِ لَشِرۡذِمَةٞ قَلِيلُونَ
«እነዚህ ጥቂቶች ጭፈሮች ናቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّهُمۡ لَنَا لَغَآئِظُونَ
«እነርሱም ለእኛ አስቆጪዎች ናቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّا لَجَمِيعٌ حَٰذِرُونَ
«እኛም ብዙዎች ጥንቁቆች ነን፤» (አለ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَخۡرَجۡنَٰهُم مِّن جَنَّٰتٖ وَعُيُونٖ
አወጣናቸውም፡፡ ከአትክልቶችና ከምንጮች፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَكُنُوزٖ وَمَقَامٖ كَرِيمٖ
ከድልቦችም ከመልካም መቀመጫዎችም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَٰلِكَۖ وَأَوۡرَثۡنَٰهَا بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
እንደዚሁ ለእስራኤል ልጆች አወረስናትም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَتۡبَعُوهُم مُّشۡرِقِينَ
ፀሐይዋ ስትወጣም ተከተሉዋቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَلَمَّا تَرَٰٓءَا ٱلۡجَمۡعَانِ قَالَ أَصۡحَٰبُ مُوسَىٰٓ إِنَّا لَمُدۡرَكُونَ
ሁለቱ ጭፍሮችም በተያዩ ጊዜ የሙሳ ጓዶች «እኛ (የፈርዖን ሰዎች) የሚደርሱብን ነን» አሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ كَلَّآۖ إِنَّ مَعِيَ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَوۡحَيۡنَآ إِلَىٰ مُوسَىٰٓ أَنِ ٱضۡرِب بِّعَصَاكَ ٱلۡبَحۡرَۖ فَٱنفَلَقَ فَكَانَ كُلُّ فِرۡقٖ كَٱلطَّوۡدِ ٱلۡعَظِيمِ
ወደ ሙሳም «ባሕሩን በበትርህ ምታው» ስንል ላክንበት፡፡ (መታውና) ተከፈለም፡፡ ክፍሉም ሁሉ እንደ ታላቅ ጋራ ኾነ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَأَزۡلَفۡنَا ثَمَّ ٱلۡأٓخَرِينَ
እዚያም ዘንድ ሌሎችን አቀረብን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَأَنجَيۡنَا مُوسَىٰ وَمَن مَّعَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
ሙሳንም ከእርሱ ገር ያሉትንም ሰዎች ሁሉንም አዳን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ ታላቅ ታምር አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱتۡلُ عَلَيۡهِمۡ نَبَأَ إِبۡرَٰهِيمَ
በእነሱም (በሕዝቦችህ) ላይ የኢብራሂምን ወሬ አንብብላቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَا تَعۡبُدُونَ
ለአባቱና ለሕዝቦቹ «ምንን ትግገዛላችሁ» ባለ ጊዜ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ نَعۡبُدُ أَصۡنَامٗا فَنَظَلُّ لَهَا عَٰكِفِينَ
«ጣዖታትን እንገዛለን፤ እርሷንም በመገዛት ላይ እንቆያለን» አሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ هَلۡ يَسۡمَعُونَكُمۡ إِذۡ تَدۡعُونَ
(እርሱም) አለ «በጠራችኋቸው ጊዜ ይሰሟችኋልን?
அரபு விரிவுரைகள்:
أَوۡ يَنفَعُونَكُمۡ أَوۡ يَضُرُّونَ
«ወይስ ይጠቅሟችኋልን ወይስ ይጎዷችኋልን?»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ بَلۡ وَجَدۡنَآ ءَابَآءَنَا كَذَٰلِكَ يَفۡعَلُونَ
«የለም! አባቶቻችን እንደዚሁ ሲሠሩ አገኘን» አሉት፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ أَفَرَءَيۡتُم مَّا كُنتُمۡ تَعۡبُدُونَ
«ትግገዙት የነበራችሁትን አስተዋላችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُمُ ٱلۡأَقۡدَمُونَ
«እናንተም የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁም (የተግገዛችሁትን)፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
فَإِنَّهُمۡ عَدُوّٞ لِّيٓ إِلَّا رَبَّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«እነሱም (ጣዖቶቹ) ለእኔ ጠላቶች ናቸው፡፡ ግን የዓለማት ጌታ ሲቀር (እርሱ ወዳጄ ነው)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ٱلَّذِي خَلَقَنِي فَهُوَ يَهۡدِينِ
«(እርሱ) ያ የፈጠረኝ ነው፡፡ እርሱም ይመራኛል፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱلَّذِي هُوَ يُطۡعِمُنِي وَيَسۡقِينِ
«ያም እርሱ የሚያበላኝና የሚያጠጣኝ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِذَا مَرِضۡتُ فَهُوَ يَشۡفِينِ
«በታመምኩም ጊዜ እርሱ ያሽረኛል፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱلَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحۡيِينِ
«ያም የሚገድለኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱلَّذِيٓ أَطۡمَعُ أَن يَغۡفِرَ لِي خَطِيٓـَٔتِي يَوۡمَ ٱلدِّينِ
ያም በፍርዱ ቀን ኀጢአቴን ለእኔ ሊምር የምከጅለው ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
رَبِّ هَبۡ لِي حُكۡمٗا وَأَلۡحِقۡنِي بِٱلصَّٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትን ስጠኝ! በደጋጎቹም ሰዎች አስጠጋኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱجۡعَل لِّي لِسَانَ صِدۡقٖ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በኋለኞቹም ሕዝቦች ውስጥ ለእኔ መልካም ዝናን አድርግልኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱجۡعَلۡنِي مِن وَرَثَةِ جَنَّةِ ٱلنَّعِيمِ
የጸጋይቱን ገነት ከሚወርሱትም አድርገኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱغۡفِرۡ لِأَبِيٓ إِنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلضَّآلِّينَ
ለአባቴም ማር፡፡ እርሱ ከተሳሳቱት ነበረና፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَا تُخۡزِنِي يَوۡمَ يُبۡعَثُونَ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
يَوۡمَ لَا يَنفَعُ مَالٞ وَلَا بَنُونَ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِلَّا مَنۡ أَتَى ٱللَّهَ بِقَلۡبٖ سَلِيمٖ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
وَأُزۡلِفَتِ ٱلۡجَنَّةُ لِلۡمُتَّقِينَ
ገነትም ለፈሪዎች በምትቀረብበት (ቀን)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِلۡغَاوِينَ
ገሀነምም ለጠመሞች በምትገለጽበት (ቀን)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَقِيلَ لَهُمۡ أَيۡنَ مَا كُنتُمۡ تَعۡبُدُونَ
ለእነሱም በሚባል ቀን «ትግገዟቸው የነበራችሁት የት ናቸው»
அரபு விரிவுரைகள்:
مِن دُونِ ٱللَّهِ هَلۡ يَنصُرُونَكُمۡ أَوۡ يَنتَصِرُونَ
«ከአላህ ሌላ ሲኾኑ ይረዱዋችኋልን ወይስ (ለራሳቸው) ይርረዳሉን?»
அரபு விரிவுரைகள்:
فَكُبۡكِبُواْ فِيهَا هُمۡ وَٱلۡغَاوُۥنَ
በውስጧም እነሱና ጠማሞቹ በፊቶቻቸው ተጥለው ይንከባለላሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَجُنُودُ إِبۡلِيسَ أَجۡمَعُونَ
የሰይጣንም ሰራዊቶች መላውም (ይጣላሉ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ وَهُمۡ فِيهَا يَخۡتَصِمُونَ
እነርሱም በእርሷ ውስጥ የሚከራከሩ ኾነው ይላሉ፡-
அரபு விரிவுரைகள்:
تَٱللَّهِ إِن كُنَّا لَفِي ضَلَٰلٖ مُّبِينٍ
በአላህ እንምላለን፤ እኛ በግልጽ መሳሳት ውስጥ ነበርን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ نُسَوِّيكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
(ጣዖቶቹን) በዓለማት ጌታ ባስተካከልናችሁ ጊዜ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَضَلَّنَآ إِلَّا ٱلۡمُجۡرِمُونَ
አመጸኞቹም እንጅ ሌላ አላሳሳተንም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَمَا لَنَا مِن شَٰفِعِينَ
ከአማላጆችም ለእኛ ምንም የለንም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَا صَدِيقٍ حَمِيمٖ
አዛኝ ወዳጂም (የለንም)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَلَوۡ أَنَّ لَنَا كَرَّةٗ فَنَكُونَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ለእኛም አንዲት ጊዜ መመለስ በኖረችንና ከአማኞቹ በኾን እንመኛለን (ይላሉ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ግሳጼ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም አማኞች አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህ እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَّبَتۡ قَوۡمُ نُوحٍ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
የኑሕ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባበሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ኑሕ ለእነሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
۞ قَالُوٓاْ أَنُؤۡمِنُ لَكَ وَٱتَّبَعَكَ ٱلۡأَرۡذَلُونَ
(እነርሱም) «ወራዶቹ የተከተሉህ ኾነህ ለአንተ እናምናለን?» አሉት፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ وَمَا عِلۡمِي بِمَا كَانُواْ يَعۡمَلُونَ
(እርሱም) አላቸው «ይሠሩት በነበሩት ነገር ምን ዕውቀት አለኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنۡ حِسَابُهُمۡ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّيۖ لَوۡ تَشۡعُرُونَ
«ምርመራቸው በጌታዬ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡ ብታውቁ ኖሮ (ይህንን ትርረዱ ነበር)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَنَا۠ بِطَارِدِ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
«እኔም አማኞችን አባራሪ አይደለሁም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنۡ أَنَا۠ إِلَّا نَذِيرٞ مُّبِينٞ
«እኔ ግልጽ አስፈራሪ እንጅ ሌላ አይደለሁም፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ لَئِن لَّمۡ تَنتَهِ يَٰنُوحُ لَتَكُونَنَّ مِنَ ٱلۡمَرۡجُومِينَ
«ኑሕ ሆይ! (ከምትለው) ባትከለከል በእርግጥ ከሚወገሩት ትኾናለህ» አሉት፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ رَبِّ إِنَّ قَوۡمِي كَذَّبُونِ
(እርሱም) አለ «ጌታዬ ሆይ! ሕዝቦቼ አስተባበሉኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱفۡتَحۡ بَيۡنِي وَبَيۡنَهُمۡ فَتۡحٗا وَنَجِّنِي وَمَن مَّعِيَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
«በእኔና በእነርሱም መካከል (ተገቢ) ፍርድን ፍረድ፡፡ አድነኝም፡፡ ከእኔ ጋር ያሉትንም ምእምናን፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَنجَيۡنَٰهُ وَمَن مَّعَهُۥ فِي ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
እርሱንም ከእርሱ ጋር ያለውንም ሁሉ በተመላው መርከብ ውስጥ አዳን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا بَعۡدُ ٱلۡبَاقِينَ
ከዚያም በኋላ ቀሪዎቹን አሰጠምን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ ታላቅ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸው አማኞች አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَّبَتۡ عَادٌ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ዓድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ هُودٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ሁድ ለነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَتَبۡنُونَ بِكُلِّ رِيعٍ ءَايَةٗ تَعۡبَثُونَ
«የምትጫወቱ ኾናችሁ በከፍተኛ ስፍራ ሁሉ ላይ ምልክትን ትገነባላችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
وَتَتَّخِذُونَ مَصَانِعَ لَعَلَّكُمۡ تَخۡلُدُونَ
«የውሃ ማጠራቀሚያዎችንና ሕንፃዎችንም ዘላለም መኖርን የምትከጅሉ ኾናችሁ ትሠራላችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِذَا بَطَشۡتُم بَطَشۡتُمۡ جَبَّارِينَ
«በቀጣችሁም ጊዜ ጨካኞች ኾናችሁ ትቀጣላችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱتَّقُواْ ٱلَّذِيٓ أَمَدَّكُم بِمَا تَعۡلَمُونَ
«ያንንም በምታውቁት (ጸጋ) ያጣቀማችሁን ፍሩ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَمَدَّكُم بِأَنۡعَٰمٖ وَبَنِينَ
«በእንስሳዎችና በልጆች ያጣቀማችሁን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَجَنَّٰتٖ وَعُيُونٍ
«በአትክልቶችና በምንጮችም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنِّيٓ أَخَافُ عَلَيۡكُمۡ عَذَابَ يَوۡمٍ عَظِيمٖ
«እኔ በእናንተ ላይ የታላቅን ቀን ቅጣት እፈራለሁና፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ سَوَآءٌ عَلَيۡنَآ أَوَعَظۡتَ أَمۡ لَمۡ تَكُن مِّنَ ٱلۡوَٰعِظِينَ
(እነርሱም) አሉ «ብትገስጽም ወይም ከገሳጮቹ ባትኾንም በእኛ ላይ እኩል ነው፤ (ያለንበትን አንለቅም)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا خُلُقُ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ፀባይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
«እኛም የምንቅቀጣ አይደለንም» (አሉ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَكَذَّبُوهُ فَأَهۡلَكۡنَٰهُمۡۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
አስተባበሉትም፡፡ አጠፋናቸውም፡፡ በዚህም ውስጥ እርግጠኛ ግሳጼ አለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَّبَتۡ ثَمُودُ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ሰሙድ መልክተኞችን አስተባበለች፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ صَٰلِحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ሷሊህ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን ?
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَتُتۡرَكُونَ فِي مَا هَٰهُنَآ ءَامِنِينَ
«በዚያ እዚህ ባለው (ጸጋ) ውስጥ የረካችሁ ኾናችሁ ትተዋላችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
فِي جَنَّٰتٖ وَعُيُونٖ
«በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَزُرُوعٖ وَنَخۡلٖ طَلۡعُهَا هَضِيمٞ
«በአዝመራዎችም ፍሬዋ የበሰለ በኾነች ዘንባባም፤ (ውስጥ ትተዋላችሁን)
அரபு விரிவுரைகள்:
وَتَنۡحِتُونَ مِنَ ٱلۡجِبَالِ بُيُوتٗا فَٰرِهِينَ
«ብልሆች ኾናችሁ ከጋራዎች ቤቶችንም ትጠርባላችሁ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَا تُطِيعُوٓاْ أَمۡرَ ٱلۡمُسۡرِفِينَ
«የወሰን አላፊዎችንም ትዕዛዝ አትከተሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ٱلَّذِينَ يُفۡسِدُونَ فِي ٱلۡأَرۡضِ وَلَا يُصۡلِحُونَ
«የእነዚያን በምድር ላይ የሚያጠፉትንና የማያበጁትን፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُوٓاْ إِنَّمَآ أَنتَ مِنَ ٱلۡمُسَحَّرِينَ
(እነሱም) አሉ «አንተ በብዙ ከተደገመባቸው ሰዎች ብቻ ነህ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
مَآ أَنتَ إِلَّا بَشَرٞ مِّثۡلُنَا فَأۡتِ بِـَٔايَةٍ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
«አንተ ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ ከእውነተኞቹም እንደኾንክ ተዓምርን አምጣ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ هَٰذِهِۦ نَاقَةٞ لَّهَا شِرۡبٞ وَلَكُمۡ شِرۡبُ يَوۡمٖ مَّعۡلُومٖ
(እርሱም) አለ «ይህች ግመል ናት፡፡ ለእርሷ የመጠጥ ፋንታ አላት፡፡ ለእናንተም የታወቀ ቀን ፋንታ አላችሁ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَا تَمَسُّوهَا بِسُوٓءٖ فَيَأۡخُذَكُمۡ عَذَابُ يَوۡمٍ عَظِيمٖ
«በክፉም አትንኳት፡፡ የታላቅ ቀን ቅጣት ይይዛችኋልና፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
فَعَقَرُوهَا فَأَصۡبَحُواْ نَٰدِمِينَ
ወጓትም፡፡ ወዲያውም ተጸጻቾች ኾነው አነጉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَخَذَهُمُ ٱلۡعَذَابُۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
ቅጣቱም ያዛቸው፡፡ በዚህም ውስጥ ግሳፄ አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَّبَتۡ قَوۡمُ لُوطٍ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
የሉጥ ሕዝቦች መልክተኞችን አስተባባሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ أَخُوهُمۡ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በእርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልለምናችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَتَأۡتُونَ ٱلذُّكۡرَانَ مِنَ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«ከዓለማት ሰዎች ወንዶችን ትመጣላችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
وَتَذَرُونَ مَا خَلَقَ لَكُمۡ رَبُّكُم مِّنۡ أَزۡوَٰجِكُمۚ بَلۡ أَنتُمۡ قَوۡمٌ عَادُونَ
«ከሚስቶቻችሁም ጌታችሁ ለናንተ የፈጠረላችሁን ትተዋላችሁን? በእውነቱ እናንተ ወሰን አላፊዎች ሕዝቦ ናችሁ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُواْ لَئِن لَّمۡ تَنتَهِ يَٰلُوطُ لَتَكُونَنَّ مِنَ ٱلۡمُخۡرَجِينَ
(እነርሱም) አሉ «ሉጥ ሆይ! ባትከለከል በእርግጥ (ከአገር) ከሚወጡት ትኾናለህ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ إِنِّي لِعَمَلِكُم مِّنَ ٱلۡقَالِينَ
(እርሱም) አለ «እኔ ሥራችሁን ከሚጠሉት ሰዎች ነኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
رَبِّ نَجِّنِي وَأَهۡلِي مِمَّا يَعۡمَلُونَ
«ጌታዬ ሆይ! እኔንም ቤተሰቦቼንም ከሚሠሩት ሥራ (ቅጣት) አድነን፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
فَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም በጠቅላላ አዳንናቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
በቀሪዎቹ ውስጥ የኾነች አሮጊት ብቻ ስትቀር (እርሷ ጠፋች)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَأَمۡطَرۡنَا عَلَيۡهِم مَّطَرٗاۖ فَسَآءَ مَطَرُ ٱلۡمُنذَرِينَ
በእነሱም ላይ (የድንጋይን) ዝናምን አዘነምንባቸው፡፡ የተስፈራሪዎቹም ዝናም (ምንኛ) ከፋ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእመናን አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህ እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَّبَ أَصۡحَٰبُ لۡـَٔيۡكَةِ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
የአይከት ሰዎች መልክተኞችን አስተባበሉ፤
அரபு விரிவுரைகள்:
إِذۡ قَالَ لَهُمۡ شُعَيۡبٌ أَلَا تَتَّقُونَ
ሹዕይብ ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنِّي لَكُمۡ رَسُولٌ أَمِينٞ
«እኔ ለእናንተ ታማኝ መልክተኛ ነኝ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَأَطِيعُونِ
«አላህንም ፍሩ፤ ታዘዙኝም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَسۡـَٔلُكُمۡ عَلَيۡهِ مِنۡ أَجۡرٍۖ إِنۡ أَجۡرِيَ إِلَّا عَلَىٰ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በርሱም ላይ ምንም ዋጋ አልጠይቃችሁም፡፡ ዋጋዬ በዓለማት ጌታ ላይ እንጅ በሌላ ላይ አይደለም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
۞ أَوۡفُواْ ٱلۡكَيۡلَ وَلَا تَكُونُواْ مِنَ ٱلۡمُخۡسِرِينَ
«ስፍርን ሙሉ፡፡ ከአጉዳዮቹም አትኹኑ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَزِنُواْ بِٱلۡقِسۡطَاسِ ٱلۡمُسۡتَقِيمِ
«በትክክለኛ ሚዛንም መዝኑ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَا تَبۡخَسُواْ ٱلنَّاسَ أَشۡيَآءَهُمۡ وَلَا تَعۡثَوۡاْ فِي ٱلۡأَرۡضِ مُفۡسِدِينَ
«ሰዎችንም ነገሮቻቸውን አታጉድሉባቸው፡፡ በምድርም ላይ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱتَّقُواْ ٱلَّذِي خَلَقَكُمۡ وَٱلۡجِبِلَّةَ ٱلۡأَوَّلِينَ
«ያንንም የፈጠራችሁን የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች (የፈጠረውን) ፍሩ፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالُوٓاْ إِنَّمَآ أَنتَ مِنَ ٱلۡمُسَحَّرِينَ
አሉ «አንተ በብዛት ከተደገመባቸው ሰዎች ነህ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَنتَ إِلَّا بَشَرٞ مِّثۡلُنَا وَإِن نَّظُنُّكَ لَمِنَ ٱلۡكَٰذِبِينَ
«አንተም ብጤያችን ሰው እንጅ ሌላ አይደለህም፡፡ እነሆ ከውሸታሞች ነህ ብለን እንጠረጥርሃለን፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَأَسۡقِطۡ عَلَيۡنَا كِسَفٗا مِّنَ ٱلسَّمَآءِ إِن كُنتَ مِنَ ٱلصَّٰدِقِينَ
«ከእውነተኞቹም እንደኾንክ በእኛ ላይ ከሰማይ ቁራጭን ጣልብን፡፡»
அரபு விரிவுரைகள்:
قَالَ رَبِّيٓ أَعۡلَمُ بِمَا تَعۡمَلُونَ
«ጌታዬ የምትሠሩትን ሁሉ ዐዋቂ ነው፤» አላቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَكَذَّبُوهُ فَأَخَذَهُمۡ عَذَابُ يَوۡمِ ٱلظُّلَّةِۚ إِنَّهُۥ كَانَ عَذَابَ يَوۡمٍ عَظِيمٍ
አስተባበሉትም፡፡ የጥላይቷ ቀን ቅጣትም ያዛቸው፡፡ እርሱ የከባድ ቀን ቅጣት ነበርና፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَأٓيَةٗۖ وَمَا كَانَ أَكۡثَرُهُم مُّؤۡمِنِينَ
በዚህ ውስጥ አስደናቂ ተዓምር አልለበት፡፡ አብዛኞቻቸውም ምእምናን አልነበሩም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّ رَبَّكَ لَهُوَ ٱلۡعَزِيزُ ٱلرَّحِيمُ
ጌታህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው አዛኙ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّهُۥ لَتَنزِيلُ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
نَزَلَ بِهِ ٱلرُّوحُ ٱلۡأَمِينُ
እርሱን ታማኙ ጂብሪል አወረደው፤
அரபு விரிவுரைகள்:
عَلَىٰ قَلۡبِكَ لِتَكُونَ مِنَ ٱلۡمُنذِرِينَ
ከአስፈራሪዎቹ (ነቢያት) ትኾን ዘንድ በልብህ ላይ (አወረደው)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
بِلِسَانٍ عَرَبِيّٖ مُّبِينٖ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَإِنَّهُۥ لَفِي زُبُرِ ٱلۡأَوَّلِينَ
እርሱም (ቁርኣን) በቀድሞዎቹ መጻሐፍት ውስጥ (የተወሳ ነው)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَوَلَمۡ يَكُن لَّهُمۡ ءَايَةً أَن يَعۡلَمَهُۥ عُلَمَٰٓؤُاْ بَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ
የእስራኤል ልጆች ሊቃውንት የሚያውቁት መኾኑ ለእነርሱ (ለመካ ከሓዲዎች) ምልክት አይኾናቸውምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
وَلَوۡ نَزَّلۡنَٰهُ عَلَىٰ بَعۡضِ ٱلۡأَعۡجَمِينَ
ከአዕጀሞች ባንዱ ላይ ባወረድነውም ኖሮ፤
அரபு விரிவுரைகள்:
فَقَرَأَهُۥ عَلَيۡهِم مَّا كَانُواْ بِهِۦ مُؤۡمِنِينَ
በእነርሱ ላይ ባነበበውም በእርሱ አማኞች አይኾኑም ነበር፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
كَذَٰلِكَ سَلَكۡنَٰهُ فِي قُلُوبِ ٱلۡمُجۡرِمِينَ
እንደዚሁ (ማስተባበልን) በተንኮለኞች ልቦች ውስጥ አስገባነው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
لَا يُؤۡمِنُونَ بِهِۦ حَتَّىٰ يَرَوُاْ ٱلۡعَذَابَ ٱلۡأَلِيمَ
አሳማሚ ቅጣትን እስከሚያዩ ድረስ በእርሱ አያምኑም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَيَأۡتِيَهُم بَغۡتَةٗ وَهُمۡ لَا يَشۡعُرُونَ
እነርሱ የማያውቁ ሲኾኑ (ቅጣቱ) ድንገት እስከሚመጣባቸውም ድረስ (አያምኑም)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَيَقُولُواْ هَلۡ نَحۡنُ مُنظَرُونَ
(በመጣባቸው ጊዜ) «እኛ የምንቆይ ነን?» እስከሚሉም (አያምኑም)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَفَبِعَذَابِنَا يَسۡتَعۡجِلُونَ
በቅጣታችን ያቻኩላሉን?
அரபு விரிவுரைகள்:
أَفَرَءَيۡتَ إِن مَّتَّعۡنَٰهُمۡ سِنِينَ
አየህን ብዙ ዓመታትን ብናጣቅማቸው፤
அரபு விரிவுரைகள்:
ثُمَّ جَآءَهُم مَّا كَانُواْ يُوعَدُونَ
ከዚያም ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ቢመጣባቸው፤
அரபு விரிவுரைகள்:
مَآ أَغۡنَىٰ عَنۡهُم مَّا كَانُواْ يُمَتَّعُونَ
ይጣቀሙበት የነበሩት ሁሉ ከእነሱ ምንም አያብቃቃቸውም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَآ أَهۡلَكۡنَا مِن قَرۡيَةٍ إِلَّا لَهَا مُنذِرُونَ
አንዲትንም ከተማ ለእርሷ አስፈራሪዎች ያሏት (እና ያስተባበለች) ኾና እንጅ አላጠፋንም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ذِكۡرَىٰ وَمَا كُنَّا ظَٰلِمِينَ
(ይህች) ግሳፄ ናት፡፡ በዳዮችም አልነበርንም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَا تَنَزَّلَتۡ بِهِ ٱلشَّيَٰطِينُ
ሰይጣናትም እርሱን (ቁርኣንን) አላወረዱትም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَمَا يَنۢبَغِي لَهُمۡ وَمَا يَسۡتَطِيعُونَ
ለእነርሱም አይገባቸውም፤ አይችሉምም፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّهُمۡ عَنِ ٱلسَّمۡعِ لَمَعۡزُولُونَ
እነርሱ (የመላእክትን ንግግር) ከመስማት ተከለከሉ ናቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَلَا تَدۡعُ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ فَتَكُونَ مِنَ ٱلۡمُعَذَّبِينَ
ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አትግገዛ፤ ከሚቀጡት ትኾናለህና፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَأَنذِرۡ عَشِيرَتَكَ ٱلۡأَقۡرَبِينَ
ቅርቦች ዘመዶችህንም አስጠንቅቅ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱخۡفِضۡ جَنَاحَكَ لِمَنِ ٱتَّبَعَكَ مِنَ ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፤ (ልዝብ ኹን)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
فَإِنۡ عَصَوۡكَ فَقُلۡ إِنِّي بَرِيٓءٞ مِّمَّا تَعۡمَلُونَ
«እንቢ» ቢሉህም «እኔ ከምትሠሩት ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱلۡعَزِيزِ ٱلرَّحِيمِ
አሸናፊ አዛኝ በኾነው (ጌታህ) ላይም ተጠጋ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
ٱلَّذِي يَرَىٰكَ حِينَ تَقُومُ
በዚያ ለሶላት በምትቆም ጊዜ በሚያይህ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَتَقَلُّبَكَ فِي ٱلسَّٰجِدِينَ
በሰጋጆች ውስጥ መዘዋወርህንም (በሚያየው ጌታህ ላይ ተጠጋ)፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
إِنَّهُۥ هُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلۡعَلِيمُ
እነሆ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
هَلۡ أُنَبِّئُكُمۡ عَلَىٰ مَن تَنَزَّلُ ٱلشَّيَٰطِينُ
ሰይጣናት በማን ላይ እንደሚወርዱ ልንገራችሁን?
அரபு விரிவுரைகள்:
تَنَزَّلُ عَلَىٰ كُلِّ أَفَّاكٍ أَثِيمٖ
በውሸታም ኀጢአተኛ ሁሉ ላይ ይወርዳሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
يُلۡقُونَ ٱلسَّمۡعَ وَأَكۡثَرُهُمۡ كَٰذِبُونَ
የሰሙትን (ወደ ጠንቋዮች) ይጥላሉ፡፡ አብዛኞቻቸውም ውሸታሞች ናቸው፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
وَٱلشُّعَرَآءُ يَتَّبِعُهُمُ ٱلۡغَاوُۥنَ
ባለ ቅኔዎችንም ጠማማዎቹ ይከተሉዋቸዋል፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
أَلَمۡ تَرَ أَنَّهُمۡ فِي كُلِّ وَادٖ يَهِيمُونَ
እነርሱ በ(ንግግር) ሸለቆ ሁሉ የሚዋልሉ መኾናቸውን አታይምን?
அரபு விரிவுரைகள்:
وَأَنَّهُمۡ يَقُولُونَ مَا لَا يَفۡعَلُونَ
እነሱም የማይሠሩትን ነገር የሚናገሩ መኾናቸውን (አታይምን)፤
அரபு விரிவுரைகள்:
إِلَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ وَذَكَرُواْ ٱللَّهَ كَثِيرٗا وَٱنتَصَرُواْ مِنۢ بَعۡدِ مَا ظُلِمُواْۗ وَسَيَعۡلَمُ ٱلَّذِينَ ظَلَمُوٓاْ أَيَّ مُنقَلَبٖ يَنقَلِبُونَ
እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችን የሠሩ አላህንም በብዛት ያወሱ ከተበደሉም በኋላ (በቅኔ) የተከላከሉ ሲቀሩ፤ (እነርሱ አይወቀሱም)፡፡ እነዚያም የበደሉ (ከሞቱ በኋላ) እንዴት ያለን መመለስ እንደሚመለሱ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
அரபு விரிவுரைகள்:
 
மொழிபெயர்ப்பு அத்தியாயம்: ஸூரா அஷ்ஷுஅரா
அத்தியாயங்களின் அட்டவணை பக்க எண்
 
அல்குர்ஆன் மொழிபெயர்ப்பு - அம்ஹாரிக் மொழிபெயர்ப்பு - மொழிபெயர்ப்பு அட்டவணை

புனித அல் குர்ஆனுக்கான அம்ஹரிய மொழிபெயர்ப்பு- முஹம்மது சாதிக் மற்றும் முஹம்மது அல்தானி ஆகியோரால் மொழிபெயர்க்கப்பட்டது. அர்ருவ்வாத் மொழிபெயர்ப்பு நிலையத்தின் மேற்பார்வையில் திருத்தப்பட்டது. மேலதிக ஆலோசனைகள், தொடர்ச்சியான மதிப்பீடு மற்றும் மேம்படுத்தல் என்பவற்றுக்காக மொழிபெயர்ப்பின் மூலப்பிரதி பார்வைக்காக விடப்பட்டுள்ளது

மூடுக